Tuesday, January 26, 2016

በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች ግድግዳዎች ላይ የተቃውሞ ጽሑፎች ተጽፈው አደሩ


(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች በሚገኙ ግድግድዎች ላይ በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት የሚቃወሙና ጥያቄም የሚጠይቁ መፈክሮች ተጽፈው አደሩ:: በተለይ መንግስት ያሰራቸውን የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ፍርድ የሚቃወም; በሃገሪቱ በተቃዋሚዎች ላይ የሚሰጡ ፖለቲካዊ ፍርዶችን የሚቃወሙ; በኦሮሞ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ግድያ የሚያወግዙና ሌሎችም መፈክሮች በትላልቁ በግድግዳዎች ላይ ተጽፈው አድረዋል::
ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ተቃውሟቸውን በስርዓቱ ላይ ቢያሰሙም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የሕዝቡን ጥያቄ ወደ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚል አሁንም በርካታ ጋዜጠኞችን; የሃይማኖት መሪዎችን; የፖለቲካ ሰዎችን አስሮ በማሰቃየት እንዲሁም በመግደልም ላይ ይገኛል::
በአዲስ አበባ ግድግዳዎች ላይ ተጽፈው ያደሩ ተቃውሞዎችን በፎቶ ይመልከቱ::

addis ababa1addis ababaaddis ababa 3addis ababa2

No comments:

Post a Comment