Saturday, November 29, 2014

የህዝብ ነጻነት

ከሃገሩ የወጣ ሃገሩ እስኪመለስ
ቢጭኑት አህያ ቢጋልቡት ፈረስ
ይባል ነበር ድሮ ምንድንነን በሃገርስ
ከእንስሳ አሳንሰው አይደል የሚያዩንስ?
ከሰው ሳይቆጠር በትውልድ በሃገሩ
እነሱ ወርቅ  ዘር እኛ አንሰን ከአፈሩ
መጨፍለቅ  አልቆመ እንዲያ መወገሩ
መታፈን መገረፍ ጨለማ ቤት እስሩ
እንደከብት ቆዳ መሰነታተሩ
ዜጋው በሃገሩ ሞት ሲሆን ቀመሩ
ላይቀናው ሲያማትር ለስደት መብረሩ።
ሃገር የማይናፍቅ ምንድነው ነገሩ?
መሬት ቆርሶ የሚሰጥ ለውጩ አድልቶ፥
ከወራሪ ጠላት ይብሳል አብዝቶ።
ይብቃ መከተሉ እስቲ እንየው ቀርቶ።
ነጩ ፋሺዚምን የጣለው ክንድ ሳይዝል
ዘመን አመጣሹን ሊመክተው ሲችል
ከከገዢዎች ወህኒ አምልጦ ኮብልሎ
በሃገሩ ከመሞት ስንቱ ባህር ዘሎ
በረሃ አቋርጦ አካሉን አጉድሎ
ያገግማል እንጂ አይሄድ ሀገር ብሎ
ይመለሳል እንጂ አይወስን ጠቅልሎ።
Abraham ZTa
juk

የሕወሐት/ኢህአዴግ ባለስልጣናት ፒ.ኤች.ዲዎችን ከተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ተቋማት መግዛታቸውን ቀጥለዋል

የሕወሐት/ኢህአዴግ ባለስልጣናት ፒ.ኤች.ዲዎችን ከተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ተቋማት እየገዙ እንዳሉ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ።
news
የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ ሐጐስ ጐደፋይና ምክትላቸው አቶ አታክልቲ እንደሚገኙበት የጠቀሱት ምንጮቹ ለሁለቱ ባለስልጣናት በመቀሌ ሆስፒታል የሚሰራ የባዮስታቲክስ ባለሙያ በኩል የጥናት ፕሮፖዛላቸውን አሰርተው ፕሮፖዛሉ ፀድቆ ዋናውን ጥናት ይህ ባለሙያ ግለሰብ እየሰራላቸው እንደሚገኝ አያይዘው ገልፀዋል።
ባለስልጣናቱ ስለጥናቱ አንዳችም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ምንጮቹ አጋልጠዋል። ሌሎች ስድስት የህወሀት ባለስልጣናትም የማስተርስና ፒ.ኤች.ዲ ጥናት እየፃፈላቸው እንደሚገኝ ምንጮቹ አክለው ገልፀዋል። ሌሎች የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችም የዚህ ህገወጥ ተግባር ተሳታፊዎች ናቸው ያሉት ምንጮቹ በተለይ ሪፍት ቫሊ የተባለውን የግል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የሚስተካከል የለም ብለዋል። የኦህዴድ ባለስልጥናት ባለድርሻ የሆኑበት ይህ ዩኒቨርሲቲ ገንዘብ ለከፈለ ሁሉ ሰነድ አዘጋጅቶ ዲግሪና ማስተርስ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

የስደተኞትና የስደት ተመላሾች እጣ

8EF5BDEB-55F0-43A5-9205-44A05F770A20_w268_r1የምሥራቅ አፍሪቃ አገሮች በስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ላይ የጋራ ራእይና እቅድ እንዲኖራቸው ለማስቻል የታለመ የሁለት ቀናት ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተጀምሯል።
የስደተኞች አንዷ መዳረሻ በሆነችው የወቅቱ የአውሮፓ ሕብረት ፕሬዝዳንት ጣልያን አነሳሽነት የሚካሄደው ይህ ውይይት በአጭርና ረዥም ጊዜ የሚተገበሩ ግቦች ያመነጫል፤ ተብሎ ተጠብቋል።
በሌላ በኩል የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ ትላንት ስትራስበርግ ፈረንሳይ ለሚገኙት የአዉሮፓ ፓርላማና ምክር ቤት ንግግር ስለ ስደተኞች ሰብአዊ መብትና መከበር ንግግር አድርገዋል።
ርእስ ሊቃነ-ጳጳሱ በሁለቱም ስፍራዎች ባደረጉት ንግግር አዉሮፓ የቆመችለትን ሰብአዊ መብትን የማክበር መርህና ዴሞክራዊ እንድታከብር ጥሪ አድርገዋል።
የሮማው ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳስ በ25 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአውሮፓ ተቋማት ያሰሙትን ንግግር ተንተርሶ የተጠናቀረ ዘገባ ነው።

የነዳጅ ዋጋ በዓለም አቀፍ ደረጃ ቢቀንስም የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን የችርቻሮ ዋጋን አልቀነሰም

ለአመት ያህል በበርሜር ወደ 110 ዶላር ንሮ የቆየው የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ፤ ካለፈው ሐምሌ ወዲህ እየወረደ በያዝነው ሳምንት ከ75 ዶላር በታች የደረሰ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ ላይ መንግስት እስካሁን ቅናሽ አላደረገም።
በአመት በአማካይ ከሰባት በመቶ በላይ እየጨመረ የመጣው የኢትዮጵያ የነዳጅ ፍጆታ፣ ባለፈው አመት 3.4 ቢሊዮን ዶላር (ከ65 ቢሊዮን ብር በላይ) ወጪ እንዳስከተለ ታውቋል። ሸቀጦች ወደ ተለያዩ አገራት በመላክ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ ባለፉት አራት አመታት እድገት ባለማሳየቱ አመታዊው ገቢ ከሶስት ቢሊዮን ዶላር ገደማ ብዙም ፈቅ ባለማለቱ፣ የነዳጅ ግዢን እንኳ ለመሸፈን የማይበቃ ሆኗል።
news
በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ባለፈው አመት በነበረበት ቢቀጥል ኖሮ፣ በቀጣዩ አመት ኢትዮጵያ ሩብ ቢሊዮን ዶላር (5 ቢሊዮን ብር) ተጨማሪ ገንዘብ ለነዳጅ ግዢ ለማውጣት መገደዷ አይቀርም ነበር። ይሁን እንጂ፣ ያለማቋረጥ እየወረደ የመጣው የነዳጅ አለማቀፍ ዋጋ በስድስት ወራት ውስጥ ሲሶ ያህል ስለቀነሰ፣ ኢትዮጵያ ለነዳጅ ግዢ የምታውለው የውጭ ምንዛሬ ዘንድሮ እንደማያሻቅብ ተገምቷል።
እንዲያውም የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል ከ80 ዶላር በታች ሆኖ ከቀጠለ፣ የአንድ ቢሊዮን ዶላር (የ20 ቢሊዮን ብር ወጪ ቅናሽ ያስገኛል፡፡) በርካታ ነዳጅ አምራች አገራትን የሚቆጣጠሩ መንግስታት በአባልነት የተካተቱበት ኦፔክ የተሰኘው ማህበር፣ ሰሞኑን በነዳጅ ዋጋ ዙሪያ የተወያየ ቢሆንም፣ ውይይታቸው በአለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ለውጥ እንደማያስከትል ትናንት ቢቢሲ ዘግቧል። እየወረደ የመጣው የነዳጅ ዋጋ፣ የበርካታዎቹን መንግስታት ገቢ እንደሸረሸረ የገለፀው ቢቢሲ፣ ከፍተኛ የበጀት ጉድለት ያጋጥማቸዋል ብሏል። “ዋጋ እንዲያንሰራራ የነዳጅ ምርት መቀነስ አለብን” የሚል ጥያቄ ከሁለት መንግስታት በኩል እንደቀረበ ዘገባው ጠቅሶ፣ ጥያቄው በአብዛኞቹ መንግስታት ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱን አመልክቷል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነዳጅ ዋጋ መውረድ የጀመረው፣ በከፊል ከአለም ኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ጋር በተያያዘ ምክንያት ቢሆንም፣ ዋናው ምክንያት ግን የአሜሪካ ኩባንያዎች ከፍተኛ የነዳጅ ምርትን የሚያስገኝ አዲስ ዘዴ በመፍጠራቸውና ተጨማሪ ነዳጅ ማምረት በመጀመራቸው እንደሆነ ፎርብስ መፅሔት ዘግቧል።
ከአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ውጣ ውረድ ጋር፣ የኢትዮጵያ መንግስት በንግድ ሚኒስቴር በኩል በየወሩ የነዳጅ ዋጋ ተመን የሚያወጣ ሲሆን፣ ከጥቂት ጊዜያት በስተቀር አብዛኛውን ጊዜ የዋጋ ተመኑ በነበረበት እንዲቀጥል አልያም የአለም ገበያን ተከትሎ እንዲጨምር ሲወስን መቆየቱ ይታወሳል።
ባለፉት ስድስት ወራትም እንዲሁ፣ በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በፍጥነት እየወረደ ቢመጣም፣ በኢትዮጵያ ግን የችርቻሮ ዋጋ በነበረበት ደረጃ እንዲቀጥል አልያም እንዲጨምር የተደረገ ሲሆን፣ በያዝነው ወር መጨረሻ የዋጋ ተመኑ ላይ ምን አይነት ለውጥ እንደሚደረግበት ገና አልታወቀም። በተለመደው የመንግስት አሰራር፣ የዋጋ ተመን ውሳኔው በይፋ እስከሚገለፅበት እለትና ሰዓት ድረስ በሚስጥር ተጠብቆ ነው የሚቆየው።

ምንጭ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣ

ኩማ ደመቅሳ በዋሽንግተን ዲሲ ሆስፒታል ተኝተዋል

አቶ ኩማ ደመቅሳ በዋሽንግተን ዲሲ ሆስፒታል ተኝተው እንደሚገኙ ታማኝ ምንጮ አስታወቁ።
kuma demekesa
  • ኩማ በጭንቅላት እጢ (ቲዩመር) በሽታ ምክንያት ለከፍተኛ ህክምና ዲሲ መምጣታቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የመዳን ተሳፋቸው 90 በመቶ የተመናመነ መሆኑን ከሃኪሞች እንደተገለፀላቸው አስታውቀዋል።

ከባለቤታቸው ጋር የመጡት ኩማ ሆስፒታል ከመግባታቸው በፊት ባለፈው ሳምንት ማርዮት ሆቴል አርፈው እንደነበረ ሲታወቅ ሁለት ኢትዮጵያውያንን በሆቴሉ መተላለፊያ ላይ ሲያገኙ ክፉኛ ደንግጠው እንደነበረ ማወቅ ተችሏል። አሜሪካ -ዲሲ መምጣታቸው እንዳይታወቅባቸው የሚጠነቀቁትና ፍርሃት የሚታይባቸው ኩማ የስጋታቸው ምንጭ እንደሌሎች ባለስልጣናት ተቃውሞ ይገጥመኛል በሚል እንደሆነ ሲታወቅ የማያውቁትን ስልክ እንደማያነሱ ማረጋገጥ ተችሏል።
በተለይ የመዳን ተስፋ እንደሌላቸው ከተነገራቸው በኋላ ከኢትዮጵያ የሚደወልላቸውን ስልክ እንደማያነሱ ታውቋል። ኩማ ደመቅሳ ከ1993ዓ.ም በፊት ሙስና ውስጥ እንዳልገቡና ነገር ግን የአዲስ አበባ ከንቲባ ከሆኑ በኋላ በከፍተኛ ሙስና ከተዘፈቁት ባለስልጣናት ተርታ እንደተመደቡ ይታወቃል።

የቻይና ኤግዚም ባንክ ለመቐለ ወልዲያ ባቡር ፕሮጀክት ብድር ሊለቅ ነው

የቻይና ኤክስፖርትና ኢምፖርት (ኤግዚም) ባንክ ለመቐለ ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት 1.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር ሊለቅ ነው፡፡
f4dd5c1a7bbb150619bc2bac1c3d9648_Lየገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በሚኒስቴሩ ከፍተኛ ኃላፊዎችና የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ጌታቸው በትሩ የተገኙበት ቡድን በቅርቡ ወደ ቻይና ሄዶ ባንኩ ባስጠናው የአዋጭነት ጥናት ላይ ማብራርያ አቅርበዋል፡፡
የፕሮጀክቱ የአዋጭነት ጥናት በኢትዮጵያ በኩል ከዚህ ቀደም የተጠና ቢሆንም፣ የቻይናው ኤግዚም ባንክ በድጋሚ ኩባንያ ቀጥሮ የአዋጭነት ጥናት አስጠንቷል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያትም የቻይና መንግሥት በኢትዮጵያ የፖታሽ ማዕድንን ከማልማት ረገድ ይህ የባቡር ትራንስፖርት መስመር የሚኖረውን ጠቀሜታ አስረግጦ ለመረዳት እንደሆነ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በዚህም መሠረት በጥናቱ ላይ ለተነሱ ውስን ጥያቄዎች ማብራርያ እንደተሰጠና በቅርቡም ገንዘቡ ይለቀቃል ተብሎ እንደሚገመት ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡
የመቐለ ወልዲያ ፕሮጀክት 268.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፣ የቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ለፕሮጀክቱ ብድር ለማቅረብ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር መግባባታቸው ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ ባቡር ኮርፖሬሽን በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ እያደረጋቸው የሚገኙ ሦስት የባቡር ፕሮጀክቶች ማለትም የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር፣ የአዲስ አበባ ሜኤሶና የሜኤሶ ድሬዳዋ ደወሌ የባቡር ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ ከቻይና በተገኘ ብድር በመገንባት ላይ ይገኛሉ፡፡
ብቸኛው ከቻይና ውጪ በተገኘ ብድር ለመገንባት ዝግጁ የሆነው ፕሮጀክት የአዋሽ ወልዲያ የባቡር መስመር ሲሆን የሚገነባው ከአውሮፓ ባንኮች በተገኘ ብድር ነው፡፡ ይህም መስመር በቻይና ብድር ከሚገነባው የመቐለ ወልዲያ ፕሮጀክት ጋር የሚገናኝ ነው፡፡

የሶስት ወር ህጻን ልጇን አንቃ የገደለችው በ16 ዓመት እስራት ተቀጣች

ህጻን ልጇን በሻሽ አንቃ በመግደል የጣለችው ተከሳሽ ላይ የእስራት ቅጣት የተወሰነባት መሆኑን የኢትዮጵያ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
crimeበአርሲ ዞን የሒጦሳ ወረዳ ፖሊስ እንደገለፀው በተከሳሽ መስታወት ደረጄ ላይ የእስራት ቅጣት ሊወስንባት የቻለው ከወለደችው የሶስት ወር እድሜ ያለውን ልጇን ሐምሌ 14 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ጎንዴ ፊንጨማ ልዩ ስሙ ሾሪማ ተብሎ ከሚታወቅበት አካባቢ በመውሰድና ከበቆሎ ማሳ ውስጥ በመግባት በያዘችው ሻሽ አንቃ በመግደሏ ነው፡፡ እንደ ሒጦሳ ወረዳ ፖሊስ ገለጻ የተገደለውን ህጻን የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ መሰረት አስከሬኑ ተነስቶ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል በተደረገለት የአስከሬን ምርመራ መሠረት ህጻኑ ታንቆ መገደሉ ተረጋግጧል ተብሏል፡፡
ተከሳሿ በቁጥጥር ስር ውላ በሰጠችው የእምነት ቃልም በቡና ቤት አስተናጋጅነት እየሰራች ሳለ ከተዋወቀችው አሽከርካሪ ጋር ፍቅር በመመስረቷና ከወለደችለት በኋላ ሊረዳት ፍቃደኛ ባለመሆኑ ድርጊቱን ልትፈጽም መነሳሳቷን ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የአርሲ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ መስታወት ደረጄን በአስራ ስድስት ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኖባታል፡፡

Tuesday, November 25, 2014

ቆንጆ መጽሔት ተከሰሰች


1507102_562094813935307_9108390875166530007_nከሁለት ሳምንት በፊት ከማዕከላዊ የምርመራ ቢሮ ከወዲያኛው ጫፍ የደወለው ሰው እንደነገረኝ ‹‹ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ነው›› ብሎ ደወለልኝ፡፡ ደዋዩ ቆንጆ መጽሔት መሆኑን ካጣራ በኋላ ዋና አዘጋጇ ስልክ ላይ ብደውል ዝግ ነው ፤ ጥር ወር ላይ ባወጣችሁት ዘገባ እኛ ጋ ክስ ተመስርቶባችኋል አለኝ፡፡ ስለሆነም ለዋና አዘጋጇ መልዕክት አድርሱ መጥታ ቃሏን ትስጥ አለኝ፡፡ ለጊዜው በቅርብ እንደሌለች ነገርኩት፡፡ ‹‹እሺ›› ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ ድጋሚ ባለፈው ሳምንት አንድ ስልክ ተደወለ፡፡ በወቅቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለነበርኩ ስልኩን ማንሳት አልቻልኩም፡፡ ስወጣ ግን ደወልኩ፡፡ ስልኩን ያነሳችው ሴት ‹‹የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዋና (ማዞሪያ ስልክ)›› መሆኑን ነገረችኝ፡፡ እንግዲህ ይህ ስልክ ግቢ ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ የሚጠቀሙበት በመሆኑ እንደ እኔ ሞባይሉ ላይ ሚስድ ኮል አይቶ መልሶ ለደወለ ማን እንደደወለለት ገና ተጠያይቆ ነው የሚታወቀው፡፡

ትናንት የደወለችው ግን ቁጣ በተቀላቀለው ንግግር ‹‹ለምንድነው ስልክ የማታነሱት›› አለች፡፡ ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢንተርቪውና ሌሎች ጥሞና የሚፈልጉ (የስልክ ድምጽ የሚረብሹ) ስራዎች ላይ ለሆነ ጋዜጠኛ ስክል ያለማንሳት የተለመደ ጉዳይ መሆኑን ላስረዳት ሞከርኩ፡፡ ስንትን በስንት እንዳባዛችው ባይታወቅም በተደጋጋሚ ጊዜ መደወሏን ተናግራ ‹‹ለረቡዕ ጠዋት ማዕከላዊ መጥተው ቃሎትን እንዲሰጡ›› አለች፡፡

በዚህ ጉዳይ ጥር ላይ ያሳተማችሁት ዕትም ስለተባልኩ ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ ያሳተምናቸውን ሁለት ዕትሞች ደግሜ ለማየት ሞከርኩ፡፡ የታየኝ ነገር የለም፡፡ እንግዲህ እነሱ የታያቸው ነገር ይኖራል፡፡ በዚያ ላይ ከሳሽ ማን እንደሆነ አልታወቀም፡፡ አቃቤ ህግ? መንግስት? ግለሰብ? ማህበር?. . . የታወቀ ነገር የለም፡፡

ባለፈው ዓመት የዛሬው ኢቢሲ የአምናው ኢቲቪ በሰራው ተከታታይ የዶክመንተሪ ፊልም ምክኒያት በብዙ መጽሔቶችና ጋዜጦች ላይ ክስ ተመስርቶ የቆንጆ መጽሔት አዘጋጆችን ጨምሮ በርካታ ጋዜጠኞች ለስደት ተዳርገዋል፡፡ ተመስገን ደሳለኝንና ብዙ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ዶክመንተሪው የግል የህትመት ውጤቶችን በሙሉ ሀጢአተኛ አድርጎ ስለፈረጀ ማተሚያ ቤቶች ጋዜጣና መጽሔቶችን ማተም ፈርተዋል፡፡ ዶክመንተሪው የግል ሚዲያውን ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የግንቦት 7 እና የሻዕቢያ ተላላኪ፤ የታሰሩ ሙስሊሞችን ገና ጉዳያቸው በፍ/ቤት እየታየ ባለበት ሁኔታ ላይ አክራሪ፤ ብሎገርና ሌሎችንም ስም እየሰጡና እየፈረጁ በፍ/ቤቶች ላይ ጫና እስከማሳደር የሚደርስ ዘገባዎች ሲሰራጩ ኢቲቪ ነውና ማንም አይጠይቀውም፡፡ የግሉ ሚዲያ ላይ ሲሆን ግን. . .
አዲስ አድማስ ጋዜጣ ባለፈው ቅዳሜ ለንባብ እንዳበቃው የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ላይ አሁንም ክስ የሚመሰረትባቸው የህትመት ውጤቶች መኖራቸውን ጠቁሟል፡፡ በዚህ መልኩ ወደ ፊት በኢትዮጵያ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ውጪ የህትመት ውጤቶች ስለመኖራቸው እንድንጠራጠር ያደርገናል፡፡

ጋዜጠኞችን በማሰርና በማሳደድ የቀዳሚነቱን ስፍራ የተቆናጠጠችው ሀገራችን የወደፊት የዴሞክራሲ እጣ ፈንታዋ ምን ይሆን? ይህ ነገር በዚሁ እንዳይቀጥል፤ የጋዜጠኞች እስርና ስደት እንዲቆም ከመንግስት ኃላፊዎች ጋር ቀርቦ ለመነጋገር የተደረገው ጥረት በኃላፊዎቹ ግትርነት መፍትሔ ማግኘት አልቻለም፡፡ ‹‹የተሰደደና የታሰረ ጋዜጠኛ የለም›› እስከማለት ደርሰዋል አይናቸውን በጨው አጥበው፡፡ የጋዜጠኞች እስርና ስደት የሀገርንና የመንግስትን ስም ጥቁር ጥላሸት ከመቀባት ውጪ ለሀገርም ለህዝብም የሚጠቅም ነገር ያለመኖሩን በተደጋጋሚ ቢነገርም ሹማምንቱ ጆሮ ዳባ ልበስ ብለዋል፡፡
የነገው የማዕከላዊ ቀጠሮዬን እያሰብኩ ይህቺን ሰነቅኩላችሁ፡፡

ቆንጆ መጽሔት ተከሰሰች


1507102_562094813935307_9108390875166530007_nከሁለት ሳምንት በፊት ከማዕከላዊ የምርመራ ቢሮ ከወዲያኛው ጫፍ የደወለው ሰው እንደነገረኝ ‹‹ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ነው›› ብሎ ደወለልኝ፡፡ ደዋዩ ቆንጆ መጽሔት መሆኑን ካጣራ በኋላ ዋና አዘጋጇ ስልክ ላይ ብደውል ዝግ ነው ፤ ጥር ወር ላይ ባወጣችሁት ዘገባ እኛ ጋ ክስ ተመስርቶባችኋል አለኝ፡፡ ስለሆነም ለዋና አዘጋጇ መልዕክት አድርሱ መጥታ ቃሏን ትስጥ አለኝ፡፡ ለጊዜው በቅርብ እንደሌለች ነገርኩት፡፡ ‹‹እሺ›› ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ ድጋሚ ባለፈው ሳምንት አንድ ስልክ ተደወለ፡፡ በወቅቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለነበርኩ ስልኩን ማንሳት አልቻልኩም፡፡ ስወጣ ግን ደወልኩ፡፡ ስልኩን ያነሳችው ሴት ‹‹የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዋና (ማዞሪያ ስልክ)›› መሆኑን ነገረችኝ፡፡ እንግዲህ ይህ ስልክ ግቢ ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ የሚጠቀሙበት በመሆኑ እንደ እኔ ሞባይሉ ላይ ሚስድ ኮል አይቶ መልሶ ለደወለ ማን እንደደወለለት ገና ተጠያይቆ ነው የሚታወቀው፡፡

ትናንት የደወለችው ግን ቁጣ በተቀላቀለው ንግግር ‹‹ለምንድነው ስልክ የማታነሱት›› አለች፡፡ ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢንተርቪውና ሌሎች ጥሞና የሚፈልጉ (የስልክ ድምጽ የሚረብሹ) ስራዎች ላይ ለሆነ ጋዜጠኛ ስክል ያለማንሳት የተለመደ ጉዳይ መሆኑን ላስረዳት ሞከርኩ፡፡ ስንትን በስንት እንዳባዛችው ባይታወቅም በተደጋጋሚ ጊዜ መደወሏን ተናግራ ‹‹ለረቡዕ ጠዋት ማዕከላዊ መጥተው ቃሎትን እንዲሰጡ›› አለች፡፡

በዚህ ጉዳይ ጥር ላይ ያሳተማችሁት ዕትም ስለተባልኩ ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ ያሳተምናቸውን ሁለት ዕትሞች ደግሜ ለማየት ሞከርኩ፡፡ የታየኝ ነገር የለም፡፡ እንግዲህ እነሱ የታያቸው ነገር ይኖራል፡፡ በዚያ ላይ ከሳሽ ማን እንደሆነ አልታወቀም፡፡ አቃቤ ህግ? መንግስት? ግለሰብ? ማህበር?. . . የታወቀ ነገር የለም፡፡

ባለፈው ዓመት የዛሬው ኢቢሲ የአምናው ኢቲቪ በሰራው ተከታታይ የዶክመንተሪ ፊልም ምክኒያት በብዙ መጽሔቶችና ጋዜጦች ላይ ክስ ተመስርቶ የቆንጆ መጽሔት አዘጋጆችን ጨምሮ በርካታ ጋዜጠኞች ለስደት ተዳርገዋል፡፡ ተመስገን ደሳለኝንና ብዙ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ዶክመንተሪው የግል የህትመት ውጤቶችን በሙሉ ሀጢአተኛ አድርጎ ስለፈረጀ ማተሚያ ቤቶች ጋዜጣና መጽሔቶችን ማተም ፈርተዋል፡፡ ዶክመንተሪው የግል ሚዲያውን ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የግንቦት 7 እና የሻዕቢያ ተላላኪ፤ የታሰሩ ሙስሊሞችን ገና ጉዳያቸው በፍ/ቤት እየታየ ባለበት ሁኔታ ላይ አክራሪ፤ ብሎገርና ሌሎችንም ስም እየሰጡና እየፈረጁ በፍ/ቤቶች ላይ ጫና እስከማሳደር የሚደርስ ዘገባዎች ሲሰራጩ ኢቲቪ ነውና ማንም አይጠይቀውም፡፡ የግሉ ሚዲያ ላይ ሲሆን ግን. . .
አዲስ አድማስ ጋዜጣ ባለፈው ቅዳሜ ለንባብ እንዳበቃው የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ላይ አሁንም ክስ የሚመሰረትባቸው የህትመት ውጤቶች መኖራቸውን ጠቁሟል፡፡ በዚህ መልኩ ወደ ፊት በኢትዮጵያ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ውጪ የህትመት ውጤቶች ስለመኖራቸው እንድንጠራጠር ያደርገናል፡፡

ጋዜጠኞችን በማሰርና በማሳደድ የቀዳሚነቱን ስፍራ የተቆናጠጠችው ሀገራችን የወደፊት የዴሞክራሲ እጣ ፈንታዋ ምን ይሆን? ይህ ነገር በዚሁ እንዳይቀጥል፤ የጋዜጠኞች እስርና ስደት እንዲቆም ከመንግስት ኃላፊዎች ጋር ቀርቦ ለመነጋገር የተደረገው ጥረት በኃላፊዎቹ ግትርነት መፍትሔ ማግኘት አልቻለም፡፡ ‹‹የተሰደደና የታሰረ ጋዜጠኛ የለም›› እስከማለት ደርሰዋል አይናቸውን በጨው አጥበው፡፡ የጋዜጠኞች እስርና ስደት የሀገርንና የመንግስትን ስም ጥቁር ጥላሸት ከመቀባት ውጪ ለሀገርም ለህዝብም የሚጠቅም ነገር ያለመኖሩን በተደጋጋሚ ቢነገርም ሹማምንቱ ጆሮ ዳባ ልበስ ብለዋል፡፡
የነገው የማዕከላዊ ቀጠሮዬን እያሰብኩ ይህቺን ሰነቅኩላችሁ፡፡

በአማራ ክልል ቅርሶች በከፍተኛ ሁኔታ እየዘረፉ ከሐገር እየወጡ ነው፡፡

ዳር ፲፮(አስራ ስድስትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል የደቡብ ወሎና የሰሜን ሸዋ ዞን ወረዳዎችና አብያተክርስቲያናት ተገቢ ጥበቃ ባለማግኘታቸው የተለያዩ ቅርሶች የተዘረፉና የጠፉ መሆኑን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ በአመት አንድ ጊዜ በሚዘጋጀው የቅርስ ጉባኤ ላይ ገለጸ፡፡ በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ በተለያዩ ወረዳዎች 37 ቅርሶች መሰረቃቸውን ይፋ ያደረጉት የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ አለበል ደሴ ፣በክልሉ ከ2001 በጀት ዓመት ጀምሮ እስከ 2006 መጨረሻ ባለው ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች 124 መድረሳቸውን ተናግረዋል።
artበክልሉ ብቸኛ የሆነው የደሴ ሙዙየም በስተደቡብ አቅጣጫ ጫካ በመሆኑና ዙሪያውም ምንም ዓይነት አጥር ስለሌለውየጥበቃ ቢሮው ተሰብሮ በውስጡ የነበሩ ሁለቱም የጦር መሣሪያዎች ከነሙሉ ጥይታቸው ከመሰረቃቸውም በላይ እስከአሁንም አለመገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ ቅርሶች በመስታውት ዉስጥ ተቆልፈው ስላልተያዙ ለአቧራና ለአላስፈጊ ንክኪ መጋለጣቸውም ሃላፊው ተናግረዋል።
በሰሜን ሸዋ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ ጥንታዊ አብያተክርስቲያናት ውስጥ የሚገኙ ጥንታዊ ቅርሶች ተገቢውን ጥበቃ ባለማግኘታቸው በሌቦች መሰረቃቸውንና አብዛኛዎቹ አለመገኘታቸውን በውይይቱ ላይ የተወሳ ሲሆን የአንኮበር ማሪያም ቤተክርስቲያን 3 የብር መቋሚያዎችና 7 የብር ጸናፅልች፤ በአንፆኪያ ወረዳ በ03 ቀበሌ አጥቆ በዓታ ማሪያም ቤተክርስቲያን 9 የብራና መጽሃፍት፣ 3 ሌሎች የመገልገያ መጽሃፌት እና 1 የመፆር የነሃስ መስቀል ተሰርቀው እስካሁን አልተገኙም።
በሞረትና ጅሩ ወረዳ የሚገኘው ይማደጋ ቅደስ ሚካኤሌ ቤተክርስቲያን ውስጥ ዘራፉዎች ገብተው 2 የቅዱስ ሚካኤል ጽላት ፣ 1 የመስቀለ እየሱስ ጽላት ፣ 3 የነሃስ የመፆር መስቀል፣ 1 መጎናፀፉያ የተዘረፉ መሆኑ ለአብነት በውይይቱ ላይ ተነስቷል፡፡ በቅርስ ዘረፋው የባለስልጣናት እጅ አለበት ሲሉ ሃሳብ ያነሱት ተወያዮች እንዴት በህገወጥ የሰዎች ዝውውር የተሳተፉ ባለስልጣናት ቅርስ ዘረፋን ይከላከላሉ ተብሎ እንዴት ይገመታል ሲሉ ሞግተዋል፡፡
በጋይንት አካባቢ ብቻ ከ30 ያላነሱ አብያተክርስቲያናት ቅርሶች መዘረፋቸውን ጥቆማ እንደደረሰው የክልሉም ሆነ የፊደራል ባህል፣ቱሪዝምና ፓርኮች ልማት ሚኒስቴር ቢያሳዉቅም ጉዳዩ ተጣርቶ የተወሰደ እርምጃ የለም፡፡ በአማራ ክልል የሚገኙ የቅርስ መገኛ ተቋማት 3ሺ እንደሚደርሱ ቢገመትም ሙዙየም በማሰራት ቅርሶቻቸውን በጥንቃቄ ለእይታ እያቀረቡ ያሉት ግን 13 ብቻ ናቸው።
በሌላ በኩል ደግሞ በብሄራዊ ሙዚየም ውስጥ ይገኙ የነበሩ የኢትዮጵያን ታሪክ የሚዘክሩ መጽሃፍት በተቀነባበረ መልኩ በርካሽ ዋጋ ለነጋዴዎች የተሸጡ መሆናቸው የተዘገበ ሲሆን፣ እስካሁን ለኢሳት በደረሰው መረጃ የጆብ ሎድፍ 1664፣ 1700፣ 1800፣ የጀምስ ብሩስ፣ የካርሎ ሮሲኒ፣ በጣሊያን ወረራ ጊዜ ይታተሙ የነበሩ የቄሳር መንግስትና የሮማ ብርሃን የተባሉ ጋዜጦች፣ 2 ሺ ኪሎ ግራም ይመዝናሉ የተባሉ የአጼ ቴዎድሮስ፣ የአጼ ዮሃንስና የአጼ ሚኒሊክ ደብዳቤዎች ተቸብችበዋል።

አንዱዓለም አራጌ በአስቸኳይ ይፈታ!!

አንዱዓለም አራጌ በአስቸኳይ ይፈታ!!
አንዱዓለም አራጌ የታሰረው ያለበደሉ ነው፡፡ ስለዚህ በአስቸኳ ሊፈታ ይገባል፡፡ ንፁህን ግለሰብ ማሰር የህግን ውድቀትና የገዥዎችን የሞራል ዝቅጠት እንጂ የህግ የበላይነት አያሳይምና፣ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈታ!! አንዱዓለም ሲታሰር ሚሊዮን ንፁሃንን ኢትዮጵያን እንደታሰሩ መታወቅ አለበት፡፡
አሁንም አንዱዓለም የህሊና እስረኛ ሰላማዊ የፖለቲካ ታጋይ እንጂ አሸባሪና ወንጀለኛ አይደለም፡፡
አንዱዓለም አራጌ በአስቸኳይ ይፈታ!!
Like 

Saturday, November 15, 2014

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው፣ ተጠንቀቅ አማራ! ከቦጋለ ካሳዬ

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው
amaraየደላቸው… የሰው ልጅ ይቅር፤ ማንኛውም ህመም ሊሰማው የሚችል ፍጡር አይጠቃ! አይገደል! ብለው እሪ! እሪ! ይላሉ። ያነባሉ። እንቅልፍ አይወስዳቸውም። የሌሎች ስቃዮች እነርሱንም ያስቃያቸዋል።
አንዴ ተማሪ እያለን የደብረ-ብርሃንን የብርድ ልብስ ፋብሪካ ልንጎበኝ ሄድን። አስተማሪያችን ፕሮፌሰር ፓንዲታ የሚባል ህንድ ነበር። ለምሳችን ስጋ ያለበት ሳንዱውች ተዘጋጅቶአል። የደብረብርሃን ብርድ ለጠኔ ዳርጎን ነበርና ሰፍ ብለን ሳንዱቻችንን መግመጥ ጀመርን። አስተማሪያችን ግን ከንፈሩ ደርቆ አይን አይናችንን ያየናል። ለመብላት ፈልጎአል። “ለምን አትበላም?” ብለን ብንጠይቀው፤ “ስጋ አልበላም። እምነቴ ማንኛውንም ፍጡር አትግደል ይላል።” ብሎን እርፍ!
በሆላንድ የእንሳስት መብት ተሙዋጋች የፖለቲካ ፓርቲ አለ። አሁን ዳች ፓርላማ ውስጥ ሁለት መቀመጫ አለው። ፓርቲው መሬት ማንኛውንም የሰው ልጆች ፍላጎቶች ለማሙዋላት ትችላለች። ይሁን እንጂ የሰዎች ስግብግብነትን ለማሙዋላት አትችልም ብሎ ያምናል። እንደ ፓርቲው ከሆነ ለምሳሌ የእንስሳትና እንስሳት ተዋጽኦ እንዱስትሪ፤ 30% በተፈጥሮ ይገኙ የነበሩ የእንሥሣትና የእጽዋት ዘሮችን በማጥፋት ተጠያቂ ነው። ከብቶችንም ለማደለብም ሆነ የወተት ጎርፍ ለማምረት መኖ በገፍ ስለሚያስፈልገው፤ በዚህም ሳቢያ መሬት ከድሃ ገበሬዎች ስለሚቀማ፤ የአለም ርሃብ እየተባባሰ የመጣበት አንዱ ዋናው ምክንያት ከእንስሳትና እንስሳ ተዋጾእኦ እንዱስትሪ ተግባር ጋር የተያያዘ መሆኑን ያረጋግጣል። በተጨማሪም የእርድ እንሳሳት ሲታረዱ ህመም እንዳይሰማቸው ይደረግ ይላል። አንዳንድ እንስሳት በተለይ አሳማዎች ለእርድ ሲቀርቡ ያለቅሳሉ! አንጀት ይበላል ነገሩ።
አሜሪካውያት ሴቶች የምጥን ህመም ስለሚፈሩ ማደንዘዣ ይወጋሉ ይባላል። በአውሮፓ ግን ሴቶቹ ማማጡ በተፈጥሮ ያለ ነገር ስለሆነ፤ እናምጣለን! የምን ማደንዘዣ ነው… እቴ! ብለው የምጡን ህመም ጥርሳቸውን ነክሰው ይጋፈጡታል።
የሰው ልጅ የቆየ እምነትም ይሁን ዛሬ በሰለጠነው አለም እንደምናየው እንስሳትም ይሁን ሰዎች እንዳይሰቃዩ የሚደረጉትን ጥረቶች ጨረፍ ካደረግን ወደ ዋናው ጉዳያችን እንግባ።
በኢትዮጵያ መገዳደል አዲስ ነገር አይደለም። በታሪካችን ግዛት በማስፋፋት፣ የተለያዩ ጭቆናዎችን በመቃወም፣ በሃይማኖት ሳቢያ የደረሱ እልቂቶች አሉ። ቀይና ነጭ ሽብር ትልቅ ጠባሳ የጣሉቡን እልቂቶች ናቸው።
አይኖችቻን ይጥፉ! እምቢ አናይም ካላልን፤ በህወሃት አገዛዝ በአማራ ላይ አላባራ ያለው ግድያ ግን ለየት ያለ ነው።
1. በኢትዮጵያ የአማራ(ሸዋ) ገዢ መደብ እየተባለ የሚጠራውን(ክላፋም እንደጻፈው፤ 48% ኦሮሞ ነው፣32% አማራ፣ትግሬዎችና ሌሎች ናቸው) እንደጠላት መፈረጅ የጀመሩት የብሄር-ብሄረሰብ ጥያቄ ያነሱ ሰዎችና ድርጅቶች ናቸው። በወገኖቻችን በኩል የጉዳዩ አነሳስ ለእኩልነት ተብሎ የታሰበና አማራን ለጥቃት ኢላማ ለመዳረግ ሆን ተብሎ የተደረገ አልነበረም ብሎ ማሰብ ይቻላል። በተጨማሪም በአገራችን የመናገር፣ የመጻፉና የመወያየት ነጻነት ስለሌለ እንደዚህ ያለው ፖለቲካ ወደሁዋላ ይዞ የሚመጣውን መዘዝ አስቀድሞ ማየት ዛሬ ላይ ተቀምጦ ያለፈውን እንደመተቸት ቀላል ነገር እንዳልሆነ እንገነዘባለን።
1.2 ይሁን እንጂ ዶ/ር መራር ጉዲናም እንደታዘበው፤ በተለይ ለእኩልነት አማሮች ከማንኛው የበለጠ ትልቅ ዋጋ ቢከፍሉም ዛሬ ግን ተክድዋል። በሁሉም በሚለው ነገር መስማማት ባይቻልም መራራ ህሊና ያለው ሰው ነው። እንደ አፈንዲ ሙተኪ አግላይ፣ ስድና እሥስት አይደለም።
2. እ.አ.አ በ1995 ዴፕሎማሲ በሚል ሄንሬ ኬሲንጀር በጻፉት መጽሃፍ ውስጥ ፤ አሜሪካ የአንደኛው ዓለም ጦርነት እንዳለቀ(1919) ፤ ዳግም በአውሮፓ ጦርነት እንዳይነሳ አውሮፓውያንን አንዱ አገር አንዱን እጠቀልላለሁ በሚል የሚደረግ የሃይል ግንባታ ፍክክር እንዲያቆሙና፤ ከእንግዲህ ብሄሮች የራሳቸውን እድል በራሳቸው መወሰን አለባቸው የሚለውን መርህ እንዲከተሉ ማስጠንቀቁዋን እናነባለን። ይህ የአሜሪካ አለምን በብሄር የማደራጀቱ ፓሊሲ በክሊንተን አስተዳደርም ዮግዝላቪያን በማፍረስ በጉልህ መከሰቱን አይተናል። በኢትዮጵያም ጊዜውን ጠብቆ ይቀር ይሆን?
3. የተቀረው የአፍሪካም ፍዳ ይኼው ነው። ምንም እንኩዋን አህጉሩ (ከኢትዮጵያ በስተቀር) በአውሮፓውያን ተቀራጭቶ የዛሬዎቹ አገሮች ቢፈጠሩም፤ ሰላም እንዲሰፍን በሚል ሽፋን የአፍሪካን ሃብት ለማራቆት በጎሳ ላይ የተመሰረቱ አገሮች እንዲመሰርቱ የሚያቀነቅኑ አሉ። አንዱ አቀንቃኝ የመለስ ዜናዊ አማካሪ የነበረ “ተራማጅ” የሚባል ሶሻል ዴሞክራት ነው። ቻይና ሳይታሰብ መጣና ጫወታውን ለውጠው እንጂ።
4. ወደ ኢትዮጵያ ስንመለስ፤ ጨቁዋኙ አማራ፤ ተጨቁዋኝ ሊሎቹ ተብሎ ህወሃትን፣ ኦነግንና ኦብነግን በሚደግፉ የውጭ ኃይሎች ሆን ተብሎ ድርሰት ተደርሶአል። በጉዳይ ላይ ብዙ መጻህፍት ተጽፈዋል። ብዙ ፒ.ኢች.ዲዎች ተመርቀውበታል። ይህቺን ማስታወሻ ዛሬ ቅዳሜ በምጽፍበት ሰዓት እንኩዋን የኢትዮጵያ ማህበር በሆላንድ ሁለት በዚሁ ድርሰት ዶ/ር የተባሉ ቀንደኛ የአማራ ጠላቶች ጠርቶ ስለ ኢትዮጵያ የወደፊት ፖለቲካ አቅጣጫ እንድንወያይ ጋብዞናል። እኔ ጠላቶቼን ቀደም ብዬ ስላማውቃቸው ከእነርሱ ጋር ስለ አገሬ አቅጣጫ መፍትሄ ለመፈለግ አልሂድም። የውይይት መብታቸውን ግን አከብራለሁ።
5. የውጭ ኃይሎች እነዚህ ብሄረተኛ ድርጅቶችን የሚደግፉበት ምክንያት ምንድን ነው? ህወሃትን የሚደግፉበት ምክንያቶች ግልጽ ናቸው። መሬት አግኝተዋል። ሽብርን ለመዋጋት በሚል ሰበብ ለሞት የሚማገድ የሰው ሃይል በቀላሉ ያገኛሉ። የህወሃት የጎሳ ፖለቲካም የኢትዮጵያን አገራዊ ስሜት ለማደብዘዝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ከመሬቱም፣ከወታደር መማገዱም ሆነ እርስ በእርስ ከማናከሱ ፖለቲካ ህወሃት ተጠቃሚ ነው። ፕሮፌሰር ዓለማየሁ በሚገባ እንዳስቀመጡት፤ ህወሃት በምጽዋት የሚኖር የለማኞች አገዛዝ ነው።
6. ኦብነግን በመደገፍ የሚገኝም ነገር አለ። ጋዝ ወይም ነዳጅ ነው። እ.አ.አ በ2009 በጄኔቫ አንድን የእንግሊዝ ኢምባሲ ሹመኛ ከሰዎች ጋር ሆነን አንገጋግረን ነበር። ኤርትራም ተሹሞ የሰራ ሰውና ስለ አካባቢው እውቀት ያለው ነው። ስለ ስብአዊ መብቶች ጉዳይ በኢትዮጵያ ገለጻ አደረግንለት። አላማችን በየአራት አመቱ አባል አገሮችን ስለ ስብአዊ መብቶች መሻሻልና ችግሮች በሚገመግመው የተባበሩት መንግስታት ጉባኤ ላይ (ዩኒቨርሳል ፕሮዴክ ሪቪው) የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ትኩረት እንዲያገኝ ለማድረግ ነበር። በጉባኤው ላይ አስተያየት ሰጭ አገሮች ከ5 ደቂቃ በላይ አይሰጣቸውም። ታዲያ እንግሊዙ የትኛውን የሰብአዊ ጥሰት አነሳ? በኦጋዴን ብቻ የተከሰተውን። በቃ። ሌላ ጥሰት ለወሬ ነጋሪም አልተሰማ። ቅዱስ ቫቲካን፣ሲዊዘርላንድ፣ሲውዴን፣ አውስትራሊያና ብራዚል በሚገባ በኢትዮጵያ ያለውን ችግር ለጉባኤው አስረድተዋል። የአሜሪካው ግን በጣም የተለየ ነበር። ኦባማ ገና በስልጣን የመጣበት ወቅት ስለነበር ለዴሞክራሲ መስፋፋት ተስፋ አልጨለመም ነበር። የአሜሪካው አምባሳደር የህወሃትን የጎሳ የበላይነት በጉባኤው ላይ ፍርጥ በማድረጉ፤ ሆዳሙ ፍሰሃ ገዳ ውሸት ነው ብሎ ቡራ ከረዩ ያለበት ትያትር ነበር ያየነው። ትእቢተኛው መለስ ዜናዊም ቀብጦ አምባሳደሩን ባለጌ ማለቱን አስታውሳለሁ።
7. ኦነግን በመደገፍና ኦሮሚያን በማስገንጠል ኦሮሞም ሆነ የውጭ ኃይሎች ምንም! ወላ ሃንቲ! የኢኮኖሚ ጥቅም አያገኙም። ባእዳን ዛሬ ካጋበሱት መሬት የበለጠ ኦነግ ኦሮሚያን መስርቶ ቢኮፈስ የበለጠ ጥቅም ሊያገኙ ይችላሉ? አይችሉም። ኦሮሞም እንደ አማራ አብሮ በደሙና በአጥንቱ በገነባት ኢትዮጵያ ሁሉ መብቱ ተከብሮ ነው መኖር የሚፈልገውም፤ የሚሻለውም።
7.1 ከተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ እየለዩ፤ ኦሮሞዎች ትናትም ሆነ ዛሬ ተጨቁኑዋል እየተባለ ጎልቶ በስብአዊ ድርጅቶች ሆነ በአለም አቀፍ ድርጅቶች የሚነገረው፤ የኦሮሞ ተቆርቁዋሪነቱ(ብሄረተኝነቱ) ገኖ ኢትዮጵያዊነቱ ተሙዋጥጦ ይጠፋል ከሚል ምኞት ነው። አቤ ቶኪቻው ይኼን ወዲያው ተገንዝቦ ማለፊያ አስተያየቱን እንዲህ ሲል ስንዝሮአል፤..”ስንቅ ያቀበሉ ኦሮሞ ያልሆኑም ታስረው እየማቀቁ ይገኛሉ።” የኦሮሞ ጥያቄ የሚባለው በተጨማሪም እንዲገን የሚደረገው አማራና ኦሮሞ እንዳይቀራረቡ ለማድረግና የወያኔን የግዛት ዘመን አደጋ እንዳይገጥመው ለመከላከል ነው። አማራና ኦሮሞ ተቀራርበው እንደ አምስቱ የአርበኞች ትግል(ጉራጌዎችም አሉበት) መዋጋት ከጀመሩ ህወሃት በግድ ይጠፋል። ይኼን እየተገነዘቡ፤ ብዙዎቹ የኦነግ ብሄረተኞች በአማራ ጥላቻ ስላበዱ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ለአድነታችን ጠላቶች መሳሪያ ሁነዋል። እነ ተስፋዬ ገ/አብና አንድናቂዎቻቸው አፈንዲ ሙተኪም የሚሰሩት ይኽንኑ ስራ መሆኑን አንብበናል። በጆራችን ስምተናል፡፡
7.2 ኢሳያስም ቢሆን እንዲህ እየባለገ በስልጣን ላይ እንዲቆይ የሚፈለገው፤ ኢትዮጵያን በማፍረሰ ቀመር ውስጥ ሊጠቅም ስለሚችል ነው። ዴምሄት 45 ሺህ የታጠቀ የትግሬ ጦር ነው። አቶ ጌታቸው ረዳ በትግርኛ ቁውንቁዋ ከተገኙ ምንጮች ሰሞኑን እንዳስነበበን፤ ትግርኝ ትግሪኝን ለመሰረት ኢሳያስ ያዋቀረው ጦር ነው። ሴቪ አድና ግን ከመሃከላችን ሆኖ ዴምሂት ወያኔን ለመጣል የሚታገል ጦር ነው ይለናል። የሚገርመው ሴቪ አድና አስብ የትግራይ ነው ሲል ጽፎኣል። ለነገሩ አስብ የአፋር ነው፡፡ የሚቀርበውም ለወሎ ነው። ትግራይ ትግርኝ ግን ግን አማራጩ ፕላን ወይም ፕላን ቢ ነው። ይቅናችሁ።
8. እንደመደምደሚያ፤ የሰው ልጅ የሚያመዛዝን አእምሮ ስላለው፤ እንኩዋን ለራሱ ለሰው ለእንሳስት ነፍስ ሲሳሳ አይተናል። ህወሃት ሰው በነገዱ አማራ ነህ እያለ መገደል የጀመረው በወልቃይት ጸገዴ ነው። እኛ ግን በስፋት የሰማነው መጀመሪያ በአርባጉጉ ነው። በአርባጉጉ አራጆቹ እርጉዝ ሴቶችን በሳንጃ ከመግደላቸው በፊት በጽንሱ ጾታ ፤ አማራ ወንድ? ወይስ ሴት? በማለት ይወራረዱ እንደነበርና ጡት ቆርጠው እስከማስበላት እንደደረሱ ራሳቸው ኦሮሞዎቹ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጽፈው ከሰጡት ደብዳቤ መረዳት ይቻላል።
8.1 አማራ ተገደለ! ራስህን ተከላከል እያልን የምንጮኸው በዘር ቆጠራ ተለክፈን አይደለም። እጅግ ስብአዊነት ስለሚሰማን እንጂ። እንሆ 23 አመታት ተቆጠሩ፤ ፕሮፌሰር ዓስራት ወልደየስ እንዳሉት ጠላቶቹ አማራ የሚሉትን ፈልገው ሲያጡት አናይም። ስንት አማራ እየጠፋ አምነስቲ ምን አለ? ምንም። የፕሮፈሰር መስፍን አማራ የለም ነገር፤ አማራን ከጥቃት ለመከላከል አላስቻለም።
8.2 ስብአዊ መብቶች ብዙ ናቸው። ዓማራ ተብሎ በተለያዩ መንገዶች ሲጠፋ፤ ጠፋ! ተፍናቀለ! ተገደለ ብለን ስንጮኽ የጎሳን ፖለቲካ ማራመድ ነው የሚሉን ስለሰብአዊነት የጠለቀ ግንዛቤ የሌላቸው ናቸው። ለነገሩ እውቀት እንደ አባት ስም አይወረሰም። ጥናትና ጥረት ያስፈልግዋል። አንዳንዶቹ ከተለያዩ ጎሳዎች በመወለዳቸው አማራ አምሮ ከተነሳ የትኛውን እንመርጣለን ብለውም የሚጨነቁ ቅይጥ-ጎሰኞች አሉ። እነዚህ ሰዎች ስብአዊነትን ከሁሉም በላይ መሆኑን የዘነጉ ናቸው። ለነገሩ በኢትዮጵያ ዳርቻ ካሉ ጎሳዎች በስተቀር ያልተቀላቀለ የለም። ስለዚህ በኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ አገርን ለመበዝበዝና ካልሆነም ለመበተን የሚካሄድ ስልታዊ ሃሳብ/አይዶሎጂ እንጂ በትውልድ ሃረግ የሚመዘን ጉዳይ አይደለም። እኛ አማራ ንጽህ ዘር ነው፤ የራሱን መንግስት ያቁም አላልንም። በአማራነቱ የሚደርሰበት ጥቃት በአገዛዙ እቅድ የሚደረግ ስለሆነ ራሱን ከጥፋት ያድን ነው የምንለው። ምንም እንኩዋን በቅርቡ ባሳተመው መጽሃፉ ስለ አማራ እልቂት አንድም ነገር ያልተነፈሰው ብርሃኑ እንክዋን በደረሰበት ትችትና፤ ይኼንኑ ጉዳይ በመገንዘብ ባለፈው መስከረም የኢትዮጵያ አዲስ አመት ምክንያት በማድረግ በአደረገው ንግግር አማራው በተለይ የጥቃት ኢላማ መደረጉን አምኖአል። ከአክሱም የተገኘው ጌታቸው ረዳ

ሊቀ ጳጳሱ ከስራና ወደ ውጭ አገር እንዳይወጡ ታገዱ (የዕግዱን ደብዳቤ ይዘናል)

Abune Yacob
የምስራቅ ኣፍሪካ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስና መቀመጫቸውን በደቡብ ኣፍሪካ ኣድርገው የነበሩት ብጹእ ኣቡነ ያዕቆብ ከሃገር አንዳይወጡና ከስራቸው መታገዳቸውን ለዘሐበሻ የደረሰው መረጃ ኣመለከተ፥፥ የዘሐበሻ ታማኝ ምንጮች ከነ ደብዳበው የላኩት መረጃ የሚከተለው ነው፥፥ ዝርዝሩን ይዘን አንመለሳለን፥፥
aba yakob
aba yakob 3
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

ቤተክርስቲያን እንዳይፈርስ የተቃወሙት ዜጎች ታፍሰው የት እንደደረሱ አልታወቀም; “ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው”

(ነገረ ኢትዮጵያ) ትናንት ህዳር 3/2007 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ የማሪያም ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ በመቃወማቸው የታፈኑት ዜጎች የት እንደደረሱ አልታወቀም ሲሉ በወቅቱ ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎችና የእምነቱ ተከታዮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
news
በወቅቱ 600 ያህል ዜጎች ተገኝተው ቤተ ክርስቲያኗ እንዳትፈርስ ሲቃወሙ እንደተመለከቱ የገለጹት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የቤተ ክርስቲያኗን መፍረስ የተቃወሙትን ጨምሮ ሌሎች በአካባቢው የተገኙ ዜጎችም በፖሊስ መታፈሳቸውን ገልጸዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ‹‹ህዝቡ በሰንደቅ አላማ አምላክ አታፍርሱብን እያለ ቢለምንም እነሱ ግን ጥይት ወደላይ በመተኩስ ህዝቡን ከማሸበራቸውም በላይ ያገኙትን እየደበደቡ በ9 የድንጋይ መጫኛ መኪና አስገድደው በመጫን ወዳልታወቀ ቦታ ውስደዋቸዋል፡፡ አድማ በታኝ ፖሊስ ቄስ፣ አዛውንት፣ ህጻንና ሴት ሳይል ያገኘውም አፍሶ ወስዷል፡፡ የኮብል ስቶን ጠራቢዎች ሳይቀሩ በአካባቢው በመገኘታቸው ታፍሰው ታስረዋል፡፡ አሁን የት እንዳሉ አይታወቅም፡፡›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራች ከሁለት አመት በላይ እንደሆነ የገለጹት አንድ የአካባቢው ነዋሪ ‹‹ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራችበት ጊዜ ጀምሮ እንድትፈርስ ጥያቄ እንደቀረበ ተገልጾልን አያውውም፡፡ አሁን ነው ደርሰው ያፈረሱት፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን አገልጋዮች ጨምሮ በጣም ብዙ ሰው በዱላ ተደብድቧል፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው፡፡›› ሲሉ ቅሬታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎችና አማኞች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ቤተ ክርስትያኗ እንዳትፈርስ እንደተቃወሙ፣ አድማ በታኝ ፖሊስ በአካባቢው ያገኘውን ሰው ካፈሰ በኋላ ቤተ ክርስቲያኗን በማፍረስ ቆርቆሮውን በመኪና ጭኖ እንደሄደ የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

Friday, November 14, 2014

ፍልፍሉ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ

በምነው ሸዋ ኢንተርቴይመንት በኩል ወደ ሰሜን አሜሪካ መጥቶ የነበረውና በተለያዩ ስቴቶች የኮሜዲ ሥራዎችን ቢያቀርብም ብዙም ተቀባይነት ሳያገኝ ወደ ሀገር ቤት የተመለሰው ኮሜዲያን ፍልፍሉ ተመልሶ ወደ አሜሪካ ለመምጣት ፈቃድ ቢጠይቅም በአሜሪካ ኤምባሲ በኩል መከለክሉ ታወቀ::
filfilu
ኮሜዲያኑ ወደ ሃገር ቤት እመለስበታለሁ ብሎ ለኢምባሲው ከተናገረበት ቀን በጣም አሳልፎ ወደ ሃገር ቤት በመመለሱ የተነሳ አሁን በድጋሚ ወደ አሜሪካ የመግቢያ ፈቃድ ሲጠይቅ ተከልክሏል:: ፍልፍሉ በስሜን አሜሪካ በተዘዋወረባቸው ከተሞች በኮሜዲ ዝግጅቶቹ ላይ የተጠበቀው ያህል ሰው ያልተገኘ ሲሆን በርካታ ፕሮሞተሮችም ለኪሳራ መዳረጋቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲገልጹ ይሰማል::
ፍልፍሉ ለመድረክ ስራዎች ሳይሆን ለተቀረጹ ስራዎች ብቻ የሚሆን ኮሜዲያን ነው የሚሉት ለሙያው ቀረብ ያሉ ሰዎች ያልፈጠረበትን ስታንዳፕ ኮሜዲ አቀርባለሁ ብሎ ለትዝብት መውደቁን ይናገራሉ::
ኮሜዲያን ፍልፍሉ የባለስልጣን ልጅ አግብቼ ቤተሰቦቿ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊገሉኝ ይፈልጋሉ እያለ በሰሜን አሜሪካ ቆይታው ሲናገር የቆየ ሲሆን ሃገር ቤት እንደገባም በዱሪዬዎች መደብደቡ አይዘነጋም::
ኮሜዲያን ፍልፍሉ ወይም በረከት በቀለ የአሜሪካ መግቢያ ፈቃድ ከተከለከለ በኋላ በየሚዲያው በመቅረብና በሄደበት ቦታ ሁሉ አሜሪካንን በማጥላላት ላይ እንደሚገኝም ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል::

አዲሱ የመኢአድ አመራር ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር የተጀመረው ግንኙነት እንደሚያስቀጥል አስታወቀ

 የፓርቲውን ማህተም ተሰርቄያለሁ ብሏል
aeupዛሬ ህዳር 4/2007 ዓ.ም በፓርቲው ዋና ጽፈት ቤት መግለጫ የሰጠው የመኢአድ አዲሱ አመራር ከመኢአድ ጋር ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸውና ከሌሎቹም የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ከአሁን ቀደም አብሮ ለመስራት የተጀመረውን እንቅስቃሴ እንደሚያስቀጥል አስታውቋል፡፡
በ2003 ዓ.ም ከታህሳስ 15-17 ድረስ አይቤክ ሆቴል ጠቅላላ ጉባኤ ከተካሄደ በኋላ በፓርቲው አመራሮች መካከል ችግር እንደነበር የገለጸው አዲሱ አመራር ከዛ በኋላ አቶ አበባው መሃሪ ፕሬዝደንት የሆኑበት አካሄድ ትክክል እንዳልነበር፤ለአራት አመት ያህል በሁለቱ ቡድን መካከል የነበረው አለመግባባት በእርቅ እንደተቋጨና አቶ አበባው ኃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው እንደለቀቁ የጻፉትን ደብዳቤ ዋቢ አድርጎ ገልጾአል፡፡ በመሆኑም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ያለ ምንም ገደብ ወደ መኢአድ ጽ/ቤት መምጣት ይችላሉ ሲል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
በአንጻሩ አዲሱ አመራር በህገ ወጥ መንገድ ነው ወደ ስልጣን የመጣው በሚል ቅር የተሰኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ዛሬ ከሰዓት መግለጫ እንደሚሰጡ ተሰምቷል፡፡ ጉዳዩን ለማጣራት አቶ አበባው መሃሪ ጋር በተደጋጋሚ ብንደውልም የእጅ ስልካቸውን ሊያነሱ ባለመቻላቸው ሀሳባቸውን ማጠቃለል አልቻልንም፡፡
በሌላ በኩል አዲስ አመራር ማህተሙ አዲሱ አመራር ከመምጣቱ በፊት ፓርቲው ውስጥ በነበሩትና በአዲሱ አመራር ጋር ባልተስማሙ አካላት እንደተሰረቀ አስታውቋል፡፡ ‹‹ማህተሙ ከዚህ ቤት በነበሩ ሰዎች ተሰርቋል፡፡ ይህን ጉዳይ በወቅቱ ለፖሊስ አመልክተናል፡፡ በፓርቲው ማህተም እኛ የማናምንበትና ህገ ወጥ ነገር ቢሰራበት ተጠያቂ የሚሆኑት እነሱ ናቸው፡፡›› ሲሉ አዲሱ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ ገልጸዋል፡

ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣ አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች ! የተረፈችው የእህት ብርቱካን ጉዳይ …(ነቢዩ ሲራክ)

birtukan
የማለዳ ወግ …
ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣
አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች !
የተረፈችው የእህት ብርቱካን ጉዳይ …
በሃገረ ሊባኖሰ ቤሩት  ከ4ኛ ፎቅ ወድቃ የተረፈችው እህት ብርቱካን  ጤንነት የተስተካከለና ከድካም ህመሟ ሙሉ በሙሉ እያገገመች መሆኑን መረጃዎች ማምሻውን ደርሰውኛል ። የቆንስል ሃላፊዎች አልማዝን ሲያነጋግሯት በሊባኖስ ቆይታ ስራ መስራት እንጅ ወደ ሀገር ቤት መመለስ እንደማትፈልግ እንደገለጸችላቸው አምባሳደር ሐሊማ ሙሃመድ አጫውተውኛል። በቀጣይ ቀናትም ህክምና እየወሰደች ያለችበትን መካስድ ሆስፒታልን ለቃ እንደምትወጣ ፣ በቤሩት የቆንስል መጠለያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን እንደምትከታተል ተረድቻለሁ !
ተስፋ የቆረጡት ኢትዮጵያውያን አስተያየት …
    በብርቱካን ጉዳይ ዙሪያ ያነጋገርኳቸው ብዙ ነዋሪዎች የቆንስል ተዋካዮች ላይ እምነት እንደሌላቸው ይገልጻሉ ። እንደ አማራጭም የብርቱካንን ጉዳይ በጠበቃ አስይዘው ለመከራከር የሚቻልበትን ንገድ ለማፈላለግ ስራ መሰራት አለበት ሲሉ  ” የቆንስል ሃላፊዎችን ዲስኩር ማመን ትቶ የተለመደው የነዋሪውን ትብብር ማስተባበር ያሻል ” ይላሉ።  ለምን በመንግስት ተወካዮቻችን እምነት አጣችሁ?  ማለቴ አልቀረም ፣ ምላሻቸው ዘርዘር ያለ መረጃና ማስረጃ ያለው እውነት ይመስላል። አንድ ያሉኝን ብቻ ላንሳው  … በሃገራ ባንዴራ ስር ፣ በቆንስሏ በር በጥጋበኛ “ጀብራሬ” አረብ  እየተጎተተች ስትደበደብ የቆንስል ሀላፊዎች ምንም አለማድረጋቸው ፣  ከዚያም  ሃኪም ቤት በገባች በቀናት ልዩነት ” ራሷን በራሷ ገደለች !” መርዶ ነጋሪና ሬሳ ተቀባይና ላኪ ከመሆን ያለፈ ስራ የመብት ማስጠበቅ ስራ በቆንስል መስሪያ ቤቱ አለመሰራቱን ያጣቅሳሉ።  ከዚሁ ጋር በተዛማጅ ከአንድ ወር በፊት እዚያው ሊባኖስ “የአሰሪዋን ህጻን ልጅ አፍና ገድላለች! ” በሚል በፍርድ ውሳኔ ያልተሰጠው ጉዳይ በመገናኛ ብዙሃን ቀርቦ ነበር። በቀረበው መረጃ ስማችን ጎደፈ ። ዳሩ ግን የቀረበው መረጃ ኢትዮጵያዊቷ ወንጀለኛ አለመሆኗ ፍንጭ ሰጠ ፣ የራሳቸው ዜጎች ከሳሽ ባቀረበው መረጃና ማስረጃ ተመርኩዘው የተገላቢጦሹን አሳዩት ። ይህ ሁሉ ሲሆን የመንግስት ተወካዮቻችን ከሳሽን ወደ ተከሳሽነት የሚያሸጋግረውን መረጃ እንኳ ይዘው ታሳሪዋ ኢትዮጵያዊት እህት በዋስ መብቷ  ተጠብቆ በውጭ ሆና  እንድትከራከር አለማድረጋቸው በቆንስሉ የብርቱካን ክትትል ላይ የረባ ውጤት የማምጣት አቅም እንደሌላቸው ማሳያ ነው በማለት የሰላ ሂስና ወቀሳ ያቀርባሉ ።
የተስፈኞቹ ኢትዮጵያውያን አስተያየት …
    ” በቤሩት የቆንስል መ/ቤት ከበፊቱ የተሻለ ለውጥ ይታያል! ”  ያሉኝ ወገኖች ፣ ለውጥ ለመምጣቱና ለመታየቱ የሚያቀርቧቸው ጥቃቅን የቆንስል ግልጋሎት አሰጣጥ መረጃዎች ናቸው ።  ያም ሆኖ የመስራት አቅሙ የላቸውም ያሉኝ  የሚያነሱትን ” …የከዚህ በፊቱን የአለም ደቻሳና ሌላው ሌላው አሳዛኝ የመብት ጥበቃ ጉድለት “ያለፈው አለፈ ፣ ይሁን !”  ቢባል አሁን ድረስ እንዳልተሻሻሉ ብዙ ማሳያ አለ። ከወር በፊት  በነፍስ ግድያ ወንጀል ያለ ተጨባጭ መረጃ የታሰረችውን እህት ቆንስሉ አያማክሯትም ። ለዋስ መብቷን አላስጠበቁላትም።  ” በማለት “የቀረበውን የሰላ ሂስ ” ለውጥ አለ! ” ባዮች በተጨበጠ መከራከሪያ መላሽ ለመስጠት አልተቻላቸውም ።  ብቻ የቀረበውን ወቀሳ ሳያስተባብሉ ” በለውጥ ተስፋ ከማድረግ የተሻለ ነገር የለም! ”  በማለት የቆንሰል መ/ቤቱ የብርቱካንን ጉዳይ በቅርብ ተካታትሎ ውል እንደሚያስይዘው ያላቸውን ተስፋ አጋርተውኛል  !  …ቀጣዩ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ቢቸግርም ዛሬ የእህት ብርቱካንን በአሰቃቂ ሁኔታ መውደቅና ከከፋ አደጋ መትረፏ በሊባኖስ ቤሩት ካሉት ባለፈ በአለም ዙሪያ ሆነን ጉዳዩን በቅርብ ለተከታተልን ሁሉ እፎይታ ሆኗል  … ተመስገን ነው !  እናም ” ያገባናል ” ባዮች በእህት ብርቱካን ሰናይ ዜና ተደስተን ፊታችን ወደ ሌላዋ ግፉዕ ማዞር ግድ ብሎን  ወደ አልማዝን እንርዳ ” ዘመቻችን ፊታችን መዞራችን እውነት ነው!
የአካል ጉዳተኛዋ የአልማዝ ጉዳይ  …
   ህዳር 2 ቀን 2007 ምሽት በሊባኖስ  የብርቱካንን ከፎቅ መውደቅ አሳዛኝ ዜና ስሰማ በሌላኛው አረብ ሀገር በኦማን የመኪና አደጋ ደርሶባት የአካል ጉዳተኛ በሆነችው በእህት አልማዝ ጉዳይ ተወጥሬ ነበር።  ከተለያዩ አረብ ሃገራት እና በሃገር ቤት በማህበራዊ መገናኛዎች ተገናኝተን የተውጣጣን ወደ ስድስት የምንደርስ ወንድምና እህቶች  ባንድ እየመከርን ነው። አላማችን ከመረጃ ልውውጡ ባለፈ የወገናችን እንባ በተግባር መጥረጉም “ያገባናል !” ብለን ነው። የእህት አልማዝን እርዳታ ለማሳካት ማድረግ ስላለብን ጉዳይ እየመከርን ባለበት ወቅት ከቤሩት የብርቱካን አደጋና  “አትተርፍም!” የተባለ መረጃ ደረሰኝ … ሌላዋን የአረብ ሃገር ኦማን ጉስቁል እህት አልማዝን አሰብኳት …
    እህት አልማዝ የአረብ ሃገሩ ስደት ሲነሳ ከመንግስት ጀምሮ እስከ ግለሰብ የእኛ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ እህቶቻችን አደጋ ላይ ጥሏቸዋል።በህግ ሽፋን ተሰጥቷቸው በሚንቀሳቀሱ ወሮበላ ህግ ይጣሳል ፣  ለህዝብ ቆመናል በሚሉ የመንግስት ተቋማት ህግ ይጣሳል ፣  በመልካም አስተዳደር እጦት ፣ በሙስና  ህይወታችን ከፍቷል ፣ በተለያያየ መንገድ በአረበወ ሃገራት ለገነነው “ዘመናዊ ባርነት ” ድጋፍ እያደረግን እያበረታታን ነው ። ይህን ማለቴ ያለነገር አይደለም ፣ በአረቡ ሃገር በኦማን አካሏ ተሰናክሎ  የእኛን እርዳታ ጠባቂ የሆነችውን እህት አልማዝ አበሳ አስታውሼ ብዙውን አውጥቸ አወረድኩት …
    …አልማዝ አንድ ፍሬ ጉብል ሳለች ካላቻ ጋብቻ   ትዳርን ሳታውቀው መስርታ ልጅ ወልዳ ነበር ፣ ብዙም ሳይቆይ ጉብሏ እናት ሆነች ፣  ኑሮ አልሞላ አልሳካ ብሏት ወደ አረብ ሀገር ወደ ኦማን ተሰደደች … ሙሉ አካሏን ይዛ ለስራ ብላ በራ ከሄደችበት ኦማን ሞስካት ብዙም ሳትቆይ ለመኪና አደጋ ተጋለጠች ፣  ሆስፒታል ገባች ፣ ለወራት በህክምና ስትረዳ ብትቆይም አዕምሮዋ ፣ እግሯና እጇ ብሎም መላ አካሏ የከፋ ጉዳት ደረሰባቸው ፣ አይሆኑ ሆነች: (  ከሃገር ቤት ጀምሮ በአረብ ሀገራት ብርቱ መረብ ያላቸው ደላሎች እህት አልማዝ ሆስፒታል ከገባች በኋላም በጉዳቷ ለመጠቀም መስገብገባቸውን ጠልቆ መረጃ መሰብሰብ አሞኛል ፣ ዛሬ ወደ ክፉዎች ባለ ጊዜ ደላላ ባለጸጎች መሰሪ ምግባር ዳሰሳ አልገባም !  … እህት አልማዝ በተስፋ አቢሲኒያ በጎ አድራጊ ቡድን  አባላት ፣ በተለይም በመስራቹ ብርቱ ወንድም በወዳጀ በመሳይ አክሊሉ ( በኑቢያ ኩሽ ቀዳማዊ  ) እና በወዳጆቹ ብርታት  በአሳር በመከራ ሃገር ቤት ገብታለች ። መቄዶንያ የአረጋውያን ደጋፊ በጎ አድራጊ ቡድን ትብብርም መጠለያም ተሰጥቷታል ።  … እህት አልማዝ እዚህ ላይ ደርሳለች …  ይህም ተመስገን ነው!
   ይህም ሁሉ ሆኖ የአልጋ ቁራኛ የሆነችው አልማዝ ” ከህመም ጉዳቷ የምታገግምበት ተስፋ አለ ” በመባሉ የእርዳታ ስራ ተጀምሯል ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተጀመረው እርዳታ እዚህ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ያለውን እርዳታ ለማስተባበር ሃላፊነት ከወሰድኩ ቀናት ወዲህ ወገኖች አልማዝን ለመርዳት ያሳዪት መነቃቃት እጅግ በጣም አበረታች ሆኖ ቀጥሏል። በኮንትራት ስራ በየአረቡ ቤት የሚሰሩ እህቶቸ የ “ነግ በኔ ” ብለው በሰብአዊነት እያደረጉት ያለው መተባበር ውስጥን ስሜት የሚያረካ ለመሆኑ እማኝ ለመሆን ታድያለሁ  !  የቤት ቆሻሻ ለመጣል መውጫ ቀዳዳውን ፈልገው ያላቸውን ለአልማዝ ለማካፈል ያሳዩት ቅንነት ፍጹም በቃላት ልገለጽ የማይቻለኝን ኩራት፣ በእህቶቼ እንድጎናጸፈው ዘንድ  ምክንያት ሆኖኛል  ! ድምጻዊ  ጆሲ እንደ ሀውስ ያን ሰሞን እርዳታ ለማሰባሰብ ሲሞክር በገጠመውና በሆነው በግኖ ይመስለኛል   ” ለመስጠት መሰጠት ያስፈልጋል! ”  ማለቱ በእኔም ላይ ደርሶ  እውነት ነው ብያለሁ  ! ለእኔ እርዳታ ማድረግ ትርጉሙ ገንዘብ መስጠት ብቻ አይደለም ፣ ቀና ማሰብ ፣ መረጃ መለዋወጥ ፣ ሌላ ተዛማች ተጎጅውን የሚደግፍ ስራ መስራት ፣ የሚረዳን አለመቃወም ፣ ገንዘብ  ከመስጠት ባለፈ ለተጎጅው ወገን ወገናዊ አብሮነት  ፍቅር መግለጫ ነው… ባይ ነኝ  !
    ለማንኛውም ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣ እሰየው ነው!   እህት አልማዝ በኦማን ተሰናክላ እንዳትቀር ወገናዊ ትብብራችን ትሻለችና እናስብበት !  በዚህ የበጎነት መንገድ በመጓዝ በጠና የተጎዱ ወገኖቻችን  በመደገፍ ልንታደጋቸው ካልቻልን ከንፈር መምጠጡ ብቻ እንዳላዋጣን ከእኛ በላይ የሚያውቀው የለም ! እናም የዜጎቹን መብት እንዲያስከብር መንግስትን ስንወተውት የዝሆን ጀሮ ሰጥቶ አልሰማን ቢልም ጩኸት በደላችን እስኪሰማ እየጮህንም ቢሆን በመደጋገፉ የተጎዱትን እየነቀስን በማውጣት የቻልነውን መስራት የዜግነት ውዴታ ግዴታ ነው ባይ ነኝ  !
ሁሉም ለበጎ ነው  !
ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 5 ቀን 2007 ዓም

Tuesday, November 11, 2014

ታላቅ ሕዝባዊ የውይይት መድረክ በአምስተርዳም ከተማ * አበራ የማነ አብ * ዶ/ር አረጋዊ በርሔ እና ዶ/ር መላኩ በሚገኙበት

የፊታችን ቅዳሜ ኖቬበር 15 ቀን 2014 ከ 14:00- ጀምሮ
አድራሻ: 1e Helmersstraat 106, 1054 EG Amsterdam next to VENA office
EthioAmsterdam
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--

“የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ”

አገሬ (ከስዊድን)፣ 2014-11-05
ይህን ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ዋናው ምክንያት በድረ-ገጽ ላይ ”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” በሚል ርዕስ በአቶ አንተነህ መርዕድ የተፃፈው ”አገም ጠቀም” የሆነና ሚዛናዊነት የጎደለው መጣጥፍ ከመቸውም በበለጠ ስለከነከነኝ ነው።
Pro Mesfin
አቶ አንተነህ እንዳሉት አንደኛ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም አይደለም ለራሳቸው፣ ለሌላም የሚተርፍ አንደበት አላቸውና ራሳቸው መልስ ይስጡ በማለ፤ ሁለተኛ ትልልቅ አገራዊ ጉዳይ እያለ በዚህ ጠባብ ነገር መጠመድ ለማን ይበጃል በሚል ቢተውት የተመረጠ ነበር። ነገር ግን ያን በማለታቸው ልክ አለመሆናቸውን አምነውበት ለንባብ ያበቁት መጣጥፍ ለፕሮፌሰር መስፍን ለመወገን ሲሉ ብቻ የአማራውን ነገድ «አለ ወይስ የለም?» ማለት እንደማይረባ ጉዳይ ቆጥረውታል። ነገር ግን በተለይ በአሁኑ ሰዓት አማራ እንደሰባዊ ፍጡር ሳይቆጠር ደመከልብ ሆኖ አጥንቱን ከስክሶ ደሙን አፍስሶ ባቆማት አገር እንዳይኖር በሚደረግበት ወቅት ”እንቶ ፈንቶ” ሲሉ ማጣጣል ትልቅ ስህተት ይመስለኛል።
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ባቋቋሙት «የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብት ጉባኤ (ኢሰመጉ)»፣ እርሰዎ እንደሚሉትና የኢትዮጵያም ህዝብ ተረድቶት እንደነበረው በወያኔ አገዛዝ ለሚደርሰው ገፍና በደል አለኝታ ለመሆን አልነበረም። ይልቁንም ከፕሮፌሰር መስፍን ከአንደበታቸው እንደሰማነው ከሆነ ኢሰመጉን ያቋቋሙት ወያኔን ለመርዳት መሆኑን ሰለሰማን የርስዎ የመከራከሪያ ነጥብ ”ከባለቤት ያወቀ ቡዳ ነው” የሚሉት አይነት ይሆንብዎታል። አቶ አንተነህ በውነቱ እርሰዎን ቅር ማሰኘትም ሆነ ፕሮፌሰር መስፍንን የመዝለፍ ሀሰብ በ አይምሮየ የለም ግን ፕሮፌሰር መስፍን የሚነግሩንና የሚሰሩት ነገር ካልተጣጣመ ቃልን ከተግባር በማጣጣም የምናስታርቀው ምን ብንል ነው፧ ፍርዱን ለርስዎ እተዋለሁ።
የአማራን ጉዳይ በተመለከተ አቶ አንተነህ እንደተረዱት ፕሮፌሰር መስፍን የወያኔውን መሪ መለስ ዜናዊን «አማራ የለም» ብለው «ዘረኝነት እንዳይስፋፋ አደረጉ» የሚል አስተያየትዎ እደተጠበቀ ሆኖ፣ እኔ ደግሞ ከአንድ ታዋቂ ግለሰብ መወቀስ ይበልጥ የኢትዮጵያ አገራችንና በህዝቧ ላይ የወደቀው የመከራ ቀንበር እጅጉን ያመኛል። ከወያኔ ወደ ስልጣን መምጣት ትንሽ ቀደም ብሎ ጀምሮ ያደረጓቸውን ድርጊቶች ላስታውስዎ፦
ፕሮፌሰር መስፍን እኤአ 1991ዓ.ም ለንደን ላይ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በራሳቸው ፈቃድ ወክለው ከነወያኔና ከነኦነግ ጋር ተደራድረው ድጋፍ በመሆን አስገቡዋቸው።
የኢትዮጵያ ህዝብ «መጣብን» ብሎ የፈራውን የዘረኝነት አገዛዝ የተከበሩ ፕሮፌሰር መስፍን በግልፅ በአደባባይ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በተለይም አማራን እንደህዝብ ከሚጠላው የወያኔ መሪ ጋር በማነጋገራቸው ወያኔን እውቅና እንዲያገኝ አደረጉ።
ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ፣ የዘረኝነት አባዜ ይዟቸው ሳይሆን ተገደው፣ ለአማራ ህዝብ የተደገሰለት ድግስ አደገኛ መሆኑን ስለተረዱ ብቻ የኢትዮጵያን ህዝብ ያካተተ የአማራ ድርጅት (ተገደው በግድ በዘር መደራጀት ስለነበረባቸው ያለበለዚያ ግን እውቅና በወያኔ ስለተነፈጉ) ሲመሰርቱ አሁንም ፕሮፌሰር መስፍን በአማራ ላይ የሚፈፀመውን በደል ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው አማራ የሚባል ነገድ የለም በሚል ጎዳና ስለተሰለፉ ህዝቡ በተለይም አማራው በአንድ ልብ እንዳይቆም በደካማ ጎኑ ስለመጡበት ኢትዮጵያን እያለ ከተገንጣይና ካስገንጣይ ጉያ እንዳይወጣና ጠንክሮ እንዳይታገል እውቅናቸውን ተጠቅመው በሚያንፀባርቁት የተዛባ አስተሳሰብ ህዝብም አገራችንም ተጎድተዋል ።
የቅንጅት መሪዎች በፈጠሩት አለመግባባት የኢትዮጵያ ህዝብ ፕሮፌሰር መስፍን አስታራቂ ሀሳብ አምጠተው ቅራኔውን ይፈቱታል ተብለው ሲጠበቁ እሳቸው ለማንም የማይበጅ ምክር በመምከራቸው ህዝብ የሳቸውን ቃል ተከትሎ ቅንጅትን እንዳያንሰራራ አድርጎ አፈረሰ።
«አማራ የለም» ከማለት አልፈው «በአርባ ጉጉ የሞተው ኦሮሞ ነው» ማለታቸው ሟች በሌለበት ገዳይ አይኖርምና የአማራን ደም ደመከልብ እንዲሆን ትብብር አድርገዋል።
ለመሆኑ እኔ እንዲህ ብዬ እንደማስብና የዚህ አይነት ሀሳብ ያለን በሚሊዮን የምንቆጠር አማሮች መሆናችንን ቢረዱ ምን ይላሉ?
አቶ አንተነህ እርሰዎ እንዳሉት ፕሮፌሰር መስፍን «ትልቅ ሰው፣ አዋቂ፣ የተከበሩና የእድሜ ባለፀጋ» በሚለው ቃል እስማማለሁ። ነገር ግን «ደምመላሽ» የሚለው ቃል ሲወጣ አባባሉ ከቅንነት ይሆናል የሚል ግምት ቢኖረኝም የተጠና አልመሰለኝም። «ደምመላሽ» መሆኑ ቀርቶ የአማራ ህዝብ ተቆርቋሪ አለመሆናቸውን ደሙ ደመ ከልብ ሁኖ አንዲቀር የተወሰነበት «የለህምና አልሞትክም» የሚሉት አማራ ይመሰክራል።
አቶ አንተነህ ስለ አቶ ተክሌና ስለእርስዎ ግንኙነት ሲፅፉ ” ….ብዙ ህዝብ በሚርመሰመስበት የደመቀ በአል መሃል የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት መሪ የሆኑትን አቶ ተክሌ የሻውን አገኘኋቸው። ደስ ብሎኝ ራሴን ካስተዋወቅሁ በኋላ በወጋችን መሃል በቅርቡ ከወጣው መግለጫቸው አምስት ገጽ እውነት ውስጥ ጨዋነት የጎደለው ስድብ ተገቢ እንዳልነበር ነገርኳቸው። የሰማሁት መልስና ለፕሮፌሰሩ ያላቸው ጥላቻ አስደነገጠኝ። ለአማራው ህዝብ መብት ቆሜያለሁ ብለው አደባባይ የወጡ እኒህ ሰው አንዱን ታላቅ ወገናቸውን በሰብዕናቸው ገብተው ሲዘልፉ መመልከት ዓላማቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ሆኖ አገኘሁት። ስልሳዎቹ ውስጥ የሚሆኑ እኒህ አዛውንት ሌላው በእድሜ፣ በእውቀትና በተመክሮ ለሚበልጧቸው ክቡር ሰው የሚሰጠውን የጨዋ አማራ ባህል ከውስጣቸው አላየሁም። ስለሆነም ውይይቴን ብቀጥል የበለጠ ህሊና የሚያቆስል ነገር እንደምሰማ በመገመት ተሰናበትኋቸው። ” ሲሉ አስነብበውናል።
አቶ ተክሌን ሲያገኙ ደስ መሰኘዎትን በዚህ አንቀፅ ቢገልፁም ከላይ በአንቀፅ 4 ላይ ደግሞ ”…የብዙዎችን ላቆየውና በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ካንድ ወገን የሚሰነዘረው ከባህላችን ውጭ የሆነ ዓላማው ግልጽ ያልሆነ ስድ በሚያሰኝ የመንገድ አዳሪ ቋንቋ የስድብ ውርጅብኝ በኒህ አዛውንት አባት ላይ ሲወርድባቸው ዝም ብሎ መመልከቱ ለህሊና ይከብዳል…” ሲሉ ቁጭትዎንና ቁጣዎትን ገልፀው ስለነበር አቶ ተክሌን ሲያገኙ የተደሰቱት ለምን እንደሆነ ለመረዳት አዋቂ መጠየቅ አያስፈልግም።
እንደርስዎ አገላለፅ አቶ ተክሌ በጥላቻ የተሞሉና ስነምግባር የጎደላቸው እንደሆኑ ተርከዋል። ለነገሩ አቶ ተክሌ ራሳቸውን መከላከል ስለሚችሉ አስፈላጊ ሆኖ ከታያቸው መልስ የሚሰጡበት ጉዳይ ይሆናል። ነገር ግን እኔን ያልገባኝ ነገር አቶ ተክሌ ጋር ስትነጋገሩ የተናገሩት ቃል አፀያፊ ከሆነ ቃላቶቹን በፅሁፍዎ ላይ በማስፈር መግለጫውን በተቹበት መልክ ቢያካትቱት የአንባቢውን የግንዛቤ አድማስ ስለሚያሰፉት አንባቢው በራሱ ሚዛን መዝኖ ለፍርድ በበቃ ነበር።
በተረፈ« በጥላቻ የተሞሉና ስነምግባር የጎደላቸው ስለሆኑ ለአማራው ህዝብ መቆማቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ሆኖ አገኘሁት» የሚለው ”ሾላ በደፈና” አባባልዎ፥ «ሞረሽ ወገኔ አላስፈላጊ ድርጅት ነው። አማራ መደራጀት የለበትም» ከማለት ተለይቶ አይታይም። ስድብ ነውር ከሆነ ነውር መሆን ያለበት ከተሳዳቢው አንደበት ሲወጣ እንጅ ተቀባዩ ላይ የሚያደርሰው ጫና ወይም የተሰዳቢው ማንነት ሚዛን ውስጥ እየተቀመጠ አለመሆኑን መዘንጋትዎ አስገርሞኛል። እንዲህ ለማለት ያበቃኝ ደግሞ እርስዎ ”ክደትና መሳት” የሚለውን ቃል በማስረጃነት በማቅረብ ያስነበበውን የሞረሽን መግለጫ ስድብ ካሉ በኋላ በአቶ ተክሌና በሞረሽ ላይ ”ስድ በሚያሰኝ” ”የመንደር አዳሪ ቋንቋ” በማለት አቶ ተክሌን «ስድ» ከማለት አልፎ የሞረሽ ወገኔን አባላትና ደጋፊ ሁሉ «የስድ ስብስብ» እንደማለት የስድብ ውርጅብኝ ሲያዘንቡ ውነቱን ተናገርኩ እንጅ አልተሳደብኩም ሊሉ ይሆን?
ለነገሩ «የወደቀ ግንድ ምሳር ይበዛበታል» ነውና የሚሞተው የሚሳደደው የሚፈናቀለው አማራ እንደ ህዝብ ከ34 ሚሊዮን በላይ ሲሆን፣ ያ ህዝብ ለሚደርስበት በደል ተጠያቂ እንኳዋን እንዳይኖር «የለህም» እያሉ አደባባይ ወጥተው የሚሞግቱት ፕሮፌሰር መስፍን ሳይወቀሱ፣ «የለም ማለት ስህተት ነው በደል የሚደርስበት ወገን ከተካደ በደል ፈፃሚ ነፃ ይሆናል» ያለውን ወገን ለማዳከም ብዕር ማንሳት የሚያሳዝን ክስተት ነው። ለነገሩ እርሰዎ የኢትዮጵያ ጀግኖች ብለው በፅሁፍዎ የደረደሩዋቸው ሁሉም ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰለፉ ጀግኖች ናቸው ብየ ስለማላስብ የእርስዎም ሰልፍ ከወዴት እንደሆነ አልገባኝምና ልተወው።
ለማንኛውም እርስዎ ከፐሮፌሰር መስፍን በተለየ «አማራ» የሚባል ነገድ እንዳለና ያም ወገን የተለየ ግፍ እየተፈፀመበት እንደሆነ ውነቱን በመመስከርዎ አድናቆቴን ልቸርዎት እወዳለሁ። ምክንያቱም እርስዎ በፕሮፌሰር መስፍን ማንነትና ፍቅር ስለተሸነፉ፣ የሞረሽ ወገኔን መግለጫ በማጣጣልና «ፕሮፌሰርን በካሀዲነት ወነጀሉ» ብሎ የፕሮፌሰርን ስህተት ማደባበስ ብሎም ያላግባብ ደሙ የሚፈስ ወገን እንዳለ ማመን የተሳነውን ሰው «ደምመላሽ» በማለት ማሞካሸትዎ እንዳለ ሁኖ፣ «በፕሮፌሰር ተፃራሪ አማራ አለ፣ በደልም እየተፈፀመበት ነው፤» ብለው ሲቆሙ ሳይ ታዲያ ምነው የሚያከብሩዋቸውና የሚያደንቋቸው ፕሮፌሰር ሲሳሳቱ በክብር እንዲያስተካክሉ አልጠየቋቸውም ያሰኛል።
እንደእኔ ግንዛቤ ፕሮፌሰር መስፍን በየጊዜው ብዙ ጠቃሚም ጎጅም ፅሁፍ ለንባብ አብቅተዋል። ለዚህም የኢትዮጵያን ህዝብ «ሆዳም» ብለው መዝለፋቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። ለአማራውም «አለሁ» ሲል «የለህም»፣ «እየተገደልኩ ነው» ሲል «የት አለህና?» በማለት 23 አመት ሞግተውታልና ለመግለጫው መልስ የሚያስፈልግ ቢሆን እርስዎም እንደገለፁት እራሳቸው ፕሮፌሰር መልስ መስጠት ስለሚችሉ የእርስዎ ጥብቅና ” የምጣዱ እያለ የንቅቡ ተንጣጣ” እንድል ዳርጎኛል። ፕሮፌሰር መስፍን ነገዱን ሁሉ እየጠሩ እውቅና ሲሰጡ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ «አማራ የሚባል ነገድ የለም» ማለታቸው ግን እንቆቅልሽ ነው በማለት ሀሳቤን እቋጫለሁ።
ፀሀፊዋን agereamanu@yahoo.com ማግኘት ይቻላል።

ዝምታው ለምን ነው? (አንተነህ መርዕድ)

ዝምታው ለምን ነው?
ኢትዮጵያ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለችው።
  • መንግስት እንደድሮው መግዛት ተስኖታል
  • ህዝቡም እንደድሮው መገዛት ታክቶታል
  • የተቃዋሚው ቋንቋም እንደባቢሎኖች የተከፋፈለበት ወቅት ላይ ነን
  • ከዚያም ብሶ ሚድያው ታፍኗል።
ትግሉን በተደራጀ መልክ ዳር የሚያደርስ ጠርቶ ባልወጣበት ሁኔታ ህዝባዊ ዓመጽ ሊፈነዳ ጫፍ ላይ መድረሱን ለማወቅ ሊቅነት የሚጠይቅ አልሆነም። በዚህ ሁኔታ ዐመጽ ከተነሳም የሚከተለው ትርምስና እልቂት ቀላል ስላይደለ ንፁህ ህሊና ያለው ሁሉ በግልፅ ታይቶት መፍራት አለበት። ይህ ፍርሃት በጎ ፍርሃት ሊሆን የሚችለው ወደ መፍትሄው መሄድ ካስቻለን ነው።
በእንደዚህ ዓይነት ፈታኝ ወቅት ነፃ ሚድያ ግዙፍ ሚና አለው።
  • ህዝብ ተገቢ መረጃ እንዲኖረውና እርምጃው በእውቀት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን በማድረግ
  • በእንደዚህ ዓይነት ቀውጢ ወቅት ብቅ የሚሉ የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎች ህዝባዊ ትግሉን ወደ ተለየ አቅጣጫ እንዳይመሩትና ለሌላ ተስፋ አስቆራጭ ክስተት እንዳይዳርጉት በማጋለጥ (ይህ ለታሪካችን አዲስ አይደለም)
  • የህዝቡን የጋራ ብሶትና የጋራ ተስፋውን አጉልቶ በማውጣት ወደ ብሄራዊ መግባባት ለመድረስ መገናኛ ብዙሃን ከባድ ሃላፊነት አለባቸው።
ስለሆነም አምባገነን ስርዓቱ ሚድያውን ለማዳከም ያሰደደንና በሁሉም የዓለም ክፍል ተበትነንና ተደላድለን የምንኖር ሆንነ አሁንም በወከባው ውስጥ ያለነው ተረጋግተን የምንነጋገርበት ወቅት አሁን ነው። የሃሳብ ልዩነቶች ሊኖሩን ይችላሉ። እንዲያውም “የሃሳብ ልዩነቶች ለዘለዓለም ይኑሩ”የሚለውን መፈክር ልናነግበው የሚገባ ነው። ነገር ግን የሃሳብ ልዩነት መኖሩ የሃሳብ ግብይትን ያቆመው እለት የሃገር ውድቀት እሙን ነው። የሃሳብ ልዩነት የሃሳብን ግብይትና መቀራረብን ሊያቆመው አይገባም። (ኮሙኒኬት የማያደርጉ ኮሙኒኬተርስ) ከመሆን እንውጣ።
ሀገርን የማዳን ቃል ኪዳን በሁላችንም ዘንድ እንዳለ ይታወቃል። ችግሩ ማን ይጀምረውና እንዴት ይጀመር የሚለው ነው።
  • የታሰሩ ወንድሞቻችን የሚከፍሉትን መስዋዕትነት በፀጋ ቢቀበሉትም የቤተሰቦቻቸውን ጫና የማቃለል የሞራል ሃላፊነት አለብን።
  • በጎረቤት አገሮች በስደት የሚሰቃዩ የሙያ ባልደረቦቻችን ያሉበትን ሁኔታ ያለፍንበት ሁሉ እናውቀዋለን። በችግሮቻቸው መድረስ ይኖርብናል።
  • ከሁሉም በላይ ግን ማንም ሳያስገድደን ለራሳችን ቃልኪዳን የገባነው ህዝብን ተመጣጣኝ መረጃ የመስጠት ሥራ እዚህ ደርሶ አላበቃም። እንዲያውም ተፈላጊነቱ እየጎላ ነው።
“ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ” የሚለው የህዝብ መፈክር ለተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆን ለጋዜጠኞችም ጭምር ነው። በነጠላ እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ የማይናቅ ቢሆንም በጋራና በተቀናጀ እንደሚደረገው ፈጣንና አመርቂ ውጤት አያመጣም። አገሪቱ ያለችበት ፈታኝ ሁኔታ ፋታ የሚሰጥ ባለመሆኑ በተገኘው መንገድ ሁሉ ግንኙነቱ ይቀጥልና በህብረት ወደ አንድ አቅጣጫ እንንቀሳቀስ። ስለዚህም መነጋገር እንጀምር። “ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም” ነው ተረቱ። ህዝቡን እንዲረዳን የምንጠራው መጀመርያ ራሳችን ችግሩን አውቀን ስንንቀሳቀስ ነው። ለችግራችን እኛው መፍትሄ እንፈልግለትና በአገር ጉዳይም የማንናቅ የመፍትሄ አካል እንሁን። ዝምታው ለምን ነው?

ለሕዝብ የተላከን ምግብ ሊሸጡ ሲሉ የተያዙ የተባሉ 4 ባለስልጣናት ታሰሩ

አኩ ኢብን ከአፋር
ባለፈው ወር በአፋር ክልል በአሚባራ አካባቢ ህዝብ ላይ የደረሰው የጎረፍ አደጋን ተከትሎ ከ30ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች ከአካባቢው መፈናቀላቸው ይታወሳል። ለእነዚህ ወገኖች ከተለያዩ የእርዳታ ድርጅቶች እና ከመንግስት የተላከው እርዳታ በመንግስት ኃላፊዎች ለሙስና መዳረጉን ምንጮቻችን ከቦታው ዘግበዋል።
afar
ባለፈው ሰኞ ከአዋሽ ፋንቲ አሌ ወረዳ ወደ መትሃራ በመንግሥት ኃላፊዎች ተዘርፎ ሊሸጥ የነበረና ብዛቱ በውል ያልታወቀ ብዙ ኩንታሎች የእርዳታ እህል በመኪና ተጭኖ ሲንቀሳቀስ ከሌሊቱ 6:00 ላይ በህዝብ ተቆማ በቁጥጥር ስር ውሏል።
እነዚህ ባለስልጣናት ለጊዜው የታሰሩ ሲሆን ስማቸው ከዚህ በታች በዝርዝር ይቀመጣል፦
1 – አቶ አደም መሀመድ የአዋሽ ፋንቲዓሌ ወረዳ ምክትል አስተዳደር
2 – አቶ አባህ አባ የግብርና የገጠር ልማት ቢሮ ኃላፊ
3 – አቶ ሙስጣፋ ሀሳን የአዋሽ ወረዳ የአብዴፓ ፓርቲ ቢሮ ኃላፊ፤
4 – ወ/ሮ ፋጡማ እብራሂም የንብረት ክፍል ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ እነዚህ ባለስልጣናት በጊዜው ለፖሊስ በሰጡት ቃል «የተያዝነው ጊዜ ባለፈበት እህልና እቃ ሲሆን ለመንግስትም ለመመለስ እየተንቀሳቀስን በነበረበት ሰአት ነው» ብለዋል ሲሉ ምንጮች ፓሊስን ጠቅሰው ዘግበዋል።
ይህን የህዝብ እርዳታ እንዲሸጡ ያስገደዳቸው የአፋር ክልል አፈጉባኤ የሆኑት አቶ መሀመድ አንበጣ ወደ አዋሽ በመሄድ ለወረዳው ካቢኔዎች ገንዘብ አምጡ ብለው 20,000 ብር ቢሰጧቸውም ጨምሩ ሰላሏቸው የህዝብ እርዳታ እንዲሸጡ መገደዳቸው አንድ ስሙ ሊገለፅ ያልፈለገ ሊንደብቅለት የመንግስት ሰራተኛ የላክለን መረጃ ያስረዳል

“እስሬ፣ ጥሩ ክርስቲያን፣ ሰውና ታጋይ አድርጎኛል” – ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ከቃሊቲ እስር ቤት

‹‹እስሬ፣ ጥሩ ክርስቲያን፣ ሰውና ታጋይ አድርጎኛል››
‹‹ኢህአዴግ በጭቆና ውስጥ ጸጥ ብሎ የተቀመጠን ሕዝብ እየቆሰቆሰ ነው››
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ከቃሊቲ እስር ቤት
ከኤልያስ ገብሩ
ትናንት፣ በዕለተ ዓርብ እኔ እና የዕንቁ መጽሄት ማኔጂንግ ዳይሬክተር ከሆነው ፍቃዱ ማህተመወርቅ (ባሪያው) ጋር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና ፖለቲከኛን አቶ አንዷለም አራጌን በቃሊቲ ተገኝተን ጠይቀናቸው ነበር፡፡
Eskinder-Nega
ሁለቱም ፍጹም ሰላማዊነት፣ እርጋታ፣ ትህትናና ፈገግታ አብሯቸው ነበር፡፡ ያው ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ማናገር ስለማይቻል ተነጣጥለን ማውጋት ግዴታ ነበርና ጥቂት ከአንዷለም ጋር ከተጨዋወትን በኋላ ከእሴው ጋር አወጋን፡፡
እስክንድር የፊታችን ማክሰኞ፣ ሕዳር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ስለምቀርብበት የክስ ጉዳይ አንስቶ የሚሰማውን ነገረኝ፤ ጠንካራ ምክርም ለገሰኝ፡፡ የክሱ እንደምታንም ባላሰብኩት መንገድ አስረዳኝ፡፡ (ይህ ግላዊ ምክር ስለሆነ ልለፈው)
እስክንድርን ከታሰረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ጠይቄዋለሁ፡፡ ስለራሱ መናገር አይፈልግም፡፡ ግን ትናንት ባተለመደ መልኩ ስለራሱ ልቡን ከፍቶ አወጋኝ፡፡ በተለይ ስለፈጠሪው! ሃሳቡን እንዲህ አስቀመጥኩት፡፡
‹‹ኤልያስ፣ እስር ለእንደእኔ አይነት፣ ቤተሰብ ለመሰረተ እና ልጅ ለወለደ ሰው ትንሽ ሊከብድ ይችላል፡፡ ስለባለቤትህ እና ልጅህ ሁሌ ታስባለህ፤ ኃላፊነት አለብህና! ነገር ግን፣ በሌላ መልኩ፣ በመታሰሬ ሎተሪ እንደወጣልኝ አድርጌ እቆጥረዋለሁ፡፡ እስሬ፣ ጥሩ ክርስቲያን፣ ሰውና ታጋይ አድርጎኛል፡፡ አሁን በጣም ሰላም ይሰማኛል፡፡ ክርስቶስን በጣም እንዳውቀው አድርጎኛል፡፡ ፍቅሩ ምን ያህል እንደሆነም ገብቶኛል፡፡ ይህን በመረዳቴ በጣም እድለኛ ነኝ፡፡ መታሰሬ መጽሐፍ ቅዱስን በደንብ እንዳነብ አስችሎኛል፡፡ ባልታሰር ኖሮ እንዲህ የምሆን አይመስለኝም፡፡ ለሌሎች ነገሮች ቅድሚያ እሰጥ ነበር፡፡ ግን ቀዳሚው መሆን ያለበት አምላክህን ማወቅ ነው፡፡ ነገ፣ ይበልጥ የተሻልኩ ሰው እሆናለሁ፡፡ …››
እስክንድር ከላይ ከጠቀስኩላችሁ ሀሳብ አስከትሎ በአሁን ወቅት በሀገሪቷ ላይ ስላለው ጭቆና በጠባቂ ፖሊሶች ፊት ሲናገር ያ ፍጹም የተለመደ ድፍረቱ እና ትህትናው አብሮት ነበር፡፡ እንዲህም አለ፡-
‹‹የስደት፣ የእስርና የክስ መብዛት ሥርዓቱ ያለበትን ከባድ ችግር በግልጽ ያሳያል፡፡ ኢህአዴግ በጭቆና ውስጥ ጸጥ ብሎ የተቀመጠን ሕዝብ እየቆሰቆሰ ነው፡፡ (ከዚህ ጋር በተያያዘ አፈታሪክ ነው ብሎ አንድ ሀገራዊ ምሳሌ ነገረኝ) ይህ ነገ በራሱ ላይ መዘዝ ያመጣበታል፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፣ ሥርዓቱ እንዲህ በማድረጉ (የስደት፣ የእስርና የክስ መብዛት) ነገ ኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲፈጠር ሳይፈልግ እና ባለማወቅ አበርክቶት እያደረገ ነው፡፡ አለመረጋጋት ይህን ይፈጥራል፡፡ …››
እስክንድር ውስጠ ወይራ ንግግር ተናግሯል፤ ልብ ያለው ልብ ይበል!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ወያኔ/ኢሕአድግ እና ምርጫ 2007

በያዝነው 2007 ዓ.ም በግንቦት ወር ለሚካሄደው አገራዊ ምርጫ በገዢው ፓርቲ እንዲሁም በተቃዋሚ ፓርቲዎች ቅድመ ዝግጅቶች እየተደረጉ ሲሆን ምርጫ ቦርድም ምርጫውን በበላይነት ለመምራት ቁሳዊና ቴክኒካል ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑን ከገዢው ፓርቲ ልሳን ከሆነው EBC በተደጋጋሚ እየተሰማ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል መከፋፈሎች እንዲሁም አለመረጋጋቶች እየተስተዋሉ ሲሆን ለዚህም ምክንያቶቹን በእርግጠኝነት መግለጽ አዳጋች ቢሆንም ካለፉት የምርጫ ተሞክሮዎች በመነሳት የገዢው ፓርቲ ረጃጅም እጆች እንዳለበት መተንበይ አዳጋች አይሆንም፡፡
በዚህ በያዝነው አመት የሚካሄደውን አገራዊ ምርጫን ለመተንበይ በቅድሚያ ከዚህ ቀደም የተካሄዱትን አገራዊ ምርጫዎች በወፍ በረር ቅኝት ማየቱ የግምቱን ይዘት ጠንካራ ያደርገዋል፡፡ በዚህ ጽሁፍ አዘጋጅ እምነት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያቶች ከሚወጡ ጥናታዊ ጽሁፎች ለመረዳት እንደሚቻለው በአገራችን ተስፋ ሰጪ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ተካሂዷል ተብሎ የሚታሰበው በ1997ዓ.ም በተካሄደው አገራዊ ምርጫ ነው፡፡ ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩትም በዋነኛነት ገዢው ፓርቲ በወቅቱ ለነበሩት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የነበረው ዝቅተኛ አመለካከት (በወቅቱ ቅንጅት የምርጫው ምዝገባ ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜያት በቀሩበት ወቅት ቅንጅት መፍጠሩን ልብ ይለዋል) እንዲሁም የምዕራባዊያኑን ቀልብ በመሳብ አገሪቷ ለዴሞክራሲያዊ ግንባታ እየተጋች መሆኗን ለማሳየትና ከፍተኛ ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞም በወቅቱ በመንግስት ይዞታ ስር የነበሩትን የንግድ ተቋማት ወደ ግል ይዞታነት በማዞር (privatization) መንግስት ቀደም ሲል ይተችበት የነበረውን ሶሻሊስምን ወደ ጎን በመተው ዘመኑን መምሰሉን በማሳየት ምዕራባዊያንን ለማሳመን የሚተጋበት ወቅት ስለነበረም ጭምር ነው፡፡ ስለሆነም ያለፉትን የምርጫ ሂደቶችን ለመገምገም ምርጫ 97 እንደመነሻ (base year) በመውሰድ ገዢው ፓርቲ እንዲሁም ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው ላይ የነበራቸውን ሚና በሚከተለው መልኩ ለመዳሰስ ወደድኩኝ፡
ምርጫ 97
ኢሕአድግ 1997ቱ ምርጫ ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ለተቃዋሚዎች በነበረው ዝቅተኛ ግምት ፤ ምርጫውን በበላይነት አሸንፋለው ከሚል የተሳሳተ ግምት እንዲሁም የምዕራባዊያኑን ቀልብ ለመግዛት የዲሞክራሲ በሩን ገርበብ አድርጎ በመክፈቱና ለምርጫው ቅስቀሳ ከዛ በፊት ይሰጡ ከነበሩት የመከራከሪያ ሰዓት በአንጻራዊነት ሰፊ ጊዜ ለተቃዋሚዮች በመስጠቱ ህዝቡ የሁሉንም ፓርቲዎች ፕሮግራም የሚሰማበት እድል ፈጥሯል፡፡ በወቅቱ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አንጻር ኢሕአድግ በፖለቲካ ልምድ እንዲሁም በህብረተሰቡ ተሰሚም ታዋቂም ስለነበር ገዚው ፓርቲ ምርጫውን በበላይነት ለማጠናቀቅ ሙሉ ዕምነት ነበረው ሆኖም ግን ወደ ምርጫው ቅስቀሳ ሲገባ እየታየ የመጣው ፈጽሞ ያልተጠበቀና ገዚው ፓርቲ የከፈተውን የዶሞክራሲ በር ለመዝጋት አስቸጋሪ የነበረበት እንዲሁም ወደ ኋላ ማፈግፈግ የማይችልበት ወቅት ነበር፡፡
በተቃዋሚዎች በኩል በወቅቱ የምሁሮች ስብስብ ተብሎ ሲሞካሽ የነበረው ቅንጅት የገዢው ፓርቲ ጠንካራ ተፎካካሪ ነበር ለዚህም ምክንያቶቹ በርካታ ቢሆኑም ድርጅቱ በውስጡ ጉምቱ የፖለቲካ አዋቂዎችን ማካተቱ ፤ ድርጅቱ በመረጃ የተደገፈ ጠንካራ ክርክር ማካሄዱ፤በምርጫ  ክርክሮች ወቅት ሚያቀርባቸው ተከራካሪዎች ኢሕአዴግ ከሚያቀርባቸው የተሻሉ መሆናቸው፤ የማህበረሰቡን የልብ ትርታን መሰረት ያደረጉ ጠንካራ ትችቶችን  በገዢው ፓርቲ ላይ በማቅረባቸው (የዘር ፓለቲካን  ፊትለፊት  በመተቸታቸው ፤ ሙስናን በመረጃ አስደግፈው በማጋለጣቸው፤ በገዢው ፓርቲ  የተንቋሸሸውን  ስራ አጥ ወጣቱን ስራ ፈጣሪ ለማድረግ ንድፈ ሃሳብ ማቅረቡ ከብዙ በጥቂቱ ሚጠቀሱ ናቸው) ፤ ዘርን መሰረት ያላደረገ  የፖለቲካ አቅጣጫ (political ideology) ይዞ መቅረቡ ፤ ድርጅቱ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶችን ያቀናጀ መሆኑና ሌሎች ምክንያቶች ተደማምረው የምርጫውን ግምት አፋልሰውታል፡፡
ኢሕአዴግን ለውድቀት የዳረጉ ውስጣዊ ምክንያቶች
ከላይ በጠቅላላው ለማሳየት እንደተሞከረው የምርጫ 97 ለተቃዋሚዎች የፈጠረውን እድልና ገዢው ፓርቲ ላይ ያስከተለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ሲሆን ከዚህ በታች የምንመለከተው በድርጅቱ ውስጥ የነበረውን ውስጣዊ ችግሮችን ይሆናል፡
1.ከመጠን ያለፈ በራስ መተማመን
ኢሕአዴግ ከ1997 በፊት በነበሩት ምርጫዎች ተቀናቃኝ የነበሩትን በቀጥታ እንዲሁም በተዘዋዋሪ ካዳከማቸው ከፊሎችንም ከበታተነ በኋላ አስጊ የፖለቲካ ተቃዋሚ ስላልነበረ በምርጫ 97 ፍጹም የበላይነትን ለመቀናጀት እምነት ነበረው ለዚህም ማሳይው ከሌሎች የምርጫ ጊዜያቶች በተለየ ሁኔታ ለተቃዋሚዎች ሰፊ የአየር ሽፋን መስጠቱ ፤ የተለያዩ በርካታ የመከራከሪያ መድረኮችን ማዘጋጀቱ ፤ ክርክሮቹ ቀጥታ የአየር ሽፋን ማግኘታቸው ሲሆኑ ባልተጠበቀ መልኩ ጠንካራ ሆኖ የቀረበው ቅንጅት እንዲሁም ሌሎች ተቃዋሚዎች እድሉን በሚገባ ስለመጠቀማቸው በወቅቱ የነበረው የምርጫ ውጤት አመላካች ነው፡፡
2.ጠንካራ ተከራካሪ ያለማዘጋጀት
በተለያዩ የክርክር መድረኮች ኢሕዴግን ወክለው የሚቀርቡ ተከራካሪዎች ከተቃዋሚዎች ተሸለው ባለመገኘታችው እንዲሁም የሚያቀርቧቸው መከራከሪያዎች በመረጃ የተደገፉ አለመሆናቸውና  በተደጋጋሚ በተለያዩ የመንግስት ሚዲያዎች ሲሰሙ የቆዩ በመሆናቸው አሰልቺ ነበሩ፡፡ በወቅቱ በተቃዋሚዎች የሚቀርቡትን ፈታኝ ጥያቄዎች በበቂ ሁኔታ የሚመልስ ባለመኖሩ ኢሕአዴግ እየኮሰሰ ሌላው እየገነነ የመጣበት ሁኔታ እንደነበር የሁላችንም የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፤፤
3.የአባላት ታማኝ አለመሆን
የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያመለክተው ኢሕዴግ በ1997 ምርጫ ወቅት ጠቅላላ ከ6 ሚሊዬን በላይ አባላት የነበሩት ሲሆን ይህንን አባላት በማሰብ ገዢው ፓርቲ በቀላሉ እንደሚያሸንፍ መገመቱ ስህተት ላይመስል ይችል ይሆናል ነገር ግን ከምርጫው ማግስት ለመረዳት እንደተቻለው አብዛኛው አባላት የድርጅቱን የፖለቲካ ፕሮግራምን በመረዳት ሳይሆን የስራ ዕድል ለማግኘትና የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን በመፈለግ ፓርቲውን መቀላቀላቸው ነው፡፡ በአዲስ አበባ ድርጅቱ ድምጽ አገኝባቸዋለው ብሎ ባሰበባቸው በተክለሃይማኖት ፤ ቦሌ እና ሌሎች አካባቢዎች መሸነፉ አንዱ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡
4.ሙስና
ኢሕአዴግ በዋነኛነት ከሚታወቅባቸው እኩይ ባህሪያቶቹ አንዱ ሙስና ሲሆን ይህም የሚከናወነው ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ሳይሆን በተወሰኑ ቡድኖች ፤ ነባር ታጋዮች እንዲሁም ዘርን መአከል ያደረገ ስለነበር ሌሎች አጋር ድርጅቶች ውስጥ ውስጡን መከፋታቸው የነበረ ሲሆን ይህም መከፋት አባላቱ ሌሎች አማራጫ ፓርቲዎችን  እንዲመለከቱ ወይም ድርጅቱ ላይ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ ከማነሳሳቱም በላይ ድርጅቱን የግላቸው አድርጎ ለማሰብ አዳጋች ነበር፡፡
ምርጫ 2002:- በዚህ ምርጫ ላይ ኢሕአዴግ ከ1997ቱ ምርጫ ብዙ የተማረበት እና በቂ ዝግጅት ያደረገበት ስለነበር ውጤቱን ለመቀልበት ችሎ ነበር፡፡ በዚህ ምርጫ ወቅት ድርጅቱ በአብዛኛ የፖለቲካ ተንታኞች ሲገለጽ እንደነበረው ብቻውን ሮጦ ብቻውን ያሸነፈበት ምርጫ ነበር፡፡ ለዚህም ምክንያቶቹ፡-
  • በምርጫ 97 ላይ ጠንካራ የነበረውን ቅንጅትን አከርካሪውን በመስበር የበላይ አመራሮቹን በማሰር እንዲሁም ከሀገር እንዲሰደዱ በማድረግ ፤ ህዝቡን ይቅርታ እንዲጠይቁ በማስገደድ በህዝቡ ውስጥ እምነት እንዳይኖራቸው በማድረግና በሌሎችም እኩይ የፖለቲካ ስራዎቹ ድርጅቱን በማዳከሙ /በማፈራረሱ
  • በራሱ በኢሕአዴግ የተፈጠሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በመፍጠር እንዲሁም ሌሎች ተቃዋሚዎች በኢሕአዴግ ሴራ እንዲሁም በግላቸው ምክንያት ከምርጫ እራሳቸውን ማግለላቸው
  • አጭር የክርክር መድረኮችን በማዛጋጀት እንዲሁም ለተቃዋሚዎች አጭር ጊዜ በመስጠት በተቃራኒው ለራሱ ሰፊ የአየር ሽፋን በመስጠት የድርጅቱን ፕሮግራሞች ማስተዋወቁ
  • በ1997 በቅንጅትና በሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይቀርቡ የነበሩ አማራጭ የልማት እስትራተጂዎችን በመውሰድና ከፊሎችንም በመተግበር ከተሰራው ስራ በላይ ፕሮፖጋንዳ በመስራት (ጥቃቅንና አነስተኛ ፤ ማህበራትን ማደራጀት ፤ ወጣቱን አደገኛ ቦዘኔ ከማለት ወደ ወጣት የልማት ሀይል መቀየር ፤ የጋራ የመኖሪያ ቤቶችን መገንባትና የመሳሰሉት ከምርጫ 1997 በፊት በገዢው ፓርቲ ተሰምተው የማይታወቁ ሲሆን ከምርጫ 97 በኋላ ጽንሰ ሀሳቡ ከተቃዋሚዎች ስለመሰረቁ ማሳይዎች ናቸው)
  • ቀደም ሲል ገጠርን ማዕከል ያደረገውን ልማት ወደ ከተማ በማምጣት የሚታዩ ለውጦችን በማቅረብ እነሱንም በመንግስት ሚዲያዎች አግንኖ ማቅረቡ (መንገድ ፤ ውሃ ፤ ኤሌክትሪክ ወዘተ)
  • የህዝቡ ተስፋ መቁረጥ፡ – በምርጫ 97 ወቅት በህዝቡ ተስፋ የተጣለባቸው ፓርቲዎች ከነአካቴው መጥፋታቸውና እነሱን ሊተካ የሚችል ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲ መጥፋቱ
  • ጠንካራ የፖለቲካ ቅስቀሳ መደረጉ ፡ – መንግስት የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት የተሰሩ የልማት ስራዎችን በማቅረብ ፤ ህብረተሰቡን በማወያየት እንዲሁም ትልልቅ ካፒታል የሚጠይቁ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋቱና የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን በማቅረቡ
  • ምርጫ ቦርድ ላይ ያለውን ስውር እጅ በማስፋፋት ጠንካራ ክትትል ማድረግና የድርጅቱ የቀኝ ክንፍ መሆኑ በዚህና በሌሎች ምክንያቶች ገዢው ፓርቲ ሙሉ ለሙሉ የምርጫው አሸናፊ ሊሆን ችሏል፡፡ ከሁለቱ ተከታታይ ምርጫዎች የምንማራቸው አበይት ጉዳዮች ቢኖሩ፡
  • ኢህአዴግ በቢሊዮን የሚቆጠር የፋይናንስ አቅም እንዳለውና ለፖለቲካ ቅስቀሳ በቂ አቅም እንዳለው በተቃራኒው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያላቸው የፋይናንስ አቅም እጅግ አናሳ በመሆኑ በራካታ አባላትን ለማፍራት እንዲሁም ቅስቀሳዎችን ለማድረግ የአቅም ውሱንነት እንዳላቸው
  • ኢሕአዴግ የ1997ቱ ምርጫ ብዙ ልምዶችን የቀሰመበትና በወቅቱ አሳይቶት የነበረው የዲሞክራሲ ጭላንጭል በማጥፋት ፍፁም አምባገነን እየሆነ መምጣቱን
  • ኢሕአዴግ የተቃዋሚዎችን ደካማ ጎን በመጠቀም እንዲሁም የስለላ መረቦቹን በመጠቀም ተቃዋሚዎችን የማዳከምና የማፈረካከስ ልምዱን ያካበተ መሆኑን እና ፓርቲዎች ለምርጫ ከመድረሳቸው አስቀድሞ ከምርጫው እራሳቸውን እንዲያገሉ ጫና ማሳደሩን
  • የምርጫ ቦርድ መመሪያዎችንና ደንቦችን ኢሕአዴግ በፈለገው መልኩ ማሻሻሉንና ህጉ ለሁሉም በእኩል ደረጃ ተጠቃሚ የማያደርግ መሆኑንና እና ሌሎች በርካታ ጉዳዮች ናቸው፡፡እነዚህን እንደ መነሻነት በመጠቀም በምርጫ 2007 ሊገጥሙ የሚችሉትን ከወዲሁ ለመገመት ያህል፡ -
ኢሕአዴግ
በገዢው ፓርቲ በኩል ለምርጫው እየተደረጉ ያሉ ቅድመ ዝግጅቶች ከዚህ ቀደም ሲደረጉ ከነበሩት በእጅጉ የላቁ ናቸው፡፡ ይህም ነፃ የግል ፕሬሶችን ያለምንም በቂ ማስረጃ  በማሰር ፤ በመክሰስ ፤ በማስፈራራት ፤ እንዲሁም አገር ለቀው እንዲሰደዱ በማድረግ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውን  የሚያስተዋውቁበትን  መንገድ መዝጋቱ፡፡ ከዚህም  በተጨማሪ  ህዝቡ አማራጭ የመረጃ ምንጮች እንዳይኖሩት በማድረግ ህዝቡ በሚያገኘው አንድ አገራዊ የቴሌቪዝን ጣቢያ የገዢውን ልማታዊ ስራዎች ብቻ እንዲያይ ማድረጉ ነው፡፡
የተለያዩ የማህበረሰብ ድህረ ገፆች ላይ ፤ የደህንነት ሀይሎችን በማሰማራት እና ድንገተኛ ፍተሸዎችን በማድረግ ህዝቡን በማሸማቀቅ ፤ ሀይማኖትን ከሀይማት በማጋጨት ፤ የዘር ግጭቶችን በማቀነባበር ፤ ህዝቡ ላይ ሽብር በመንዛት ህዝቡ ከኢሕአዴግ ውጭ አማራጭ እንዳያስብ በማድረግ ህዝቡ እንዲመርጠው ብሎም ደግሞ የደህንነቱን ጡንቻ በማሳየት ለማስፈራራት በመሞከር ላይ ነው ለዚህም ማሳይው የተለያዩ የፖለተካ ስደተኞችን እና እንዲሁም በተለያዩ አገራት ይኖሩ የነበሩ የተቃዋሚ ድርጅት ቁልፍ ሰዎችን  አፍኖ በማምጣት ህዝቡ ላይ ፍራቻን ሲዘራ ይስተዋላል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ እንደ ምርጫ 2002 ሁሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን  በመከፋፈል ፤ በመታተን እንዲሁም በተለይዩ ምክንያቶች አመራሮቻቸውን በማሰር ተሳትፏቸውን ማዳከምን ተያይዞታል እንደ ማሳይም በአንድነት ለዲሞክራሲና ለልማት ፤ በአረና ፓርቲ እንዲሁም በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እያደረሰ ያለው የማፈራረስ ፤ የማሸማቀቅ እንዲሁም እስራቶችን ማየት በቂ ማስረጃ ነው፡፡
የፖለቲካ ቅስቀሳዎችን በተመለከተም በአሁኑ ወቅት በሲቪል ሰርቫንቱ እና በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሁም በነዋሪው ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ስልጠናዎችን እያካሄደ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ  ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰብሰቢያ አዳራሾችን የመከራይት አቅም ማሳጣት  አቅም ያላቸውንም  ደግሞ የአዳራሽ፣ ቢሮ፣እንዲሁም  ኪራይ ቤቶች እንዳያገኙ ተጽዕኖ በመፍጠር  ላይ ነው፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎች
በያዝነው ዓመት ማገባደጃ ላይ ለሚከናወነው አገራዊ ምርጫ ተቃሚ ፓርቲዎች እያደረጉ ያለው ቅድመ ዝግጅት በገዢው ፓርቲ ጥብቅ ክትትል ስር ሲሆን ፓርቲዎቹ የሚደርስባቸውን ጫና ለመቋቋም እንዲሁም ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን እንዲያስችላቸው ውህደት ለመፈፀም በሂደት ላይ ሲሆኑ በገዢው ፓርቲ ስውር እጆች ምክንያት በሚፈለገው ፍጥነት እየተጓዘ እንዳልሆነ እያየን ነው፡፡ በዚህ ምርጫ በሃገር ውስጥ ትልቅ  ግምት ከሚሰጣቸው እንደ አንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ  በገዢው ፓርቲ ተደጋጋሚ ትንኮሳ እየደረሰባቸው ሲሆን ይህም የምርጫው ዋዜማ ላይ ሊበረታ እንደሚችል ይገመታል፡፡
ህብረተሰቡ
ካለፉት የምርጫ ጊዜያቶች በተለየ ሁኔታ ማሕበረሰቡ የፓለቲካ አድማሱ የሰፋበት ሆኔታ ሲሆን ለዚህም አበይት ምክንያቶቹ በማሕበራዊ ድህረ ገፆች የሚለቀቁ የተለያዩ አክቲቪስቶችን  ንግግር ፤ ክርክሮች ፤ በግል ፕሬሱ ይታተሙ የነበሩ የፖለቲካ ትንታኔዎች ፤ ከገዢው ፓርቲ እየሾለኩ የሚወጡ የተለያዩ መረጃዎች እንዲሁም ህብረተሰቡ አማራጭ የመረጃ ምንጭ በማግኘቱ ነው፡፡ በመሆኑም ማሕበረሰቡ ምርጫው በገዢው ፓርቲ የተለመደ ማጨበርበሮች ሊጠናቀቅ እንደሚችል ግምቱ ቢኖረውም እንደ ባለፉት የምርጫ ጊዜያቶች በቸልታ ያልፈዋል ተብሎ አይታሰብም ምክንያቱም ህዝቡ መንግስት የሚያደርገውን የመብት ረገጣ ፤ አድሎአዊ አገዛዝ ፤ ሙስና ፤ እንዲሁም በእስልምና ሀይማኖት እና በኦርቶዶክስ የዕምነት ተከታዮች ላይ እጁን በማስገባት እየፈፀመ ያለውን በደል በሚገባ ስለሚያውቅ ድርጅቱ ጉልበት ያለው ቢመስልም ውስጡ ግን ባዶ ፤ ደጋፊ ያለው ቢመስልም አባላቱ በጥቅም ፤ በዘር እንዲሁም በመልካም አስተዳደር እጦት ያኮረፉ የሚበዙበት ሲሆን ገዚው ፓርቲ ከሕወሓት ውጨ ያሉ ፓርቲዎችን በአይነ ቁራኛ መመልከቱና አብዛኛውን ስልጣን ጠቅልሎ መያዙ በአጋር ድርጅቶች ጥርስ ውስጥ እንዲገባ ምክንያት ሆነዋል፡፡
ማጠቃለያ
የምርጫውን ውጤት ከወዲሁ መተንበይ ባይቻልም በገዢው ፓርቲ ውስጥ ያሉ አባላት   በወያኔ ሕወሓት ላይ በተለይዩ ምክንያቶች ውስጣቸው የሻከረ በመሆኑ (ብአዴን በግንቦት 7 ፤ ኦሕዴድ በወጣት ተተኪዎቹ የስልጣን ይገባናል ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ፤ እንዲሁም በሌሎች አጋር ፓርቲዎች) የምርጫውን ውጤት ወዳልተገመተ አቅጣጫ ሊመሩት እንደሚችል ይገመታል፡፡ የማሕበረሰቡ ንቃተ ህሊና መጨመር ፤ ገዢውን ፓርቲ በተጨባጭ መረጃዎች መወንጀል መጀመሩ ፤ መንግስት በተደጋጋሚ የሚፈፅማቸው የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ፤ የአገሪቱን ከፍተኛ ቁጥር የሚሸፍኑትን አንጋፋ የሀይማኖት ተቋማትን ማስኮረፉ ከሀይማኖቱ ተከታዮች የምርጫ ካርድ ሊነፈግ እንደሚችልም  ይገመታል ይሁንና ገዢው ፓርቲ በምርጫ ቢሸነፍም ስልጣኑን ለመልቀቅ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ድምፁ የተሰረቀበት ማሕበረሰብ አልመረጥኩም ብሎ በጥያቄ  ተቃውሞ ቢነሳ  ተቃውሞውን በበቂ ሁኔታ የሚያስተባብርና ሀላፊነቱን የሚወስድ ፓርቲ ባለመኖሩ አገሪቷን ወደ አላስፈላጊ ዕልቂት እንዳይጥላት ያሰጋል፡፡ ገዢው የወያኔፓርቲ የምርጫውን ውጤት በጸጋ ተቀብሎ ለመጪዋ ኢትዮጵያ ዘላለማዊነት በቅን ልቦና ምርጫውን ለግል ጥቅም ሳይሆን የህዝቡን ድምፅ እንዲያከብር ልባዊ  ምኞቴ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!