Thursday, March 31, 2016

የጋራ ፊልሚያ በዘረኛው ወያኔ ላይ! (ታደለ መኩሪያ


ታደለ መኩሪያ
ወያኔ    የአጋዚን ጦር ፣ የስለላ መረቡን፣ በሕብረተሰቡ የተጠሉ ግለሰቦችን ፣  የዘር ወርዴ  ሰለባዎችን፣ የገንዘብና የሥልጣን ጥመኞችን ይዞ ለሃያ አምሰት ዓመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ሲ ፏሏል ቆይቷል፤ በጋራ ፊሊሚያ በቃህ ሊባል ይገባዋል። የሀገራችን ክፍለ ሃገር የሆነችው  የትግራይን  ሕዝብ ስም ይዞ  በወቅቱ ደርግ  በሕዝብ ላይ ከሚያደርሰው በደል  ለመላቀቅ መቀሳቀሱ የታወቀ ነበር፤ ይሁን  እንጂ ሀገርን ለመበታተን የቆመ መሆኑ ቢታወቅ  በምንም ዓይነት  የተከዜን ወንዝ  አይሻገርም ነበር፤ እንደማይሻገሯት የወያኔ መሪዎች  ጠንቅቀው ያውቁታል። ዛሬ እንደጌኛ ሊጭኑት የተነሱት  የወልቃይት ጠገዴ፣የከፍታ ሑመራ፣ የጥልመት ሕዝብ  ባለውለታቸው ነበር፤ባጎረስኩ  እጄን ተነከስኩ ሆኖበት ፤ ዛሬ  ንብረቱን ተቀምቶ፤ እርሱነቱ ተገፎ፤  በስውር በጥይት እየተቆላ ነው፤  ልጆቹ  ከትምህርት ቤት ይልቅ  በእስር ቤቶች ታጉረው ይገኛሉ።
ወደ መሐል ሀገር ሰንመጣ፡ በየፈርጁ  ወያኔዎች   የሚያሳዩን  ትዕይንቶች እንደተመልካቹ  ይለያያሉ፤ ሆኖም ግን  ግባቸው አንድ ነው፤ ሕዝብ በጋራ  ሰለሀገሩ እንዳይመክር ማድረግ ነው።  የሚከተለውን ሃይማኖት፣  የመጣበትን የሕብረተሰብ ክፍል፣  በመጠቀም  ሕዝቡን  ለመከፋፈል  አጥብቆ ሠርተዋል፤
ከአራት ዓመት በፊት ጀምሩ ‘ድምፃችን ይሰማ’ በማለታቸው በ እስር የሚማቅቁት  የእስልምና ተከታይ ወገኖቻችን  ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ በጽናት በቆራጥነት ቆሙ እንጂ ሕልውናቸውን አሳልፈው አልሰጡም።  በእኛ ላይ እየተፈጸመ ያለው፣ ‘ቤሔራዊ በደል ነው’ በማለት የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የፍትህ እጦት ሰለባ መሆኑን በዚህ አገላለፃቸው ግለጽ አድርገውታል፤
እውነትን  ለሕዝብ በማቅረባቸው የታሰሩ ጋዜጠኞች፣ ለሰበዐዊ መብት የቆሙ፣ ግለሰቦች፣ በሰላም  ለውጥ ጠያቂዎች ሁሉ  ጭህታቸው አንድ ነው። እንደሙሰሊም ወንድሞቻችን የፍትህ ነው፤ የፍትህ ጥያቄው የእስር ቤት ብቻ ሣይሆን የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ ሆኗል።
ዛሬ በኦሮመኛ ተናጋሪው ሕዝባችን  የተነሣው የ መሬት አንቀጥቅት አመጽ የወያኔን መሪዎች የተነፈሰ ጎማ አስመስሏቸዋል። የኦሮሞ እናቶች ባዶ እጃቸውን   ሞትን ሳይፈሩ በቆራጥነት ታንክና መትረየሰ ካሰለፈው፤ ቦንብና ክላሽ ከታጠቀው፣ የአጋዚ ጦር ፊት ለፊት ተጋፍ ጠው፣ ታሪክ ሠርተዋል። የኦሮሞን ሕዝብ በአድር ባዩ  ኦፒዲዎ መነጽር ይመለከቱት የነበሩት፤ የወያኔ መሪዎች የውርደት ማቃቸውን ለብሰዋል፤ ‘ልክ እናገባችሃለን’ ባዩ  አባይ ፀሐዬ ድንፋታው  ባዶና  ግልብ የቁራ ጭሆት ሆኖ ቀርቷል።
ወያኔ  በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ ሕዝብ ላይ  አጋዚ ጦሩን አሰልፎ   የዘር ማጥፋቱን  ተልኮውን  ቢያጧጥፍም  ሕዝብ አልተበረከከም። ለፍትህ ለነፃነት ለዲሞክራሲ ለአንድነት ፊሊሚያው ከወያኔ ጋር በተባበረ ሃይሉ ቀጥሏል።
የቤገምድር ባጠቃላይ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በተናጥል፣ ከወገኔ ከትግራይ ሕዝብ ጋር አታጣሉኝን ብሎ የወያኔ መሪዎችን ቢማጠን  ጆሮ ዳባ ልበስ አሉ፣  ልመናው እንደፍረሃት ተቆጠረበት፣ ሃያ አምስት ዓመት  ዘንባባ አንጥፎ መለመኑ እንደጅል አስቆጠረው፣  በደሉና ወርደቱ  ሳይበቃው ርዕስቱን ተቀምቶ  ‘ማደሪያ  እንደጣች  ወፍ ‘ተከራተተ፣አሁን  ግን  ወርደት በቃኝ  ብሎ እራሱን  ከወያኔዎች ጥቃት ለመከላከል ‘ጓንዴ  አነሣ!  ጥያቄው የፍትህ ጥያቄ ነው።
ወያኔዎች ሀገር ለማሰተዳደር   ሕዝብን  በጎሣ  አለያይቶ በክልል ከልሎ የቀኝ ገዥዎችን መንገድ መከተላችውን  ሊገባን ይገባል፤  በሕብረተሰባችን  አነጋገር ክልል ለግጦሽ ሣር፣ ዘርም  ለገበሬ ነው ይባላል።  በዚህ  በከፋፍለህ ግዛው መመሪያችው ዜጎችን  እርስ በእርስ ማጫረሱ  አልሳካ ሲላችው፤  መጪው ትውልድ  እንደሕዝብና ሀገር ሊኖርባቸው የሚገባውን የተፈጥሮ ሐብቶቹ  ላይ  ዘምተዋል፤  የአፈር መመረዝ  ፣ የወንዞች  መበከል፣ ሆን ብሎ   ተወላጁን  ከመሬቱ አፈናቅሎ ለባአዳን መሰጠት  ትውልድን ከማጥፍት  ሀገርን   ከመሸጥ ተለይቶ የሚታይ አይደለም፤  ፈጥነን ይህንን  የወያኔ  እብደት  በጋራ   ካላስቆምነው   ከአስር ዓመት በኋላ  ሀገር አለን ብለን  ማውራት  አንችልም። የሀገራችንን ሁኔታ በጥልቀት ካየነው፣ በመግለጫ፣ በዲስኮር፣ በ ጉንጭ አልፋ  ይሰጥ  አገባ  የምንወጣው አይደልም። በእግር  ኳስ  ሕግ ‘ኳሷን ለማን እንድምታቀብላት ከመጨነቅህ  በፊት አስቀድመህ ወደ ኳሷ ተጠጋና  በቁጥጥርህ ሥር አውላት ’ ይላል ። ዛሬ ኳሷ  በኢትዮጵያ  ሕዝብ ሜዳ ላይ  ትገኛለች  ፤  በሀገር ጉዳይ  ላይ  ገለልተኛም  ቆሞ  ተመልካችም   መሆንን  ከዜጋ የሚጠበቅ  አይደለም።  በጋራ  በሀገር ሰም ተቧድኖ  ወደ መስኩ ገብቶ  ኳሷን   ከግብ  ማግባትን  ይጥይቃል።   በሀገር ጉዳይ ካታንጋና   ትሪቢዮን  ላይ   ተቀምጦ በቲፎዞነት   ማጨብጨቡ  ዋጋ አይኖርውም።
በመስኩ ላይ  ለነፃነት ለፍትህ  ለዴሞክራሲና ለአንድነት  እየሠራን  ሕብረት ፈጥረን    የወያኔን የዘረኛ አካሄድ እንፋለም!

ውጭ አገር ሊሄዱ ሲሉ በስህተት ተይዘው ታስረው የነበሩት ሹም ተለቀቁ



–    ስህተቱ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ነው ተብሏል

የአዲስ አበባ የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የግንባታ ዘርፍ ማስተባበሪያ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፣ በስህተት ታስረው አንድ ቀን ካደሩ በኋላ ተፈቱ፡፡
ምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክሉ ፍቅሩ መጋቢት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. ለ18 አጥቢያ ወደ ግሪክ ለመሄድ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሱ 


Breaking News zehabesha

ፓስፖርታቸውን ለኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምርያ ሰጥተው ወደ ውስጥ ለማለፍ ሲጠባበቁ፣ መታገዳቸው ተነግሯቸው ለብቻቸው እንዲሆኑ መደረጋቸው ታውቋል፡፡
የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የግንባታ ዘርፍ ማስተባበሪያ ምክትል ሥራ አስኪያጁ ግራ እንደተጋቡ፣ የቀረውን የሌሊት ክፍለ ጊዜ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አድረው በነጋታው እሑድ መጋቢት 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በምን ጥፋት እንደታገዱ ሲጠይቁ፣ ከአገር እንዳይወጡ ያሳገዳቸው የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መሆኑ እንደተነገራቸው ታውቋል፡፡
ቀኑ እሑድ በመሆኑ በምን ምክንያት እንደታገዱ መጠየቅ ያልቻሉት አቶ ተክሉ አዳራቸውን በመምርያው ለማድረግ ተገደዋል፡፡ መጋቢት 11 ቀን 2008 ዓ.ም. ከአገር እንዳይዋጡ ዕግድ ያስጣለባቸው ፀረ ኮሚሽን ሲጠየቅ፣ በ2006 ዓ.ም. ከአቶ ተክሉ መሥሪያ ቤት በሙስና የተጠረጠሩ ኃላፊዎች ሲከሰሱ የሳቸውም ስም ወደ ተቋሙ ተልኮ እንደነበር፣ የተከሰሱት ከአገር እንዳይወጡ ዕግድ ሲጣል ስማቸው አብሮ መላኩን መግለጹን አቶ ተክሉ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ አቶ ተክሉ በወቅቱ ስማቸው የተላከ ቢሆንም፣ የማይፈለጉ መሆኑን አረጋጋጦ ማሰረዝ (ማስነሳት) ሲገባው ዝም ብሎ ከሁለት ዓመታት በላይ ማቆየቱ ተገቢ አለመሆኑን አስረድተዋል፡፡
አቶ ተክሉ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ የተያዙት የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ከግሪክ አቻው ጋር በውኃና ፍሳሽ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ላለው ትምህርታዊ የልምድ ልውውጥ ለመሄድ ሲሉ ነው፡፡
የልምድ ልውውጡን ለመካፈል ወደ ግሪክ የሚሄዱት አቶ ተክሉን ጨምሮ አምስት አባላት ያሉትና በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ዋለልኝ የሚመራ ቡድን የነበረ ቢሆንም፣ ኮሚሽኑ ፈጠረው በተባለ ስህተት ምክንያት አቶ ተክሉ ሳይሄዱ ቀርተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከግሪክ ውኃና ፍሳሽ መሥሪያ ቤት ጋር ትምህርታዊ ሥልጠናና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ባደረገው ከፍተኛ ጥረት ዕድሉን በማግኘቱ፣ ለልዑኩ የአውሮፕላን ትኬትና ሌሎች ወጪዎችን ወጪ ማድረጉ ታውቋል፡፡ ከፍተኛ እምነት የተጣለባቸውና የልምድ ልውውጡን በመካፈል ለባለሥልጣኑ የአሠራር መሻሻልና ለውጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ የታመነባቸው አቶ ተክሉ፣ በፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የግዴለሽነት አሠራር ሊጨናገፍ መቻሉ አሳዛኝ መሆኑን፣ የውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የሥራ ባልደረቦች ለሪፖርተር አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
አዲስ በተረቀቀውና ለፓርላማ በቀረበው የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ፣ የመመርመርና የመክሰስ ሥልጣኑ ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ እንደሚሰጥበት በቅርቡ የተገለጸው የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ በአቶ ተክሉ ፍቅሩ ላይ ፈጽሞታል ስለተባለው ስህተት ማብራሪያ እንዲሰጥ ሪፖርተር ለማግኘትና ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡ አንድ ተጠርጣሪ በተጠረጠረበት ወንጀል ፍርድ ቤት ቀርቦ በሚደረግ ክርክር፣ የዋስትና መብቱ ተከብሮ በውጭ ሆኖ ጉዳዩን እንዲከታተል ሲፈቀድለት፣ እንደየጉዳዩ ክብደት ከአገር እንዳይወጣ ለብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት እንዲጻፍ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚሰጥ ቢሆንም፣ አቶ ተክሉ በወንጀል ተጠርጥረው ሳይከሰሱ፣ ምርመራ ሳይጣራባቸውና ሳይታሰሩ ከአገር እንዳይወጡ መታገዳቸው ከማስገረምም ባለፈ፣ በእያንዳንዱ ዜጋ ላይ ጥርጣሬ የሚፈጥር መሆኑን አስተያየት የሰጡ የሕግ ባለሙያዎች ተናግረዋል፡፡

የማለዳው ሰማይ መረጃ ! – ነቢዩ ሲራክ



እህት ፈቲሐ ነገ ወደ ሐገር ቤት ትገባለች !
=================
* ለወራት በህክምና ላይ የነበረችው እህት ፈቲሐ በወገኖቿ አይዞሽ ባይነት ከትናንት ዛሬ ተሽሏታል
* ያ የተቃጠለ የሚመስለው መልኳ ዛሬ ወዝ ይታይበታል 
* እህት ፈቲሐ ነገ ወደ ሐገር ቤት እንድትገባ ትልቅ ድጋፍ ያደረጉላት አረብ አሰሪዎቿ ናቸው
* አረብ አሰሪዎቿ የመውጫ ቪዛ አስጨርሰው በራሳቸው ገንዘብ ትኬት ቆርጠውላታል
* አረብ አሰሪዎቿ መራመድ የማይችለውን እህት ፈቲሐን ሐገር ቤት ደግፎ የሚያደርስ የጤና ረዳት ቀጥረውላታል
* ፈቲሐ ነገ አርብ በሳውዲ አየር መንገድ ከምሽቱ 10:30 ላይ የሀገሯን ምድር ትረግጣለች
* እህት ፈቲሐ የናፈቋት ቤተሰቦቿን እስክትቀላቀል ከአየር መንገድ ለመቀበል ያቀረብነውን ጥሪ ወዳጃችንSamuel Masresha ተቀብሏል፣ እናመሰግናለን!
* ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቲሐን ምስል ተመልክቶ በእንባ የታጠበው አንጀተ ርህሩህ ወዳጃችን ሳሙኤል ማስረሻ ለእህት ፈቲሐን በመንግስት ሐኪም ቤቶች ግብታ ህክምና እንድታገኝ እንደሚሞክር ቃል ገብቶልኛል
* የተመላሽ ስደተኞች አባት የምንለው ወዳጃችን ሳሙኤል ማስረሻ ቀይ መስቀልን አምቡላንስ ጠይቆ ተፈቅዶለታል
* እዚህም እዚያም ዝግጅቱ ተጠናቅቋል
* እህት ፈቲሐ በጤና እያለች ሰርታ ካገኘችውና በአደራ በጅዳ ቆንሰል ያስቀመጠችውን 4800 የሳውዲ ሪያል ገንዘቧን ዛሬ እንደምትረከብ ትናንት አጫውታኛለች

በእህት ፈቲሐ ለወራት በንጉስ ፉአድ ሆስፒታል ታክማ አሁን ከበፊቱ ተሽሏታል ። በጅዳና አካባቢው ያሉ ለነፍሳቸው ያደሩ በርካታ ኢትዮጵያውን ዘር ሐይማኖት ሳይለዩ ላለፉት ወራት ፈቲሐን እየጎበኙ ተስፋ ሰጥተዋታል ፣ ደግፈዋታል !
” የመንግስት ተወካዮች እርባና ያለው ድጋፍ በማያደርጉበት ሰአት ዜጎች እርስ በርሳችን እንዲህ ሲተባበሩ ማየት ደስ ይላል ! ” ያለኝ ፈቲሐን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው እየደገፈ ያለው ወንድም ነው !
እህት ፈቲሐ ለደገፋት ለሁሉም ምስጋና አቅርብልኝ ብላኛለች ፣ ምስጋናዋ ይድረሳችሁ !

ነቢዩ ሲራክ
መጋቢት 22 ቀን 2008 ዓም

127128


129




Wednesday, March 30, 2016

‹ሀገር ማለት ሰው ነው›፤ እስኪ ሙት በለኝ! (በዲያቆን ዳንሄል ክብረት)



ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገርሙኝ ዘፈኖች አንዱ ‹ሀገር ማለት ሰው ነው› የሚለው ነው፡፡ እሥራኤላዊና ጂፕሲ ይህንን ቢሰሙ ምን ይሉ ይሆን? እላለሁ፡፡ አይሁድ በመላው ዓለም ለ1900 ዓመታት ያህል ተበታትነው ሲኖሩ በየአካባቢው ሰው ነበራቸው፤ያውም እንደ ብረት የጠነከረ ማኅበረሰብ፤ ሀገር ግን አልነበራቸውም፡፡ ሀገር ማለት ሰው ከሆነ አይሁድ ሀገር ፍለጋ ከሺ ዓመታት በላይ መኳተን አልነበረባቸውም፡፡ በአውሮፓ የሚኖሩት ጂፕሲዎች የታወቀ ማኅበረሰብ አላቸው፡፡ ነገር ግን ሀገር የላቸውም፡፡ ሀገር ማለት ሰው ቢሆን ኖሮ ጂፕሲ የሚባል ሕዝብ ብቻ ሳይሆን ጂፕሲ የሚባል ሀገርም ይኖር ነበር፡፡ ግን የለም፡፡
daniel kibret
በአሜሪካ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን አሉ፡፡ ‹በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን› የምትባል ሀገር ግን የለቺም፡፡ 1.3 ሚሊዮን የሚደረሱ ግሪኮች በአሜሪካ ይኖራሉ፡፡ ‹የአሜሪካ ግሪኮች› የምትባል ሀገር ግን የለችም፡፡ ‹ግሪክ ሲሠራ አሜሪካ ይኖራል፣ ሲያረጅ ግሪክ ይጦራል› የተባለው ሀገር ሰው ብቻ ስላልሆነ ነው፡፡
ሰዎች ተሰብስበው ሀገር ሊመሠርቱ አይችሉም፡፡ በየሀገሩ የተሰበሰቡ ማኅበረሰቦች ‹ኮሙኒቲ› ይባላሉ እንጂ ሀገር አይባሉም፡፡ ሀገር ሀገር ለመሆንና ለመባል ከሰው በተጨማሪ የምትፈልገው ብዙ ነገር አላትና፡፡ ሀገርን ሀገር ለማስባል መሬትም ያስፈልጋል፤ መሬት ሳይኖርህ ሰው ስለሰበሰብክ ብቻ ሀገር ልትሆን አትችልም፡፡ ያውም የእኔ የምትለው፣ የምትሞትለትና የምትለፋለት ታሪካዊ መሬት ያስፈልግሃል፡፡ አይሁድ በ1930 አካባቢ በኡጋንዳ ኡዋሲን ጊሹ (Uasin Gishu County) በተባለ ቦታ እንዲሠፍሩና ሀገር እንዲኖራቸው ታስቦ ነበር፡፡ እንደ ቴዎዶር ኸርዝል ያሉ ታላላቅ የጽዮናዊነት መሪዎችም ለጊዜውም ቢሆን ተስማምተውበት ነበር፡፡ ብዙኀኑ አይሁድ ግን ‹ሀገር ማለት የሆነ መሬት አይደለም፡፡ ታሪካዊ መሬት ነው› ብለው ተቃወሙት፤ ሀገር ማለት የሆነ መሬት ብቻ ቢሆን ለአይሁድ ከዛሬዋ እሥራኤል ይልቅ በአየር ንብረትና በተፈጥሮ ማዕድን፣ ብሎም በአቀማመጥ ኡጋንዳ ትሻላቸው ነበር፡፡
ባድሜ ለምትባል ከጦርነቱ በፊት ብዙው ሕዝብ ሰምቷት ለማያውቅ መሬት የተደረገውን ጦርነት የረሳ ሰው ነው ‹ሀገር ማለት ሰው ነው› የሚል፡፡ ሀገር ማለት ሰው ከሆነ ለባድሜ የተደረገው ጦርነት ለማን የተደረገ ነው ሊባል ነው፡፡ በሄግ ፍርድ ቤት የነበረው ክርክርስ የመሬት ክርክር እንጂ የሰው ክርክር ነበር እንዴ?
ሀገር ማለት ሰው ቢሆን ኖሮ ሰው ስለ ሀገሩ ሲያነሣ ወንዙን፣ ተራራውን፣ ሸለቆውን፣ ሜዳውን፣ ጫካውን እያነሣ ለምን ይዘፍን ነበር ፡፡
‹ያገሬ ተራራ ወንዛ ወንዙ ለምለም
እማማ ኢትዮጵያ ኑሪ ለዘላለም› ለምን ይል ነበረ፡፡
ሀገር ማለት ሰው ከሆነ ይሄ የኔ ክልል፣ ጎጥና መንደር ነው የሚለው ክርክር ከየት ይመጣ ነበር? ሀገር ማለት ሰው ከሆነ የተለየና የታወቀ የሀገር ድንበርና ካርታ ለምን ያስፈልግ ነበረ? ሰውማ የትም ነው የሚኖረው፡፡ ካርታ አያሻውም፡፡ ሀገር ማለት ሰው ከሆነ ለምን የአብዛኞቹ ሀገሮች ብሔራዊ መዝሙር ስለ መሬቱና ስለ ድንበሩ ያወራል? ሀገር ማለት ሰው ከሆነ ለሰው ፓስፖርትና ቪዛ ለምን ያስፈልገዋል? ሰው ያለበት ቦታ ሁሉ ሀገሬ ስለሆነ ለምን እንደፈለግኩ ወጥቼ አልገባም? አንድ ሰው ወደ አንድ ሀገር ገባ የሚባለው ወደ መሬቱ ሲገባ እንጂ የሀገሩን ሰው ሲያገኝ ነው እንዴ? ምናልባትም ከአንታርክቲካ በቀር ቪዛ መጠየቅ ያለበት ሀገር አልነበረም፡፡ እርሱ ሰው የለበትምና ‹ሀገር ማለት ሰው ነው› የሚለው አይመለከተውም፡፡ ሀገር ማለት ሰው ከሆነ በሰማይ የሚሄድ አውሮፕላን ‹የአየር ክልሌን ጣሰ› ብሎ መሟገት ምን የሚሉት ሞኝነት ነው? ሰውን አልጣሰ፣ የጣሰው አየር ነው፡፡
ደግሞም አገር ማለት መሬት ብቻ አይደለም፡፡ ያማ ቢሆን ኖሮ አንታርክቲካ ሀገር ይሆን ነበር፡፡ ያማ ቢሆን ኖሮ በዓለም ላይ የሚገኙ ወደ ሃምሳ የሚጠጉ ሰው አልባ ደሴቶች(nonecumene)‹ሀገር› ተብለው በተባበሩት መንግሥታት ይመዘገቡ ነበር፡፡ ሀገር ማለት መሬት ቢሆን ኖሮ መሬት ያለው ሁሉ ሀገር ይኖረው ነበር፡፡ የአሜሪካ ሕንዶች፣ የአውስትራልያ አቦርጅኖች፣ ከጥንት ጀምሮ የሚኖሩበት መሬት አላቸው፡፡ የራሳቸው የሆነ ሀገር ግን የላቸውም፡፡ ደቡብ ሱዳናውያን የራሳቸው የሆነ የሚኖሩበት መሬት ነበራቸው፤ ሀገር ለመሆን ግን መዋጋት ነበረባቸው፡፡ ደቡብ ሱዳኖችን ያን ሁሉ ዘመን ያዋጋቸው የመሬት ጥያቄ ሳይሆን የሀገርነት ጥያቄ ነው፡፡ የራሳቸውን ፖለቲካዊ መሬት አግኝተው እንኳን ሀገር ለመሆን ገና እየተሠሩ ነው፡፡ ፍልስጤማውያን ይብዛም ይነስ የሚኖሩበት መሬት አላቸው፡፡ አገር ግን የላቸውም፡፡
አገር ከዚህ ሁሉ በላይ ነው፡፡ ሰው፣ ሰው የኖረበትና ታሪክ የሠራበት መሬት፣ ማኅበረሰብ ከማኅበረሰብ፣ ሰው ከሰው፣ ሰው ከማኅበረሰብ፣ ሰው ከመሬት፣ ሰው ከአራዊት፣ ሰው ከተፈጥሮ፣ ሰው ከወራሪ ጋር የነበረው ትግል፣ ውጊያና ወዳጅነት፤ የተረተው ተረት፣ ያወጋው ወግ፣ የፈጠረው አፈ ታሪክ፣ ያከማቸው ትዝታ፣ ሰው ለመሬቱ፣ ለወገኑና ለእምነቱ የከፈለው መሥዋዕትነት፤ የዘፈነው ዘፈን፣ ያቅራራው ቀረርቶ፣ የፎከረው ፉከራ፤ ያገኘው ድልና የተሸከመው ሽንፈት፤ ያደረሰው በደልና የደረሰበት በደል ይሄ ሁሉ ነው ሀገር፡፡
መገለጫው ቅርስ፣ መዋሐጃው ባህል፣ መታያው ልብስና መዋቢያው ጌጣጌጥ፣ መገናኛው ቋንቋ፣ መዝናኛው ጭፈራ፤ ማስተማሪያው ተረት፣ መክበሪያው ዓመት ባል፣ መጠበቢያው ምግብ፣ መቆዘሚያው እንጉርጉሮ፣ መተከዣው ልቅሶ፣ መተኪያው ልደት፣ ማሳረጊያው ቀብር፤ መገምገሚያው ምግባር፣ ማነወሪያው ነውር፤ መኩሪያ ጀግንነቱ፣ ማፈሪያ ገመናው፤ መደበቂያ ቤቱ፣ መመረሪያ ጫካው፤ ይሄ ሁሉ ነው ሀገር፡፡ ታሽቶ ተገርኝቶ ያመጣው አንድነት፣ ተጣልቶ ተባልቶ ያመጣው ልዩነት፣ እንደ ዘሐ ዘጊ የተጠላለፈው፣ እንደ እግር ሠንሠለት የተቆላለፈው፣ ሲፈተል፣ ሲገመድ፤ ሲባዘት፣ ሲዳውር፤ ሲከካ፣ ሲሰለቅ፤ ሲጣላ፣ ሲታረቅ፤ ሲያውቅና ሲማይም፤ ሲሠለጥንና ሲደኸይ፤ ሲሰፋና ሲጠብ፤ የኖረውና የኖረበት፣ የኖረለትም ነው ሀገር፡፡
ሀገር ትዝታ ነው፡፡ የትም ቦታ ስትሄድ ጠምዶ የሚያመጣህ፡፡ ምንም ሥጋ ብትቆርጥ ከብቱ ትዝ ይልሃል፤ ምንም ቢች ዳር ብትዝናና ወንዙ ትዝ ይልሃል፤ ምን በሽቱ ብትታጠን አፈሩ ይሸትሃል፤ ምን በሥጋጃ ላይ ብትሄድ ጉዝጓዙ ይመጣብሃል፡፡ በኮምፒውተር እየሠራህ ያቦካኸው ጭቃ ይናፍቅሃል፤ በጄት እየበረርክ አህያና በቅሎው ያምርሃል፤ ማንሐተን ተቀምጠህ ሰባተኛ፣ ሎንደን ተቀምጠህ ቂርቆስ፣ ኖርዌይ ሆነህ ጅግጅጋ፣ ካናዳ ሆነህ ሐረር ይወዘውዝሃል፡፡ ሀገር ማለት ትዝታ ነው፡፡
ሀገር ማለት ከምትገልጠው ብታስበው፣ ከምትኖርበት ብትሞትበት፤ ከምትስቅለት ብታለቅስለት የምትመርጥለት ነገር ነው፤ ሀገር ማለት ትተህው ብትሄድ ትቶህ የማይሄድ፣ በራቅከው ቁጥር ልብህ ውስጥ የሚቀር፣ ባወቅከው ቁጥር የምትንገበገብለት፤ በተረዳኸው ቁጥር የምትሳሳለት፣ አንተን እርሱ ውስጥ እንደምታገኘው ሁሉ እርሱንም አንተ ውስጥ የምታገኘው፤ የተሠራህበት ውሑድ፤ የተቀረጽክበት ማንነት ነው ሀገር፡፡
ሀገር ማለት ሰው ብቻ ቢሆን ኖሮ ዘመድ የሌለው ሰው ወደ ሀገሩ ለመምጣት ባልናፈቀ ነበር፡፡ ሀገር ማለት ሰው ብቻ ቢሆን ኖሮ ዘመዶቹ ሁሉ ከእርሱ ጋር ውጭ የሚኖሩለት ሰው ‹ሀገሬን ሀገሬን› እያለ መከራ ባላየ ነበር፡፡ ሀገር ማለት ሰው ብቻ ቢሆን ኖሮ ሰዎች በየዘመናቱ የበደሉት ሰው ሀገሬ በደለችኝ ባለ ነበር፡፡ ሀገር ማለት ሰው ብቻ ቢሆን ኖሮ ሰው ስለ ሀገሩ ሲያስብ ተራራውና ወንዙ፣ አዕዋፉና አራዊቱ፣ ማሳውና ቀየው ለምን ትዝ ይለው ነበር፡፡ በሀገር ማለት ሰው ብቻ ቢሆን ኖሮ ያሸነፈ አትሌት፣ ድል ያደረገ ኳስ ተጨዋች ባንዴራው ሲሰቀል ለምን ያለቅስ ነበር?
‹አዙረሀ አዙረህ ሀገሬ መልሰኝ
በሹም ታዘዘ አፈር አታልብሰኝ› ብሎ ለምን ያንጎራጉር ነበር፡፡ ዐጽሙ በአፈሩ እንዲያርፍ ለምን ይናዘዝ ነበር፡፡ ለምን ሙሾውን፣ የሠርግ ዘፈኑን፣ ወጉን ማዕረጉን ይፈልገው ነበር፡፡
ሀገር በአርምሞ እንጂ በንግግር፣ በተግባር እንጂ በዝርዝር ሊናገሩለት የማይቻል ነገር ነው፡፡ ውጥንቅጥ ሰበዞች የሰፉት ሞሰብ፣ዓይነተ ብዙ ድርና ማጎች የሸመኑት ጋቢ፣ ልዩ ልዩ ቅመሞች የሠሩት ወጥ፣ ብዙ ገባሮች የፈጠሩት ዓባይ፣ ብዙ ትውልዶች የከመሩት ተራራ፣ ከአራቱ አቅጣጫ ተሰብስቦ በአንድ ወፍጮ የተፈጨ እህል፣ ከየአበባው ተቀስሞ በአንድ ቀፎ የተሠራ ማር፣ ከየእህሉ ወጥቶ በአንድ ማድጋ የተጠመቀ ጠላ፣ ከየ እንጨቱ ተለቅሞ በአንድ ጽንሐ የታጠነ ዕጣን ነው ሀገር፡፡
ሀገር ማለት ሰው ነው? እስኪ ሙት በለኝ

በኦሮሚያ በአርሲና ኤሊባቡር የተማሪዎች ተቃውሞ አገርሽቷል – በምዕራብ ሐረርጌም ለሁለተኛ ቀን እንደቀጠለ ነው

ዘ-ሐበሻ) ጋብ ያለ መስሎ የነበረው የኦሮሞ ሕዝብ ተቃውሞ እንደአዲስ በየቦታው እያገረሸ መሆኑ ከስፍራው ለዘ-ሐበሻ የሚደርሰው መረጃ ጠቆሙ::
በኦሮሚያ በተለያዩ አካባቢዎች እንደአዲስ ተቃውሞው ያገረሸባቸው አካባቢዎች ኢሊባቡር; ሐረርጌ እና አርሲ ናቸው:: በምዕራብ ሐረርጌ ፋዴስ ወረዳ የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ ሁለተኛ ቀኑን የያዘ ሲሆን በኦሮሚያ ክልል የሰፈረው የሕወሓት ልዩ ኃይል በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ተቃውሞውን እንዲያቆሙ እርምጃ ለመውሰድ ቢሞክርም የሕዝቡ ቁጣ ገንፍሎ እንደሚገኝ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ለዘ-ሐበሻ የሚደርሱት መረጃዎች ያመለክታሉ:: የአካባቢው ነዋሪ የወረዳውን አስተዳደር ከስልጣን እንዳባረረውም ጨምሮ የደረሰን መረጃ ይጠቁማል::
oromo
በኤሊባቡርና አርሲም እንዲሁም ዳግም የሕዝቡ ቁጣ አይሎ ከሕወሓት ልዩ ኃይል ጋር ህዝቡ ተፋጦ እንደሚገኝ ተሰምቷል:: በኤሊባቡርና አርሲ የተለያዩ ከተሞች የተነሳውን የሕዝብ ተቃውሞ እያካሄዱ የሚገኙት ተማሪዎች ናቸው ተብሏል::

በሌላ ዜና በኮፋሌ በተደረገ የህዝብ ተቃውሞ በሕወሓት ልዪ ኃይል ተመቶ ቁስለኛ የነበረው ወጣት አሊ ቡሪ ቀሬሶ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሕይወቱ ማለፉ ተሰማ:: በኮፋሌ ከተማ ሓዊ ሆቴል ውስጥ ሰራተኛ የነበረው ይኸው ወጣት የአጋዚ ወታደሮች ወደ ሆቴል በመምጣት ወጣቱን የግል ቴሌቭዥን ጣቢያዎችን በተለይም ኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክን ለሆቴሉ ደንበኞች ታሳያለህ በሚል ክፉኛ ቀጥቅጠው አቁስለውታል:: በዚህም ጉዳት የደረሰበት ወጣት ለሕክምና ወደ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መጥቶ ዛሬ ሕይወቱ ማለፉ ተሰምቷል::oromo st

የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር ዜናዎች



ርዕሰ ዜና 
– ኖርዌይ የፖለቲካ ጥገኛነት የጠየቁ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው ልትልክ ነው
– የታክሲ ነጅዎች አድማ እንደገና ሊጀምር ይችላል ተባለ
– በትግራይ የቤት መስሪያ የቦታ ስፋት እንዲጨምር ተደረገ
– የሶማሊያ መንግስት 115 የአልሸባብ አባላት የተገደሉና ሌሎች 110 የተማረኩ መሆናቸውን ገለጸ
* የግብጽ የመንገደኛ አውሮፕላን ተጠለፈ
– በመከካለኛው አፍሪካ ሪፕብሊክ ተጨማሪ የተመድ የሰላም አስከባሪ አባላት በወሲብ ወንጀል ተከሰሱ

መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø የኖርዌይ መንግስት የፖሊቲካ ጥገኝነት የጠየቁ 800 ኢትዮጵያውያንን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ የተዘጋጀ ሲሆን ከሚላኩት ውስጥ 60ዎቹ ህጻናት እንደሆኑ ተገልጿል። መንግስቱ ስደተኞች ያቀረቡት የፖሊቲካ ጥገኝነት ጥያቀ ተቀባይነት አላገኘም በማለት በግዳጅ ለመመልስ ይወስን እንጅ የስደተኛ ከለላ ጠባቂ የሆኑ ድርጅቶች ግን ስደተኞቹ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱ በአካላቸውና በመንፈሳቸው ጉዳት ከማምጣቱ በተጨማሪ ለህይወታቸው አስጊ እንደሚሆን በመጥቀሰ መንግስት ጉዳዩን እንደገና እንዲመለተው ውትወታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በቅርቡም በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የኖርዌይን መንግስት ውሳኔ በመቃወም ኦስሎ ላይ ታላቅ የተቃውሞ ስለፍ ማድረጋቸው ይታወሳል። የወያኔ ቡድን መሪዎች በሀገር ውስጥ ሕዝብን በዘረኛ አምባገነን አገዛዝ ረግጦ መግዛት ብቻ ሳይሆን በውጭ ሀገር የሚኖሩትም ገጽታችንን ያበላሻሉ በማለት ከየቦታው ለማስወጣት ከየአገሮቹ ጋር ልዩ ልዩ ስምምነት እየፈጠሩ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከፍተና መከራና ስቃይ እየደረሰባቸው ነው።
Taxii
Ø ከጥቂት ቀና በፊት በአዲስ አበባ ከተማ የታክሲ ሹፌሮችና ባለንብረቶች አዲስ የወጣውን የትራፊክ ህግ በመቃወም የሥራ ማቆም አድማ በማድረጋቸው የወያኔ መሪዎች ሕጉ እንደገና እንደሚታይና ለሶስት ወር ተግባራዊ እንደማይሆን በመግለጽ የሥራ ማቆም አድማውን ለጊዜውም ቢሆን ማስቆማቸው ይታወሳል። ሰሞኑን ውስጡን አዲሱን የተራፊክ ሕግ ተግብራዊ እያደረጉ በመምጣታቸው ምክንያት አንዳንድ የታክሲ ሹፌሮች ትናንት መጋቢት 19 ቀን 2008 ዓም ለአገልግሎት ሳይወጡ የቀሩ መሆናቸው የታየ ሲሆን በወያኔ ካድሬዎች ለታክሲዎቹ መጥፋት የገብርኤል በዓል እንደምክንያት ሲሰጥ ውሏል ። በዛሬው ዕለት መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓም በስራ መግቢያ ሰዓት ላይ ከፍተኛ የታክሲ ዕጥረት እንደነበር ታውቋል፡፤ ይህ የታክሲ ዕጥረት የተከሰተው በርካታ አሸከርካሪዎች ለሥራ ባላመውጣታቸው መሆኑ ሲታወቅ ምናልባት የታክሲ ማኅበራቱ አጥቃላይ አድማ ሊጠሩ ይችላሉ ተብሎ ተገምቷል። አሁን ያለው የታክሲ ሥራን የማቀዝቀዝ አድማ አዲስ አበባ ከተማን ውጥረት ውስጥ ከቷል።
Ø ከምርኮኛ ወታደሮች ወያኔ በአምሳሉ ጠፍጥፎ የሰራው ኦህዴድ የመሠረተበትን 24 ኛ ዓመት አከብራለሁ ይበል እንጅ እንደታሰበውና እንደታቀደው መከበሩ አጠያያቂ እየሆነ ነው። የወያኔው ኦህዴድ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በተዋረድ ታች ያሉትን አባላትና ደጋፊዎች ሰብስቦ ለማነጋገር ይታቀድ እንጅ ከሕዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ ከሕዝብና ከታች አባላት ጋር መገናኘቱ አስቸጋሪ እንደሚሆን ከወያኔው ኦህድዴ ጽሕፈት ቤት አካባቢ የተገኘው መረጃ አመልክቷል። ኦህዴድ ቀደም ሲል በያዘው መርሀ ግብር መሠረት የድርጅቱ ባለሥልጣናት በየቦታውና በየአዳራሹ እየተገኙ የኦህዴድን በዓል እንዲያስከብሩ የታቀደ ቢሆንም የወገኖቻችንን ደም በአግአዚ ወታድሮች እያፈሰሰ እንዴት በዓልና ፌስታ ይኖራል? ኦህዴድ የአሰገዳይና የገዳዮች ተባባሪ ሆኗል በማለት ካድሬዎቹ እርስ በርስ መነጋገራቸው የኦህዴድ በዓል መከበሩ አጠያያቂ ሆኗል። ከዚህ በዓል አካባበር ጋር በተያያዘ ዋና የተባሉ ካድሬዎች በዓሉ ከተከበረ ላለመገኘት የዓመት ፈቃድና የህክምና ፈቃድ እየጠየቁ ከስራ እየወጡ መሆናቸው ታውቋል።
Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ለከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲያቸው እንዲያመች አድላዊና ዘረኛ አምባገነን አገዛዝን ከመሠረቱ ጊዜ ጀምሮ የትግራይ ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመነጠል የኢኮኖሚ የፖሊቲካ የወታደራዊ የትምህርት የልማትና የኢንቨስትመንት የሚዲያዎች ወዘተ ሥራዎች ለትግራይና ለትግራይ ተወላጆች ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል። ሰሞኑን ደግሞ በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል የማይታሰበውን በትግራይ አዲስ ቤት የሚሰራበትን ቦታ ስፋት በመጨመር መመሪያ አውጥቷል። በመመሪያው መሠረት ቀደም ብሎ ቤት ሰሪዎች ከ180 ካሬ ሜትር በላይ የማይፈቅድላቸው የነበረ ሲሆን አሁን ከዚያ በላይ በሆነ የቦታ ስፋት ላይ መስራት እንደሚችሉ ተፈቅዶላቸዋል። የወያኔ ቡድን መሪዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመላ ኢትዮጵያ እየተቀጣጠለ የመጣውን የተቃውሞ እሳት በትግራይ ሕዝብ ኪሳራ ለማዳፈን ትግራይ ውስጥ አንድ ግዙፍ የኬሚካል ፋብሪካ ለማቋቋም ከወስኑ ወዲህ አሁን ደግሞ የቤት ሠሪዎችን የቦታ መጠን ለማስፋት መፍቀዱ የትግራይ ሕዝብ ከጎኑ ለማሰልፍ የሚደርግ ጥረት መሆኑ ታውቋል። ብዙ ሀገር ወዳድ ዜጎች ወያኔ ከትግራይ ውጭ ባሉ ኢትዮጵያያኖች ላይ የሚፈጽመው ግድያ እስር በደልና አድልዎችን በትግራይ ሕዝብ ላይ ለለላው መጠን እንዲፈጽም ፍላጎት ባይቦራቸውም እንደ ትግራይ ግን ልማትና እንክብካቤ ቢኖራቸው እንደማይጠሉ ይናገራሉ።
alshebab
Ø ሰሞኑን በሰሜን ሶማሊያ በአልሸባብና መንግስቱን በሚደግፉ ወታድሮች መካከል በተካሄደ ውጊያ 115 የአልሸባብ ወታድሮች መገደላቸውን የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ አስታውቋል። 110 የአልሸባብ ታጣቂዎች መማረካቸንና ሌሎች ወደ ገጠር ማምለጣቸውን መግለጫው ጨምሮ ገልጿል። ታጣቂዎቹ ሽንፈት የገጠማቸው ለአራት ተከታታይ ቀኖች በተደረገ ጦርነት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የሶማሊያ መንግስት በውጊያ ስለደረሰበት ጉዳይ የሰጠውም መግለጫ የለም።ይህ የመንግስት መግለጫ በሌላ በሶስተኛ ወገን አልተረጋገጠም። አልሸባብ በደቡብ ሶማሊያ በርካታ ሽንፈት ስለገጠመው በሰሜን የጦር ሰፈር ለመመስረት እየሞከረ ነው ተብሏል። 22000 የሚደርሱ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል በሱማሊያ የሚገኝ ሲሆን የሶማሊያ መንግስትን አልሸባብን ለመደምሰስ የቆረጠ መሆኑን በተደጋጋሚ ቢዝትም የቡድኑ እንቅስቃሴ ጎላ እያለ መምጣቱን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ሰዎች ይጠቁማሉ
OPDO 5
Ø አሌክሳንድሪያ ከምትባለው የወደብ ከተማ ወደ ካይሮ ሲበር የነበረው የግብጽ የመንገደኛ አውሮፕላን ተጠልፎ ወደ ቆፕሮስ (ሳይፕረስ) መወሰዱ ተነገረ። ጠለፋው ከሽብረተኛነት ጋር የተያያዘ አይደለም የተባለ ሲሆን አውሮፕላኑ በቆፕሮስ አውሮፕላን ማረፊያ እንዳረፈ ተሳፋሪዎቹ በሙሉ ተለቀዋል። በአውሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት 55 መንገደኞች መካከል 21 ዱ የውጭ አገር ሰዎች መሆናቸው ተገልጿል። ጠላፊው በእጁ ላይ የያዘው ምንም ዓይነት ፈንጅ ወይም መሳሪያ ያልተገኘ ሲሆን ጠለፋውን ለመፈጸም ያስገደደው በቆፕሮስ የምትኖረውን ፍቅረኛውን ለማይት መሆኑን ገልጿል። ጠላፊው በቁጥጥር የተደረገ ሲሆን በቆፕሮስ የፖሊቲካ ጥገኛነት ጠይቋል።
Ø በአይቮሪ ኮስት ሰሜናዊ ግዛት ባለፈው ሳምንት ረቡዕ መጋቢት 14 ቀን 2008 በአርብቶ አደሮችና በአካባቢው ገበሬዎች መካከል በግጦሽ ምክንያት በተነሳ የእርስ በርስ ግጭት የአስራ ሰባት ሰዎች ህይወት የጠፋ ሲሆን ከ 1300 የሚሆኑ ሰዎች በላይ የሆኑ ሸሽተው ወደ ቡርኪና ፋሶ የገቡ መሆናቸው ተገልጿል። ከተሰደዱት መካከል አብዛኞቹ ሴቶችና ህጻናት ናቸው። በአይቮሪ ኮስት በዘላኑ ህብረተሰብ እና በገበሬዎች መካከል በግጦሽና በውሃ አጠቃቀም ብዙ ግጮት ሲደደሩ የቆዩ ቢሆንም የአሁኑ ከፍተኛ የነበረ መሆኖ ተገልጿል።
Ø በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ የሚገኙ ሁለት የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በወሲብ ወንጀል የተከሰሱ መሆናቸውን የተመድ ቃል አቀባይ ሰኞ መጋቢት 19 ቀን ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ገለጹ። ተጠርጣሪዎቹ አንዱ የብሩንዲ ሌላው የሞሮኮ ወታደሮች ሲሆኑ በማዕካለአዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ሴቶችን አስገድዶ በመድፈር ክስ የተመሰረተባችደውን የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ቁጥር ወደ 25 ከፍ አድርጎታል። በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ ብሩንዲ 1128 ወታድሮች ሞሮኮ ደግሞ 741 ወታድሮች ሲኖሯቸው ሞሮኮ በወታደሩ ላይ የተሰነዘረውን ክስ የምትመረምር መሆኗን ገልጻለች። ባለፈው ሳምንት አስፈላጊ ከሆነ በቻድ ውስጥ የሚገኘው ወደ 12 000 የሚደረሰው የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል በሙሉ በለላ ኃይል ሊለውጥ እንደሚችል የተመድ ዋና ጸሀፊ ባንኪ ሙን መግለጻቸውና ይህንን አስመልክቶ በመጋቢት 2 ቀን 2008 ዓም ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡
Ø በምግብ እጥረት ምክንያት ከደቡብ ሱዳን ወደ ሱዳን የሚሰደደው ሕዝብ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መሄዱ ተነገረ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽን ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓም እንዳስታወቀው በደቡብ ሱዳን ውስጥ በሰሜን ምዕራብ ግዛቶች ብቻ 38000 ሺ የሚሆኑ ስደተኛች ወደ ምስራቅና ደቡብ ዳርፉር ግዛት የተሰደዱ መሆናቸውን ገልጿል። ኮሚሽኑ የስደተኞቹ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ እንደሆነ ገልጾ ልጆች ከወላጆቻቸው የተለዩ መሆናቸውንና ከፍተኛ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑ አብራርቷል። ባለፉት ሶስት ዓመታት በደቡብ ሱዳን በተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነት 2.3 ሚሊዮን የሚሆን የደቡብ ሱዳን ዜጋ ከሚኖርበት ተነቅሎ ወደ ሌሎች ቦታዎች የተሰደደ መሆኑ ይታወቃል።
Ø በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ ከተማ የኖርዝ ዌስት ዩኒቨርስቲ ለአንድ ወር ያህል ከተዘጋ በኋላ እንደገና መከፈቱ ተነገረ። ከጥቂት ወራት በፊት በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የትምህርቱ ክፍያ እንዲቀንስ፤ የኖሮ ሁኔታ እንዲሻሻልና ለነጮች ፍላጎት የተዘጋጀው የትምህርት ሥርዓት እንዲሻሻል በመጠየቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ሲካሄድ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ባለፈው ወር የኖርዝ ወስት ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ባደረጉት ተቃውሞ የአስተዳድሩን ቢሮና የሳይንስ ማዕከሉን ማቃጠላቸው ይታወሳል። ሁኔታው ተረጋግቶ በዛሬው ዕለት ትምህርት መጀመሩ ተነግሯል።

Oromo
Ø የአዲስ አበባን አጎራባች ከተሞችን ወደ አዲስ አበባ ለመጠቅለል የወጣውን ማስተር ፕላን በመቃወም በተለያዩ ቦታዎች ሕዝባዊ ተቃውሞ ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። ለዚህ ሕዝባዊ ተቃውሞ አስፈላጊውን እርምጃ አልወሰዳችሁም፤ ተባባሪ ነበራችሁ በማለት ከወያኔ መሪዎች በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ኦህዴድ ከፍተኛ ባለስልጣኖችን ከፓርቲው የኃላፊነት ቦታ ማባረሩም ይታወሳል። ሰሞኑን ከሚደመጡና ከሚነበቡ ሪፖርቶች ደግሞ የወያኔው ፓርላማ አፈ ጉባዔ አባዱላ ገመዳና የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የተባለው ዲሪባ ኩማ እንቅስቃሴያቸው በወያኔ ደህንነት ራዳር ስር መውደቁ ተዘግቧል። ሁለት ከፍተኛ የአገዛዙ ባላሥልጣናትና የወያኔ ኦህዴድ መሪዎች ከተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ጋር በተያያዘ በዓይነ ቁራኛ ውስጥ እንዲወድቁ መደረጉ ሲታወቅ ወደ ውጭ ሀገራም እንዳይወጡ ፓስፖርታቸውን መነጠቃቸው ተገልጿል። የወያኔ መሪዎች ላጠፉት ህይወትና ላወደሙት ንብረት አገልጋዮችና አሽከሮች የሆኑትን ከፍተኛ የኦህዴድ ካድሬዎችና መሪዎች ጭዳ ለማድረግ መዘጋጀታቸው ቀደም ሲል መገለጹ ይታወሳል
Ø የወያኔ መሪዎች የሥልጣን ዘመናቸውን ለማራዘም እንዲያስችላቸው በውጭ ሀገራት የማግባቢያ ሥራ (የሎቢ ሥራ) ለሚሰሩላቸው ኩባንያዎች የአገሪቱን ሀብት ማዕድኗን እንዲበዘብዙ መንገዶችን ሲያመቻቹ መቆየታቸው ይታወቃል። ከአፋር ግዛት ከሰመራ የሚመጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከአስር ዓመት በፊት ለቀድሞ የወያኔ መሪና ጠቅላይ ሚኒስትር ለመለሰ ዜናዊ ሽልማት የሰጠው ያራ የተባለው የኖርዌይ የማዳበርያ አምራች ድርጅት በአፋር ዳሎል የሚገኘውን የፖታሽ ክምችት እንዲያወጣ ፈቃድ ተሰጥቶታል። ከኖርዌይ ያራ በተጨማሪ አንድ የእንግሊዝ የማዕድን ኩባንያም ይህንኑ የአፋር ማዕድን እንያወጣ ተፈቅዶለታል። ኢትዮጵያ በከርሰ ምድሯ ያላትን ሃብት የወያኔ መሪዎች ከንግድ ሸሪኮቻቸውና ከባለውለታና አጋር ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ጋር በመሆን እየበዘበዙና በባዕድ ሀገርም ከፍተኛ መጠን ያለው ሀብትና ንብረት እያከማቹ መሆናቸው ይታወቃል። የኖርዌይና የእንግሊዙ ማዕድን አውጭዎች በቅርብ ጊዜ ወደ ማዕድን ቁፋሮ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Ø ከጎንደር የሚመጡ ሪፖርቶችና መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ የጎንደር ሕዝብ የወልቃይት ጠገዴ ነዋሪ ያነሳውን የማንነት ጥያቄ በመደገን ለወያኔ አገዛዝ ያለውን ተቃውሞ ባገኘው አጋጣሚና ሁኔታ እየገለጸ መሆኑ ታውቋል። መጋቢት 18 ቀን 2008 ዓም በጎንደር ከተማ በጎንደር ስታዲዩም ለብሔራዊ ሊግ በጎንደር ከነማና በአዲግራቱ ውልዋሎ ክለብ መሃል የእግር ኳስ ግጥሚያ በሚደረግበት ሰዓት የስታዲየሙ ተመልካች በቦታው መሰብሰቡን እንደ አጋጣሚ በመጠቅም ተቃውሞን ሲያሰማ፤ ብሶቱን ሲገልጽ ቁጣውን ሲያሳይ ውሏል። በዕለቱ በስታዲየሙ የነበረው ተመልካች “የወያኔ ኖር ይለያል ዘንድሮ”፤ “ወልቃት ይመለስ”፤ “አማራ ነን”፤ “የትግራይ የበላይነት ያብቃ”፤ “አፈና ይቁም” የሚሉትን መፈክሮችና ልዩ ልዩ የተቃውሞ መዝሙሮችን ሲያሰሙ ውለዋል። ወያኔ ህዝብ እንዳይሰበሰብና ተቃውሞውን እንዳይገልጽ ቢገድብም በስፖርት ሜዳና በጸሎት ቦታ ሳይቀር ሕዝብ ሲሰባሰብ ብሶቱን መግለጽ መጀምሩ ምናልባት ነገ ተሰባስቦ አደባባይ መውጣቱ የማይቀር ነው የሚሉ ታዛቢዎች አሉ።
Ø የወያኔ አጃቢና ሻማ ያዥ የሆኑት የፖሊቲካ ፓርቲ መሪ የተባለት ግለሰቦች ከወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር መነጋገራቸውን ወያኔ አስታውቋል። ይህ በወያኔ መሪዎች ትዕዛዝ በኃይለማርያም ደሳለኝ ፈጻሚነት የተካሄደው የብሔራዊ መግባባት የተባለለት ስብሰባ ከፕሮፓጋንዳ ወፍጮነት ባለፈ እንደ ስሙና አጀንዳው ምንም የተግባር ምላሽ ያልሰጠና ይልቁንም በወያኔ የምርጫ ድራማ ወቅት ስለሚከፈላቸው የገንዘብ መጠን የተጨነቀ ንግግር ሲያደርጉ መዋላቸው ታውቋል። የወያኔ ፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ግን ለመልካም አስተዳድር ችግር ብሔራዊ መግባባት ዋና መሳሪያ ስለሆነ ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ጋር ውይይት ተደረገ ቀጥሎ ከሕዝብ ጋር ይሆናል በማለት ሲያናፉ ሰንብተዋል። የፓለቲካ ታዛቢዎች ወያኔ በአራቱም ማዕዘና የተነሳበትን ተቃውሞና አገዛዙ በቃን በማለት ሕዝብ እያካሄደ ያለውን የአመጽ እንቅስቃሴ ለማዳካም አንዴ ይቅርታ ተጠየቀ ሌላ ጊዜ ስለ መግባባት ንግግር ተደረገ በማለት ለማወናበድና ዕድሜ ለማስረዘም የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑን ይጠቅሳሉ። የወያኔ መሪዎች የሰላምና የዕርቅ ብሩን ከዘጉ ዓመታት ማስቆጠራቸውን ገልጸው በአሁኑ ወቅት የተባለው የብሔራዊ መግባባት ንግግር የተደረገው የወያኔ አጃቢና ሻማ ያዥ ፓርቲዎችን ከቀውሱ ጀርባ የቤት ስራ ሊሰጣቸው ታስቦ መሆኑን ሕዝቡ ይገነዘባል በማለት ተጨማሪ አስተያየት ይሰጣሉ።
Ø ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከአፍሪካ ወደ አውሮፓ አገሮች ለመሰደድ ሙክራ ሲያደርጉ የነበሩት 600 ስደተኞች በየሊቢያ የወደብ ጠባቂዎች የታገዱ መሆናቸው ታወቀ። ስደተኞቹ ከተለያዩ የአፍሪካ አገሮች የመጡ ሲሆን ህጻናትና እርጉዝ ሴቶች እንደሚገኙባችውም ተነግሯል። መቀመጫው ትሪፖሊ የሆነውና የዓለም አቀፍ እውቅና ባያገኝም ራሱን መንግስት ብሎ የሚጠራው አካል ስር የሚገኘው የሊቢያ ባህር ኃይል ስደተኞችን ያገተው ከትሪፖሊ ምዕራብ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሳብራታ በምትባለው ወደብ ነው። ሊቢያ ውስጥ ከ800 000 በላይ ስደተኞች እንደሚገኙ ቀደም ብሎ በፈረንሳዩ የመከላከያ ሚኒስትር የተሰጠውን መረጃ የሊቢያ ባለስልጣኖች የተጋነነ ነው በማለት ውድቅ ቢያደርጉትም ባለፉት ሶስት ዓመታ እስከ 300 000 ስደተኞች ሊቢያ መግባታቸውን አልካዱም። ከአምስት አመት በፊት የጋዳፊ መንግስት ተገርስሶ ሊቢያ ውስጥ ቀውስ ከተፈጠረ ጀምሮ ከፍተኛ ገንዘብ በማስከፈል ስደተኞች ከቦታ ወደ ቦታ የማስተላለፍ ስራ በጣም አትራፊ የሆነ የንግድ ስራ መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ።፡
Ø የሩዋንዳ መንግስት ያለፈበትን የሰው እልቂት ወደ ብሩንዲ በመላክ የአገሪቱ ዜጎች እርስ በርስ እንዲጫረሱ በማድረግ ላይ ነው በማለት የብሩንዲ የገዥው ፓርቲ መሪ ከሰሱ። የፓርቲው ፕሬዚዳንት ፓስካል ንያቤንዳ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ለተባለው የዜና ወኪል በጽሁፍ በላኩት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት የብሩንዲን ዜጎች በወታደራዊ ትምህርት አሰልጥነው ወንድሞቻቸውን እንዲገድሉ ወደ ብሩንዲ ይልካሉ የሚል ክስ ከሰነዘሩ በኋላ የአውሮፓ አገሮችም መሳሪያና ገንዘብ በመስጠት እየተባበሩ ነው ብለዋል። በቅርቡ በሩዋንዳ እና በብሩንዲ መንግስታት መካከል የእርቅ ውይይት እንዲካሄድ ግፊት ስታደርግ የነበረችው የካቶሊክ ቤተክርሲያን ከወቀሳው ያልዳነች ስትሆን የፓርቲው መሪ አሸባሪዎች የሚሏቸውን የአማጽያንን ዓላማ በማራገብ የሀሰት ዜና ያስፋፋሉ በማለት በውጭ ጋዜጠኞች ላይም የከረረ ሂስ ሰንዝረዋል። በብሩንዲ የፖሊቲካ ቀውስ መከሰት ከጀመረ ወደ አንድ ዓመት ገደማ እየተጠጋ ሲሆን እየተካሄደ ባለው የእርስ በርስ ግጭት ከ400 ሰዎች በላይ መገደላቸውና ከ250 000 ሰዎች በላይ ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሰደዳቸው አይዘነጋም።
Ø የጣሊያን ዜጋ የሆነውን ወጣት ገዳዮች ናቸው ተብለው የተጠሩ የቡድን አባሎች በአሰሳ ተገድለዋል በማለት የግብጽ መንግስት መግለጫ መስጠቱ የሚታወቅ ሲሆን በወጣቱ ግድያ ላይ የግብጽ ባለስልጣኖች ያሉበት መሆኑን የሚጠረጥረው የጣሊያን መንግስት የግብጽ ባለስልጣኖችን መግለጫ ያልተቀበለ ከመሆኑም ሌላ በጉዳዩ ላይ የጣሊያን መርማሪዎች በሚገኙበት የምርመራ ቡድን ተመስርቶ ምርመራው እንዲቀጥል የጠየቀ መሆኑ ታውቋል። የግብጽ መንግስት በጣሊያን መንግስት ግፊት ወንጀለኞቹ ተገድለዋል ካለ በኋላ ምርመራው የቀጠለ መሆኑን እንዲሁም ሌሎች ተባባሪዎች መያዛቸውን የሚገልጽ መግለጫ ቢሰጥም የጣሊያን መርማሪዎች ምርመራ ውስጥ ይሳተፉ ለሚለው ጥያቄ ገና መልስ ያልሰጠ መሆኑ ተነግሯል።
Ø ከጥቂት ቀናት በፊት በአይቮሪ ኮስት የወደብ መዝናኚያ ከተማ ለ19 ሰዎች መገደል ምክንያት የሆነው የሽብር ጥቃት ውስጥ ተሳትፈዋል የተባሉ ሁለት የእስላማውያን አክራሪ ድርጅት አባላት በማሊ ውስጥ የተያዙ መሆናቸውን የማሊ የስለላና የጸጥታ ክፍል ባለስልጣኖች ገለጸዋል። ከተያዙት መካከል አንደኛው ሾፌር በመሆን ጥቃቱን ለፈጸሙት ግለሰቦች የትራንስፖርት አገልግሎት የሰጠ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የእርሱ ተባባሪ መሆኑ ተነግሯል። ግንቦት አራት ቀን ግራንድ ባሳም በተባለው የአይቮሪ ኮስት የቱሪስት መዝናኚያ ቦታ ላይ የተካሄደው የሽብር ጥቃት በጥቂት ወራት ውስጥ ከተካሄዱት መካከል ሶስተኛው ሲሆን በሰሜን አፍሪካ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን መውሰዱ ይታወቃል።

Tuesday, March 29, 2016

የኖርዌይ መንግሥት 800 ኢትዮጵያውያን እና 60 ሕፃናትን ወደ ኢትዮጵያ ሊመልስ ነው | VOA

የኖርዌይ መንግሥት 800 ኢትዮጵያውያን እና 60 ሕፃናትን ወደ ኢትዮጵያ ሊመልስ ነው | VOA

የኖርዌይ መንግሥት 800 ኢትዮጵያውያን እና 60 ሕፃናትን ወደ ኢትዮጵያ ሊመልስ ነው | VOA



norway


የኖርዌይ ከለላ ጠያቂዎች ድርጅት ከፍተኛ አማካሪና የሕግ ባለሞያ በፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ያላቸው ስደተኞች ስጋታቸው ተገቢ ነው ይላሉ።
ዋሽንግተን ዲሲ —
ያቀረቡት የጥገኝነት ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘላቸው 800 ኢትዮጵያውያን እና 60 ሕፃናትን የኖርዌይ መንግሥት በግዳጅ ወደ ኢትዮጵያ እመልሳለሁ ማለቱ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደከተታቸው ተናገሩ።
የኖርዌይ ከለላ ጠያቂዎች ድርጅት ከፍተኛ አማካሪና የሕግ ባለሞያ በፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ያላቸው ስደተኞች ስጋታቸው ተገቢ ነው ይላሉ።
ጽዮን ግርማ ስደተኞችንና የሕግ ባለሞያውን አነጋግራ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች።

ፈርዖናዊው የወያኔ አገዛዝ በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ሲደገም ምን ይመስላል?



ከወልቃይት ጠገዴ ብጌምድር፤ ጎንደር ኢትዮጵያ
በ24 አመታት ውስጥ በተለያዩ የኢትዮጵያ አከባቢ ጥቂት የሚባሉ መልካም ለውጦች ቢኖሩም እንኳ ጀግናው የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አይደለም የመልካሙን ለውጥ ሊያጣጥም እንዲያውም በተቀነባበረ ሁኔታ የዛሬ 24 አመት ከነበረበት የህልውናና ኑሮ ብዙ እጥፍ አሽቆልቁሎ ተምዘግዝጎ ወርዶበታል፤ ወያኔ አሰቃይቶታል፤ ህይወቱና አኗኗሩ አመሰቃቅሎበታል፤ ለብዙ መከራና ስቃይ ሞትና እንግልት መታሰርና ደብዛ መጥፋት መሰደድና መሸማቀቅ ዳርጎታል። የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከ1972 ጀምሮ የወያኔ መርዝ የተርከፈከፈበት ህዝብ ነው። አሳዛኙ ነገር ወያኔ የፈጠረው ችግር በሁሉም የኢትዮጵያ መርዙን ከመትፋቱ ጋር ተያይዞ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ወገኑ የየራሱን ህመም ሲያዳምጥ ስለኖረ ከህመም ሁሉ ህመም፣ ከእልቂት ሁሉ እልቂት ሲፈጸምበት፣ በእስራኤላውያን ላይ በኦሽዊትስ ካምፕ በናዚዎች የተቀነባበረው የዘር ማጥፋት በ21ኛው መ.ክ.ዘ በወያኔዎቹ በግልጽና በድብቅ ሲደገም የሚዲያ ሽፋን ስለማይደርሰው ኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ሊያውቁለትና ሃይ ሊሉት አልቻሉም መከራዉን ከ1972 አ/ም ጀምሮ ወገኖቹ ሳይደርሱለት ብቻውን ሲጎነጭ ኖሯል።
welkayet - satenaw
እዚህ ላይ ለማሳሰብ እምፈልገው ዋና ነጥብ በአማራነታችን እየደረሰብን ያለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ ህወሃት በመልካም አስተዳደር ስም ለማስተባበል መሞከር በፍጹም አይቻልም፤ የመልካም አስተዳደር ችግርማ አሜሪካም ውስጥ ቢሆን ይኖር ይሆናል። እኛ አንደላቃችሁ አኑሩን አይደለም እያልን ያለነው። ዋናው ጥያቄያችን የወልቃይት ጠገዴ ህዝብና መሬት አማራ ስለሆነ ወደ እናት አገራችን ወደ ጎንደር ወደ አማራነታችን መልሱን የሚል ነው። ሰላምን ፈልገው ከመለሱን እጅግ ደስ ይለናል ካልሆነ ደግሞ የእነርሱ ፈቃድና ምስክርነት ሳያስፈልገን በራሳችን ራሳችንን አማራነታችንን አስረግጠን እንመልሳለን።በቃ ይሔው ነው!!! ይህ በትግራይ ተስፋፊና ነጻ አውጭ ቡድን፣ በትግራይ ፖሊስ፣ በትግራይ ልዩ ሃይል፣ በአጋዚ ወታደር፣ በትግራይ አስተዳደር አመራሮችና ካድሬዎች ማዳፈን የማይቻል የሚፋጅ ረመጥ ጥያቄ ነው።
የኢትዮጵያ ወገኖቻችን ሆይ ታሪክ የሚመሰክረስው እውነት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብና መሬት የአማራ እንጂ የትግሬ ሆኖ እንደማያውቅ እንድታውቁሉን ነው። የታሪክ መዛግብት ከሚመሰክሩት እውነት በተቃራኒ ታሪኩን በማዛባት እንደማጣቀሻ ከሚያቀርቡ የትግራይን ህዝብ ከማይወክሉ የወያኔ ባንዳ የሆኑ የታሪክ ሙሁር ነን ባዮች ለምሳሌ እንደ ዶክተር ገላውዲዮስ ያሉ የውሸት ታሪክ አጣቃሾች ታሪክ ይፋረዳቸዋል። በነገራችን ላይ ገላውዲዮስ በትግሬኛ የአሜሪካን ድምጽ ሬድዮ ቃለ ምልልስ ሲያደርጉ ያጣቀሱት መጽሓፍ መጽሓፉ ከሚለው በተቃራኒ ስለሆነ ክስ ለመመስረት ዲግሪያቸውን ለማስነጠቅና ሌላም ህጋዊ ቅጣት እንዲወሰድባቸው ሙሁራኖች እየሰሩ ነው። በዉሸት የህዝብን ጥያቄ አዳፍኖ ዘሩን መጨረስ እንደማይቻል ሊማሩ ይገባቸዋል እነዚህ ከንቱና ጠፊ ዘራፊዎች። ሌላው የተማረ ኢትዮጵያዊ ያለ የማይመስላቸው ጠባቦቹና ዘረኞቹ የትግራይን ምስኪን ህዝብ የማይወክሉ ወረበሎች የኢትዮጵያ ህዝብ በቃችሁ ሊላቸው ይገባል። በዚህ አጋጣሚ የታሪክ እውነተኛ ሙሁር አቻምየለህ ታምሩን ስለሚያደርጉት የውሸተኞች ካድሬ ሙሁሮችን ሴራ ማጋለጥ በእጅጉ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ልባዊ ምስጋና እንዳስተላልፍላቸው ይፈቀድልኝ። እንዲሁም ክቡር ልኡል ራስ መንገሻ ስዩም፣ክቡር አቶ ገብረመድህን አር አያ፣ ክቡር አቶ ያሬድ ጥበቡንና ሌሎች ውድ የኢትዮጵያ አንድነት የሚገዳቸውና አጥብቀው የሚሰሩ እውነተኛ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ አብዛኛው ሙሁር በወልቃይት ጠገዴ ዝምታውን መርጦ የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ህዝብ እንደበግ ለመታረድ ወያኔ የውሸት ታሪክን እንደቅመም እየተጠቀመበት ባለበት ስአት እውነተኛ ቃላቸውን ስለሰጡ በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ልዩ ምስጋናየን አቀርባለሁ። ሌሎች ሙሁራን ተሳትፎ እንዲያደርጉ አሁንም ህዝቡ የግረሱልኝ ጥሪውን በማስተጋባት ላይ ነውና እባካችሁ ድረሱልን።ተሳትፎ ያደርጋችሁ ሙሁራንም ሳይለየን የአገራችን ህግ በወያኔ ምክንያት ካልዳኘን ወደ አለማቀፍ ህግ ጉዳያችን ወስዳችሁ ከሞት እንድትታደጉን እርዳታችሁ እንዳይለየን በእግዚአብሔር ስም አደራ እንላለን።
ወያኔ ይህ ሁሉ ስቃይ የሚፈጸምበት ምክንያት ህዝቡ ፍጹም ኢትዮጵያዊነት የሚታይበት ከዘረግኝነት የጸዳ ኢትዮጵያዊ ህዝብ ስለሆነ ነው። ይህም ማለትም እስከቅርቡ ድረስ በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያየ ብሔር ያላቸውን ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በአሁኑ ግዜም ቢሆን ለአፍሪካዉያንም ጭምር ማለትም ሰሜንም ደቡብም ሱዳናዉያን የመሳሰሉ የአፍሪካ ዜጎችም ሰርተው ህይወታቸውን ቀይረውበት በሰላምና በፍቅር ደስ ብሏቸው የሚኖሩበት ከኢትዮጵያዊነቱ በዘለለ በአፍሪካዊነቱም የማይታማ ህዝብና በጣም ለምና በተፈጥሮ ሃብት በኢትዮጵያ ግንባር ቀደም የሆነ አካባቢ በመሆኑ ዘረኞቹ ወያኔዎችና ትግሬዎቹ የተፈጥሮ ሃብቱን ቋመጡት፤ ኢትዮጵያዊ ስሜቱንም አልወደዱትም። የሚገርመው ነገር ህዝቡን አጥፍተው ‘ታላቂቷን ትግራይ’ በመመስረት ከሱዳንና ኤርትራ ጋር እንዋሰናለን አማራም እናጠፋለን ብለው ተነሱ። የሚገርመው ነገር ላለፉት 36 አመታት እነርሱ የሚፈጸሙት ስቃይ አላረካ አልበቃ ብሏቸው በሱዳን ልዩ ሃይሎች ከፍተኛ የአፈናና ግድያ አስፈጸሙበት። የስንቱ የሃገር ጀግናና የአገር አልኝታ ህይወት ቀጠፉት አስቀጠፉት መሰላችሁ። ጀግናው ህዝብም የሚቻለውን ያህል ታገለ ቢሆንም ግን ወያኔ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ ብሗላ ወታደራዊ ሃይሉን አጠናክሮ በመምጣት ቦታውን ተቆጣጠረ ህዝቡንም በተለይም ወንዶችን ልክ እንደፈርዖን እያደነ ማሰር፣ ማሳደድ፣ ማሰቃየትና መዝረፍ ጀመረ በተለይ ከ1983 አ/ም ጀምሮ።

የወያኔ ባለስልጥኖች ከራሳቸው ባሻገር ለየትኛም ጎሳ ዘላቂ ጥቅም አልቆሙም



ኢትዮጵያ ክብሬ
ወንድማችን አቶ ኦባንግ ሜቶ ከጥቂት ቀናት በፊት የትግራይ ነጻ አውጪ ብሎ እራሱን የሚጠራውን ድርጅት ምንነት የተመርኮዘ ጽሁፍ ኢካደፍ ላይ አውጥቶ ነበር። የጽሁፉ ዋና ሀሳብ በጎሳ ተከፋፍሎ ነጻ መውጣት በጭራሽ አንደማይቻል በመጠቆም በአንድነት ለአንድነት መስራት አማራጭ የሌለው የችግራችን መፍትሄ እንደሆነ ማሳየት ነው። ይሄ የማያጠያይቅ እውነታና በጣም የሚደገፍም ሀሳብም ነው። ነገር ግን ወያኔን ያቋቋሙት ሰዎች ጫካ የገቡት የትግራይን ህዝብ ነጻ ለማውጣት ነው አሁንም አላማቸው ይሄንን ብሄረስብ መጥቀም ነው የሚለው አገላለጽ ብዙም አልተመቸኝም።

አንድ እግሩን ኢትዮጵያ አንድ እግሩን ኤርትራ አንፈራጦ በሁለት ቢላ የሚበላ ለእናቱም ይሁን ለአባቱ ሀገር ሙሉ ታማኝነት የሌለው እንደመለስና አቦይ ስብሀት አይነት ራስ ወዳድ የሚቆጣጠረው ድርጅት አላማው የትግራይን ህዝብ ጥቅም ማስጠበቅ ነው ማለት አይጥ የምትቦረቡረውን ቤት ለመሸሸጊያነት ፈልጋው ሳይሆን ቤቱን ላጠንክረው ብላ ነው ስትቆፍረው የምታድር እንደማለት ነው። ትግሬውን ከሌላው አናክሰው የራሳቸውን ጥቅም ለማግበስበስ የሚያሴሩ ለትግራይ ህዝብ ዘላቂ ጥቅም የመቆም ፍላጎቱም ይሁን ብቃቱ የላቸውም። ስለዚህ ወያኔ ለትግሬ የቆመነው የሚለውን የነአባይ ጸሀዬ ማወናበጃ ፕሮፖጋንዳ እኛም በማስተጋባት “አማራው መጣብህ፣ ኦሮሞው ሊፈጅህ ነው፣ እኛ ከስልጣን ከወረድን ወየውልህ” እያሉ የሚያስፈራሩትን ወገናችንን እኛም አስፈራርተን ወደነሱ ጉያ አንግፋው።
እርግጥ ነው ሌላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ሰብእናውንና ታሪኩን እያንቋሸሹ ትግሬውን “ወርቁ ህዝብ ጀግናው ዘር” እያሉ ሰብከዋል። ለተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ መሰረታዊ አገልግሎት እየነፈጉና የኢኮኖሚ አቅሙን እያደቀቁ ትግራይ ላይ የተሻለ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ሁኔታን ፈጥረዋል። ትግራይ ጫት እየከለከሉ ሌላውን ኢትዮጵያዊ ወጣቱ በአጉል ልማድ እየበከሉ ተስፋውን ያጨልሙበታል። ከጽዳት ሰራተኛ እስከ ከፍተኛ ሹመት ለማግኘት መመዘኛው ትግሬ መሆን ብቻ እስኪመስል ሌላውን ወገን ከስራ እያፈናቀሉ በትግራይ ተወላጆች ይተካሉ። ነባር ነጋዴውን በሰበብ አስባቡ ንብረቱን እየቀሙ ከአስመጪና ላኪ ከጅምላ እስከችርቻሮ ንግድ የኛ በሚሉት ወገን አስይዘዋል። ሌላው ኢትዮጵያዊ በኪራይ የሚኖርበት ቤት በላዩላይ እየፈረሰበት ከትግራይ ነኝ የሚለውና ከንሱ በጥቅም ጡት የተጣባ በርካታ ኮንዶሚኒየም እየተሰጠው አከራይቶ ብሩን ያጋብሳል። ኮንሶውና አኝዋኩ አንገቱና እግሩ እንደበግ በሲባጎ ታስሮ ከመሬቱ እየተፈናቀለ መሬቱ ሀገሩን ረግጠው ለማያውቁ የትግራይ ተወላጆች በነጽ ይቸራል። ይሄና ከዚህም የከፋ ብዙ አድሎአዊ ድርጊት በአለፈው 25 አመት መከናወኑ አይካድም። ነገርግን በጭራሽ ሊዘነጋ የማይገብው ነገር ይህ ድርጊታቸው ለትግራይ ህዝብ ከመቆርቆር የመነጨ ሳይሆን የትግራይ ተወላጆችን ከተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በማናከስ ለስልጣን ዘመናቸው መራዘም መስዋእት የሚሆን የትግሬ ጀሌ ጦር ለመፍጠር የተቀመረ መሰሪ ስሌት መሆኑ ነው።
በእኔ እምነት ሁሉም በጎ ነገር ለትግሬዎች እያለ የሚጮኽው የወያኔዎች ፖሊሲ አላማው ትግሬውን ከተቀረው ወገኑ ካናከሱት በኋላ በፍርሀት ሰንሰለት አስረው ሲያበቁ የነአባይ ወልዱ ትንሽ የትግራይ ቤተመንግስት ዘበኛ ማድረግ ነው ምኞታቸው። አላማቸው ያ ባይሆን ኖሮ በእነሱ እኩይ ስራ ምክንያት “የኛ ወርቅ ህዝብ” የሚሉትን ህብረተሰብ በመላው ኢትዮጵያዊ ሰብሉን እንደሚያጠፋበት ተምች እንዲጠላ የሚያደርግ ለከት ያጣ የዘረኝነት ፖሊሲ አያላራምዱም ነበር። ይህ ድርጊታቸው ትግሬ ወገኖቻችን በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል በሰላም ተንቀሳቅሰው እንዳይሰሩና በሰላም እንዳይኖሩ ሊያደርጋቸው እንደሚችል ጥርጣሬ የለኝም። ለዚህ ነው እነሲዩም መስፍንና አቦይ ስብሀት ጫካ የገቡትም ሆነ ከጫካ መልስ ኢትዮጵያ ላይ የሚያኪያሂዱት ጦርነት ጸረ ትግሬ እንጂ የትግሬን ዘላቂ ጥቅም የሚያስጠብቅ አይለም የምለው። የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ትግል የግፋቸው ዘመን ማለቁ እንድማይቀር ጠንቅቀው ያውቃሉ። ታዲያ ያቺ ለህዝቡ መልካም ለእነሱ ክፉ የሆነች ቀን መምጣት የሚያደርጉት ዝግጅት አንዱ አካል የሆነው ትግራይ የምትባል የግዞት ሀገር በመፍጠር እንደ ቤት ሰርሳሪዋ አይጥ የዘረፉትን ሀብት እየበሉ የሚሞቱበት መደበቂያ ጉድጓድ ነው መማስ ነው። ይሄ ጉድጓድ ለረጅም ጊዜ መብቱን በተገፈፈውና ንብረቱን በገፍና በግፍ በተዘረፈው ህዝብ አመጽ ሲደረመስ ለአንድ ጎሳ አባልነቱና ለጊዜያዊ ጥቅም ሲል ሀገሩንና ወገኑን በመክዳት ለወያኔ ባለሀብቶች ጠባቂነት የተደረደረውን ደሀ ጀሌ ሁሉ ጠራርጎ ይፈጀዋል። የእኛ ስራ መሆን ያለበት ይሄ መአት እውን እንዳይሆን የትግራይ ተወላጆችም በጭፍን የወያኔ ደጋፊ ከመሆን እንዲቆጠቡ መምከር እኛም ሁልም ትግሬ በፈቃዱ የወያኔ ክፉ ሥራ ተጠቃሚ ነው ብለን ከማሰብ መቆጠብ ነው።
ሌላው የእነ አቦይ ስብሀትና አርከበ እቁባይ ከስልጣን በኋላ እቅድ ከደሀው ጉሮሮ ሲዘርፉት የኖረውን ሀብት በባእድ ሀገር መደበቅ ነው። ለዚህ በዝርፊያ ላካበቱት ሀብት አንዱ ምንጭ በትግሬ ማቋቋሚይ ስም ያላቸውና አንድም ቀን ሂሳቡ ተመርምር የማያውቀው ኤፈርት ነው። እነኚህ ባለስልጣኖች እውን ለትግራይ ህዝብ የቆሙ ቢሆን እነአዜብ ጎላና ሲዩም መስፍን የግል ንብረታቸው ያደረጉት ድርጅት ንብረት ለትግራይ ህዝብ ግልጽ በሆነ ነበር። ደግሞስ ትግራይ እስከመቼ ነው በተቀረው ኢትዮጵያዊ ህዝብ አጥንት መልሳ የምትቋቋመው?
መዘንጋት የሌለብን ሌላው ሀቅ እንመለስ ዜናዊ የደረሱበት የስልጣንና ሀብት ደረጃ የደረሱት በርካታ አብረዋቸው ጫካ የነበሩትን “ታጋይ” ትግሬዎች በለሊት አሳርደውና ከነህይወታቸው ጉድጓድ ውስጥ ቀብረው በመግደል መሆኑን ነው። የውጪ ድጋፍ ለማግኘት ሲሉም ሀውዜን ላይ የራሳቸውን ህዝብ በቦንብ አሰድብድበዋል። በተራበው ህዝብ ስም የሚመጣላቸው ገንዘብና እህል መጠኑ እንዲጨምር በመፈለግ ብቻ ረሀብተኛው ድጋፍ ወደሚያገኝበት ስፍራ እንዳይሄድ አግተውት ስንቱን ለመከራና ሞት ዳርገውታል። በብዙ ሺህ የሚቆጥር የትግራይ ተወላጅ በጠኔ ሲረግፍ በእነሱ ስም በተሰበሰብ ገንዘብ የወያኔ ባለሟሎች ስንቴ ድል ያለ ፓርቲ ደግሰው በውስኪ ተራጭተዋል። ስንቱን ከወያኔ በአስተሳሰብ የተለየ ትግሬ ደርግ ውስጥ አሰርገው ባስገቧቸው ካድሬዎቻቸው አማካኝነት ለነሀምሳ አለቃ ለገሰ አስፋውና ለደህንነቱ ተስፋዬ ወልደስላሴ ሀገር ከሀዲዎች ናቸው እያሉ በመንገር አሳስረዋል አስገድለዋል። መሀል ሀገር ከገቡስ በኋላ በደም በአጥንታቸው ወያኔን ተሸክመው አዲስ አበባ ያስገቡ ስንት አካለ ስንኩላን የወያኔ ወታደሮች እንደቆሻሻ ተጠራርገው ተሸኝተዋል። ስንቱስ ተገድሏል። ሌላው ይቅር መለስን ሳይቀር ጠመንጃ አያያዝ ያስተማሩት አቶ አሰግድ ገብረሰላሴ ከነመለስ የተልየ አስተሳሰብ ስላላቸው አይደል የወያኔን ጭካኔ መቀበል ከሳቸው አልፎ ለልጆቻቸው የተርፈው። እንዲህ አይነት በርካታ ምሳሌዎችን ስናስታውስ የወያኔ ባልስልጣናት ከራሳቸው ባሻገር ለማንም ጥቅም አለመቆማቸው ፍንትው ብሎ ይታየናል። ሌላውን ተጠቃሚ ካደረጉም የእንሱን የስልጣንና ዘረፋ ዘመን እንዲራዘም በማድረግ እንዲያግዟቸው በማሰብ ብቻ ነው።
በአለም አቀፍ ደርጃ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩትም በአብዛኛው ብሶት አለብን ብለው በጎሳና ሀይማኖቶ ጥላ ስር የሚነሱ ስብስቦች መሰረታዊ አላማቸው በህብረተሰብ ላይ የሚደርስን በደል መቅረፍ ሳይሆን የራሳቸውን ስግብግብነት ማርካት እንደሆነ ነው። ሴራሊዮንን ብንመለከት የኮንጎ ሪፕብሊክን ብንቃኝ አሁን ደግሞ በእስልምና ስም የተሰባሰቡትን ቦኮ ሃራምም ይሁን አይስስ ቡድኖች ብናይ ድጋፍ ለማሰባሰብ ይረዳቸው ዘንድ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮችን ሲገድሉ ቢታዩም ከማንም በላይ በብዛት የሚያሰቃዩት፣የሚያርዱትና በታንክ የሚደፈጥጡት ሀይማኖታችሁን ለማስከበር ነው የቆምነው የሚሏቸውን እስላሞች ነው ።
ለምሳሌ ሴራሊዮን ውስጥ ከሰባ አምስት ሺህ ሰው በላይ የሞተበትና ከግማሽ ሚሊዮን የማያንስ ሰው ስደተኛ ሲሆን የሀገሪቱ ህዝብ ግማሽ የተፈናቀለበት ጦርነት ዋና ተዋናይ እራሱን የተባበሩ አብዮታዊ ግንባር ብሎ የሰየመየው ሀገርበቀል አማጺ ቡድን ነበር። ይህ ቡድን ነበር ህጻናትን ሳይቀር በሱሰኛ እጽ እየበከለ የራሳቸውን ቤተሰቦች ጭምር እጅ በቆንጨራ እየቆረጡ አዛውንትና ህጻናት ሴቶችን እንዲደፍሩና እንዲገድሉ ያደረጉት። ይህን ሲያደርጉ ዋና አላማቸው ልጆቹ የራሳቸውን ቤተሰብ ካዋረዱን ከገደሉ ብኋል የሚሸሹበት ስለማይኖራቸው የአረመኔዎቹ የሽፍታ መሪዎች ታማኝ አገልጋይ እንዲሆኑ ማድረግ ነው። የመሪዎቹ የነፎዴ ሳንኮህ ብቸኛ አላማቸውም የሀገሪቱን የአልማዝ ሀብት መቆጣጠር ነበር። ይህን አላማቸውን ለማሳካት ሲሉ ስፍር ቁጥር የሌለው ወገናቸውን ለስቃይና ለሞትና ስደት ዳርገዋል። ወያነዎችም ትግሬውን ከተቀረው ህዝብ የሚያጣሉት የምሸሽበት የለኝም ብሎ እነሱ ግደል ሲሉት የሚገድል ዘበኛ እንዲሆን ለማድረግ ነው።
ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎንና ደቡብ ሱዳንን እንደ ተጨማሪ ምሳሌ ብንመለከት ወገን በወገኑ ላይ ጠብመንጃና ቆንጮራ አንስቶ እንዲተላለቅ የሚቀሰቅሱትና የሚያናፍሱት አላማችን የህዝባችንን ጥቅም ማስጠበቅ ነው ይላሉ እንጂ እውነተኛ ፍላጎታቸው የሀገራቸውን ጥሬ ሀብት መቆጣጠር መሆኑን አይናገሩም። ያንን ከተናገሩ ብዙ ድጋፍ ስለማያገኙ። የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት ባህሪይም ከዚህ የተለይ አይደለም።
የወያኔና ኢሀዴግ አባላት እያንዳንዳቸው የቆሙት ለራሳቸው የግል ጥቅም ብቻ ነው። ወገን የሚሉት የላቸውም። ለዚህም ነው የተለያየው ብሄር ተጠሪ ነኝ የሚለው የወያኔ ጀሌ በሙሉ ጨካኙን አጋዚ መንገድ እየመራ ወዳጅ መስሎ በዘር የሱ ወገን የሆነዉን ሁሉ የሚያስፈጀው። የወያኔ ስርአት ለማንም ደህንነት የማይጨነቅና ስልጣን ላይ ያሉትን ብቻ በሀብትና ዝና ለማግነን የሚሰራ የዘራፊ ቡድን እንጂ የየትኛውንም ብሄረሰብ ዘላቅ ጥቅም አስጠባቂ አይደለም።
ይሄ የወያኔ ተፈጥሮና ባህሪይ ለኛ የሚሰጠን ግንዛቤ ማንኛውም በዘርም ይሁን በሀይማኖት አመካኝቶ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ቡድን አላማው ህዝባዊ ሳይሆን ግላዊ መሆኑን ነው። ሁሉም ሰው የሚፈልገው በተረጋጋ ሰላም ያለፍርሀት ሰርቶ በደስታ መኖርን ነው። ከጎረቤቱ ጋር የጎሪጥ እየተያየ ሳይቀድመኝ ልቅደመው በሚል የፍርሀት መንፈስ ተውጦ ደስታና ብልጽግናን ማግነት ከቶውንም አያልም። ስለዚህ ለህዝብ ጥቅም ቆመናል የሚል ማንኛውም ስብስ አንድን ህብረተሰብ ከሌላው ጋር በዘርና ሀይማኖት ሰበብ ማናከስ አላማው ሊሆን አይገባም። ይህ ማለት የባህልና የቋንቋ ልዩነታችን ይከበር ብሎ መጠየቅ መጥፎ ነው ለማለት አይደልም። ልዩነታችን ለጸብ ሳይሆን ለፍቅርና ለመደጋገፍ እንዲረዳን ልንጠቀምበት እንችላላን። ከነልዩነታችን ተከባብረን በአንድነት መኖር እንችላላን።
በመጨረሻም ከልምድ ጠንቅቀን የምናውቀው የአንድ እናትና አባት ልጆች ጠላት ሁነው ሲጋደሉ ፍጹም ባእድ የሆነው ሰው በሰው ልጅነቱ ብቻ አዝኖ ሌላውን ለመርዳት እራሱን እንደሚሰዋ እናውቃለን። በአጭሩ የአንድ ጎሳ ወይንም ሀይማኖት አባል መሆን ብቻውን ለወዳጅነት ለመታመንም መሰረት ሊሆን አይችልም። በደም ግማሽ ኤርትራዊ በአንዳንድ ድርጊቱ ከኤርትራዊያን በላይ ኤርትራዊ ይባል የነበረውና ወላጅ እናቱም ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንደትገነጠል ድምጻቸውን የሰጡት ባለራዕዩ መለሰ ዜናዊ “የአይናችሁ ቀለም ካላማረኝስ” እያለ ኤርትራዊያንን ከኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር ሲያባርር ተባራሪዎቹን እያለቀሱ የሸኙትና ንብረታቸውን በአደራ የጠበቁላቸው የተለያየ ጎሳ አባል የሆኑ ኢትዮጵያውያን ናቸው።

በኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ ላይ የመከረው ስብሰባ ተጠናቀቀ




Vision-Ethiopia-22

ኢሳት (መጋቢት 19 ፥ 2008)

በቪዥን ኢትዮጵያና ኢሳት በዋሽንግተን ዲሲ ጆርጅ ታውን መሪየት ሆቴል ከማርች 26-27 2016 የተዘጋጀውና በኢትዮጵያ የወደፊት ሁኔታ በለውጥ፥ ዲሞክራሲና፣ የብሄራዊ አንድነት ላይ የሚመክር ስብሰባ በስኬት መጠናቀቁን የስብሰባው አዘጋጆች ገለጹ። በስብሰባው የኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ የሚመለከቱ ጉዳዮች የተዳሰሱበት ሲሆን በርካታ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ምሁራን፣ የሲቢክ ድርጅቶች እና የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጥናታዊ ጽሁፎቻቸውን ያቀረቡበትና የተሳተፉበት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
ፕሮፌሰር ጌታቸው በጋሻው የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በኮንፈረንሱ አንኳር አንኳር አገራዊ ጉዳዮች እንደሚነሱ ሃሳባቸውን አንስተዋል። በኢሳትና በቪዥን ኢትዮጵያ ትብብር ተዘጋጅቶ በነበረው በዚሁ ኮንፈረንስ ከተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ምሁራን በኢትዮጵያ ወቅታዊና የወደፊት አቅጣጫ ዙሪያም ሰፊ ውይይትን አካሄደዋል።
ከተለያዩ የሲቪክና የሰብዓዊ መብቶች እንዲሁም የእምነት ተቋማት የተወከሉ ተጋባዥ እንግዶች በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና የተረጋጋ ሰላምን ማምጣት በሚቻልበት ዙሪያ የመከሩ ሲሆን፣ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመፍጠርም ብሄራዊ እርቅና ብሄራዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ሃገራትን ተሞክሮ በዋቢነት በማንሳት ለታዳሚ ገለጻን ያደረጉት ፕሮፌሰር አቻምየለህ ደበላ፣ በአህጉሪቱ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ መንግስት አይነት ምርጫ አድርጎ መቶ በመቶ አሸንፌያለሁ ብሎ ያወጀ መንግስት እንደሌለ አውስተዋል።
በጋና በናይጀሪያና በሌሎች ሃገራት በትምህርት ቆይታቸው የታዘቧቸውን ፖለቲካዊ ጉዳዮች ለኮንፈርነሱ ያካፈሉት ፕሮፌሰር አቻምየለህ፣ በሌሎች የአህጉሪቱ ሃገራት ፖለቲካዊ ለውጦች መታየት ቢጀምሩም በኢትዮጵያ ያለውን አካሄድ ግን ገና ብዙ የሚቀረው እንደሆነም አስረድተዋል።
በኒው ዮርክ ሲቲ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር ጆን ሀርብሰን በበኩላቸው, በኢትዮጵያ ከ1960 የአብዮት ፍንዳታ ጀምሮ ሃገሪቱን ዴሞክራሲያዊ ሊያደርጉ የሚችሉ አራት እድሎች ሳይሳኩ መቅረታቸውን ገልጸዋል።
በግንቦት 1977 የተካሄደው ብሄራዊ ምርጫ ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ ትግሎችን ያወሱት ፕሮፌሰር ሀርብሰን፣ ከኢትዮጵያ ጋር በሽብርተኛ ዙሪያ ትብብር ያላት አሜሪካ በሃገሪቱ ዴሞክራሲ እንዲያብብ ትብብር ማድረግ እንዳለባት ባቀረቡት ገለጻ አመልክተዋል።
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባት የስራ አስፈጻሚ አባል የሆኑት ሌንጮ ባቲ፣ በመንግስት የሚፈጸሙ የኢሰብዓዊ ድርጊቶች በዝርዝር ካስረዱ በኋላ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት በመሆን በስልጣን ላይ ያለውን ኢህአዴግ መስወገድ እንዳለበት ተናግረዋል።
በሃገሪቱ እየተፈጸሙ ስላሉ ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ሰፊ ሪፖርትን ያቀረቡት አቶ ነዓምን የኢህአዴግ መንግስት ፌዴራላዊ፣ ዴሞራሲያዊ ወይም ሪፐብሊክ ተብሎ ሊፈረጅ እንደማይችል አክለው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የወደፊት ጉዳይ የሚመክረው ስብሰባ እሁድ እለትም በዚሁ በማሪየት ሆቴል ቀጥሎ የዋለ ሲሆን፣ በትግሉና በግጭት አፈታት እና ለዲሞክራሲ፣ አንድነት ዙሪያ ሴቶች የሚጫወቱት ሚና በሚል መድረክ ውይይት ተካሄዶበታል።
በሃዋርድ ዩንቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ የሆነችው ወ/ሪት ኤልሳቤጥ ላቀው ወደአሜርካ የፈለሱ አፍሪካውያን ሴቶችን ጉዳይ ከኢትዮጵያውያን ትግል አንጻር ትንተና ሰጥታለች። በመቀጠልም በኖርዌይ ሃገር የሚኖሩት ወ/ሮ ሰዋሰስ ጆሃንሰን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲንና ነጻነትን በኢትዮጵያ ለማምጣት በአንድነት መታገል እንዳለባቸውና ካወሱ በኋላ፣ አዲሲቷን ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ በመጀመሪያ እርቅ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል። በመቀጠል የተናገሩት በፍራንክፈርት የሚኖሩት የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ወ/ሮ አሳየሽ ታምሩ ሲሆኑ፣ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥ ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያውያን ሴቶች አጋርነታቸውን ማሳየት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ወ/ሮ አሳየሽ፣ “ለልጆቻችን ማውረስ ያለብን ነጻነትን ነው” ሲሉ ተደምጠዋል። በዚህ ፓነል መጨረሻ ላይ የተናገሩት በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ሴቶች የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ወ/ሮ ወሰን ደበላ ሲሆኑ፣ 51% የሚሆነውን የኢትዮጵያን የሚሸፍኑት ሴቶች ቢሆኑም፣ በአገራዊ ጉዳይ ተሳትፏቸው ግን እጅግ ዝቅተኛ ነው ብለዋል። ወ/ሮ ወሰን የኢትዮጵያ ሴቶች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል። ፓነሊስቶቹ የኢትዮጵያ ሴቶች ድምጽ እንዲሰማ ቪዥን ኢትዮጵያና መድረኩን በማመቻቸታቸው አመስግነዋቸዋል።
እሁድ ከሰዓት በኋላ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ለመዳሰስ ስብሰባ ተካሄዷል። ስብሰባውን የመሩት አቶ ግዛው ለገሰ ናቸው። በመጀመሪያ ጥናታዊ ጽሁፋቸውን ያቀረቡት አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሲሆኑ፣ በፓርቲዎችና በማህበረሰብ (ኮሚኒቲ) አባላት መካከል መተባበር አለመኖር ለለውጥ ከፍተኛ እንቅፋት እንደሆነ ተናግረዋል። ለአጭር ይሁንም ለረጅም ጊዜ የጋራ ግብ በእነዚህ የማህበረሰብ አባላትና ፓርቲዎች መካከል በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። ዶ/ር መስፍን አብዲ በመሬት ጉዳይ ዙሪያ ትንተና ሰጥተዋል። በህወሃት አገዛዝ መሬት የገበሬዎች ሆኖ እንደማያውቅና ከመሬት ይዞታ ጋር የተያያዙ አያሌ ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንዳሉ ተናግረዋል።
አሁን ያለችዋን ኢትዮጵያ በማስመልከትም ያለፈው ታሪክ ሆኖ ያለፈ በመሆኑ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ሁሉም በእኩል አይን የሚታይባት አገር መሆን ይኖርባታል ብለዋል። ከዚህ ጋር በማያያዝም ኦሮምኛ የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። የኦሮሞና የአማራ ልሂቃንም በሁለቱ ህዝቦች መካከል መተማመን እንዲኖር እንዲሰሩ እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
በመሬይ ስቴት ዩንቨርስቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ሰይድ ሃሰን በመሬት ነጠቃና ሙስና ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል። ፕ/ር ሰይድ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሙስና በአለም ላይ ከታዩት ሙስናዎች ለየት ያለ ነው ብለዋል። መሬት የስልጣን ምንጭ በመሆኑ የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት መሬት ነጠቃውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተንብየዋል። ሁሉም የኢትዮጵያ ተደራሽ አካላት ይህ ዘርፈ-ብዙ ውስብስብ ችግር ለመፍታት ተቀራርበው መነጋገር እንዳለባቸው ተናግረዋል።
በኬተሪንግ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር እዝቅኤል ገቢሳ፣ የዲሞክራሲ፣ የእድገት፣ የሰብዓዊ መብት፣ የሰላም ማስፈን እሴቶችን ከውስጣችን መመልከት እንዳለብን የሚተነትን ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ዲሞክራሲ የምትሻገርበትን ብዙ እድሎችን ያጣችበትን አጋጣሚ የተነተኑት ፕሮፌሰር እዝቅኤል፣ ኢትዮጵያውያን ህወሃት ኢህአዴግን ከማስወገድ ባለፈ የወደፊት እቅድ ሊኖራቸው እንደሚገባ አስረድተዋል። ፕሮፌሰር እዝቅኤል በገዳ ስርዓትና በኦሮሞ እሴቶች ላይ ትንተና ሰጥተዋል።
“ከዚህ በኋላ ወዴት? ያልተመለሱ ጥያቄዎች!” የሚለው የመጨረሻው ስብሰባ የተመራው በኮሎራዶ ሜትሮፖሊታን ስቴት ዩንቨርስቲ መምህር በሆኑት በፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽ ነው። ለዲሞክራሲ፣ ለለውጥና ለአንድነት ምን መደረገ እንዳለበት የመከረው ይኸው ስብሰባ፣ ኢትዮጵያ በአስቸኳይ ለውጥ የሚያስፈልጋት አገር እንደሆነች ተናግረዋል። የኢትዮጵያውያንን ህይወት የዳሰሰ በምስል ያሳዩት ፕሮፌሰር ሚንጋ፣ ኢትዮጵያ የሰላም፣ የዲሞራሲና የብልጽግና አቅጣጫ (Roadmap) ያስፈልጋታል ብለዋል። በመሆኑንም ከኤርትራ ጋር ያንዣበባት የጦርነት አደጋ፣ በኦሮሚያ፣ ኮንሶ፣ አማራ፣ ሶማሌ እና ጋምቤላ አካባቢዎች የሚታየው ግጭት ኢትዮጵያን ከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደከተታት ተናግረዋል። ከህወሃት/ ኢህአዴግ መወገድ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚተገበር አቅጣጫ መቀመጥም እንዳለበት ፕሮፌሰር ሚንጋ ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር ተሾመ ከበደ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ብጥብጥ የመንግስት የስልጣን ምንጭ እንደሆነ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ፕሮፌሰር ተሾመ ኢትዮጵያ የዲሞክራሲ እሴቶችን የምታከብር፣ በሉዓላዊነቷ የማትደራደር አገር እንድትሆን ማድረግ ሃላፊነት እንዳለብን ለታዳሚው ተናግረዋል። ሕወሃት/ኢህአዴግን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ እንዲደመሰስ ማድረግ ሳይሆን ዲሞራሲያዊ እሴቶችን እንዲቀበል ማስገደድ እንዳለብን ተናግረዋል። “አገራችን ችግር ላይ ናት፣ የእኛን እርዳታ ትሻለች” ሲሉ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል።
ከዚህ ቀጥሎ የተናግሩት የህግ ባለሙያና የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባት አባል የሆኑት ዶ/ር በያን አሶባ ሲሆኑ፣ ያለፉትና የአሁኑ አምባገነን መንግስታት በህዝቦቻችን ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን ተናግረዋል። ሌሎች ኢትዮጵያውያን በኦሮምያ እየተከሰተ ያለውን ህዝባዊ እንቅስቃሴ በጥርጣሬ መመከታቸውን ትተው እንዲደግፉት ጥሪ አቅርበዋል።
በካሊፎርኒያ ግዛት ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማሪያም የአምባገነን መንግስታት ባህሪ ነገሮችን መደበቅ ነው ብለዋል። በመሆኑም ህወሃት ኢህአዴግ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳይታወቅበት ኢሳትን በብዙ ሚሊዮን ብር በመክፈል በተደጋጋሚ በሞገድ ለማገድ መሞከሩን ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ሆኖም ህወሃቶች ለሰሩት ጥፋት ሁሉ ተጠያቂ የሚሆኑበት ጊዜ ሩቅ እንዳልሆነ ለተሰብሳቢው ገልጸዋል። ለዲሞክራሲና ለእኩልነት የሚደረገው ትግልም ህወሃት/ወያኔ ኖረም አልኖርም መቀጠሉ አይቀሬ መሆኑን አስረድተዋል። አዲስ አቅጣጫ የሚያመላክት ህገ-መንገስትም መዘጋጀት እንዳለበት ተሰብሳቢውን መክረዋል።
በመጨረሻ የቀረቡት በዳይተን ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ ናቸው። የተሻለው አቅጣጫ አሁን ያለውን በዘውግ የተከለለውን አስተዳደር መከተል መሆኑን አስመረው፣ ኢህአዴግ ቢወገድም የዘውግ ጥያቄ በቀላሉ የሚጠፋ አለመሆኑን ገምተዋል።
ከቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፎች በሁላ በርካታ ጥያቄዎች ለተሰብሳቢዎች የቀረቡ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ከመድረክ መልስ ተሰጥቶባቸዋል። አንዳንድ ያልተመለሱ ጥያቄዎች ወደ ፊት በሚካሄዱ ስብሰባዎች እንደሚነሱ ለማወቅ ተችሏል።

Monday, March 21, 2016

ኖርዌይ ኢትዮጵያውያን የፓለቲካ ጥገኝነት ጠያቂዎችን በግዳጅ ወደ ሀገራቸው ለመመሰስ ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ያደረገችውን ስምምነት የሚቃወም ታላቅ ሰልፍ በታላላቅ የኖርዌይ ከተሞች ተካሄደ!!


0328351be332f7a63ab778c6aecd8c3f_M
ኢትዮጵያውያን በስደት ከሚኖሩባቸው የተለያዩ የአውሮፓና ስካንዴኔቪያን ሀገሮች አንዷ የሆነችው ኖርዌይ ስትሆን በኖርዌይ ሃገር ቁጥራቸው አነስተኛ የማይባል ኢትዮጵያውያን የፓለቲካ ስደተኞች ይገኛሉ። እነዚህ ስደተኞች ከሌላው ሀገር ለየት የሚያደርግ ጠንካራ የፓለቲካ አቋም ያላቸው መሆኑም ይታወቃል። ስደተኞቹ በተለያየ ጊዜያት የገዢውን ፓርቲ ብልሹ አስተዳደር የሚያጋልጡ የፓለቲካ ስራዎችን ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወሳል።
ሆኖም ግን የኖርዌ መንግስት እ.ኤ.አ በ2012 ከቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ መለስ ዜናዊ ጋር በኖርዌይ የሚኖሩ ጥገኝነት ጠያቂዎችን አስገድዶ ወደ ሃገር ለመመለስ የሚያስችል ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። ሆኖም ግን ይህ ስምምነት በተለያዩ ምክንያቶች ተግባር ላይ ሳይውል ቀርቷል። ኖርዌይ በድጋሚ አሁን በያዝነው አመት በፌብርዋሪ ወር እንደገና ስደተኞችን አስገድዶ ወደ ሀገር የመመለሱ ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን ከውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ቴዎድሮስ አደሃኖም ጋር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን በኖርዌይ የሚገኙ ታላላቅ የዜና አውታሮች ሰሞኑን ሲዘግቡ ሰንብተዋል።

ይህንኑ ስምምነት አስመልክቶ በኖርዌይ የሚገኘው የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ማህበር ስምምነቱ ትክክል እንዳልሆነ ተቃውሞውን ለመግለፅ በማርች 15፣ 2016 ሰልፍ አዘጋጅቶ ነበር። ይህ የተቃውሞ ሰልፍ በሶስት ታላላቅ የኖርዌይ ከተሞች፦ በኦስሎ፤ በበርገን እና እስታቫንገር ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በታላቅ ተቃውሞ ተካሂዷል። ስደተኞቹ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በተለይ በቅርቡ በሀገራችን በአደባባይ እየተገደሉ ያሉ ወገኖቻችንን የያዙ ምስሎችንና የኖርዌይ ዜግነት ያላቸውና ከደቡብ ሱዳን ታፍነው በኢትዮጵያ እስር ቤት እየማቀቁ ያሉንት የአቶ ኦኬሎ አኳይ ፎቶግራፍ እንዲሁም የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ፎቶግራፎች በመያዝ ስለነሱም አያይዞ ለኖርዌይ ፓርላማ ተወካይ ጥያቄ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ሁኔታ እየታወቀ ሰዎች በየሰከንዱ እየተገደሉ ባለበት ወቅት ሀገሪቱ በብዙ አቅጣጫ የህዝብ አመፅ ባለበትና ገዢው ፓርቲም ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ሰዎችን እየገደለና እያሰረ ባለበት ጊዜ ስደተኞችን አስገድዶ ለመመሰል ስምምነት ማድረጉ ለምን እንዳስፈለገ፤ እንዲሁም የኖርዌይ መንግስት ለኖርዌጅያን ዜጎች በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች መዘዋወር አደገኛ መሆኑን መግለጫ እየሰጠ ባለበት ሁኔታ የፓለቲካ ስደተኞችን አሳልፎ መስጠት ሰብአዊነት የጎደለውና የስደተኛ መብት ህግን የሚጥስ መሆኑን ኢትዮጵያውያኑ በሰልፉ ላይ ተናግረዋል።

በሰልፉ ላይ ከተለያዩ ድርጅቶች የተወከሉ ተወካዮች ንግግር ያደረጉ ሲሆን በኖርዌ የስደተኛ መብት ተከራካሪ የሆኑ የኖርዌጅያን ድርጅቶችም በሰልፉ ላይ ተገኝተው በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደሚያውቁና ስምምነቱንም እንደማይደግፉ አቋማቸውን ገልፀዋል። በመጨረሻም የስደተኛ ማህበሩ ሊቀመንበር የስደተኛውን የአቋም መግለጫ በማንበብ ሰልፉ በተያዘለት ሰአት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
ኢትጵያ ለዘላለም ትኑር
የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዌ!

Friday, March 11, 2016

ነገሮች አዲስ የሚሆኑት፣ በእኛ ትናንትን መርሳት – ይገረም አለሙ



ሰሞኑን  በደቡብ ኢትዮጵያ በሚኖሩ ዜጎች ላይ የተፈጸመን የባሪያ ፍንገላን ዘመን የሚያስታውስ  ኢሰብአዊ ድርጊት  የሚያሳይ ፎቶ  በማህበራዊ ድረ-ገጽ ተሰራጭቶ አጀኢብ ጉድ ብለናል፡፡ ነገሩ ትናንትን እየረሳን ዛሬ ለሚያጋጥመን ነገር አዲስ እየሆንን ጉድ ጉድ ለምንለው  ለእኛ ነው እንጂ አዲስነቱ ለወያኔ ከበርሀ ጀምሮ አብሮት የኖረ ተግባሩ ነው፡፡
አይደለም ሥልጣኑን ሊነጥቁት በተቃውሞ የተሰለፉ፣  እኩይ ድርጊቱን እያጋለጡ ማንነቱን ጸሀይ የሚያሞቁ ፣ ሀሳብ እቅዱን እየተቃወሙ ጉዞውን የሚያደናቅፉ ቀርቶ የህውሀት አባል ሆነው ስህተት የጠቆሙ የዓላማቸውን መስመር መሳት የገለጹ የመሪዎቹን እኩይ ተግባር የነቀፉ ወዘተ ምን እንደተፈጸመባቸው የአይን ምስክር የሆኑ ሰዎች ሲናገሩ ሰምተናል ጽፈው አንብበናል፡፡ ባዶ ምንትስ ይባሉ በነበሩት እስር ቤቶች በውልደታቸው ትግሬ በድርጅታቸው ህውኃት የነበሩ ዜጎች ሳይቀሩ ምን አይነት ኢሰብአዊ ድርጊት አንደተፈጸመባቸው እነ ገብረ መድህን አርአያ ደጋግመው የነገሩን ነው፡፡ ዛሬም በተለያየ የሥልጣን ስም ተቀምጠው አረመኔያዊውን ድርጊት የሚፈጽሙ የሚያስፈጽሙት እነዛ የበርሀው ሲኦል እስር ቤቶች ሀላፊዎች የነበሩቱ ናቸው፡፡



12801147_966036103443554_4958790932868175941_n
ለሥልጣናቸው የሚያሰጋ፣ ያሰቡ ያቀዱትን ተፈጻሚ እንዳያደርጉ አንቅፋት የሚሆን፣ ማንም ሆነ ከየትም  ከማጥፋት የማይመለሱት ወያኔዎች (በተለይም አቶ መለስ) ዘር ሀይማኖት ሳይለዩ አስሮ ማሰቃየቱን አፍኖ መሰወሩን ገድሎ መጣሉን ብሎም ርስ በርስ ማገዳደሉን አብይ ተግባራቸው አድርገው የኖሩ ለመሆናቸው  ብዙ እጅግ ብዙ ማረጃዎችን መዘርዘር ይቻላል፡፡
የህውኃት ቀኝ እጅ የነበረው የደህንነቱ ሹም ክንፈየአግልግሎት ግዜው ሲያበቃ እንዴት እንዳስገደሉትና የግድያ ትዕዛዙን በፈጸመው የዋህ ታዛዥ ላይ ያደረጉትን የምናውቅ  በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ የሚፈጽሙት አረመኔያዊ ተግባር ለምን አዲስ አንደሚሆንብንና እንደሚገርመን  ራሱ የሚገርም ነው፡፡ ለህይወታቸው መድህን ለሥልጣናቸው ዘብ ሆነው የኖሩ ሰዎቻቸውን ለማጥፋት የማይመለሱ ሰዎች አንገዛም ባሉ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጽሙት ኢሰብአዊ ድርጊት ሁሌም አዲስ የሚሆንብን እኛ ትናንትን በመርሳት በሽታ በመለከፋችን  አለያም ሞኝ የሰማ/ያየ እለት እንደሚባለው እየሆነብን እንጂ ድርጊቱ ለወያኔ አዲሰ  አይደለም፡፡ እንደውም  ትናትን የመርሳት ችግራችን ከእባብ አንቁላል ርግብ አይጠበቅም የሚለውን አባባል  አስረስቶን የተቃውሞአችን እንዴትነትና  የጩኸታችን ምንነት  ከወያኔ የባህሪው ያልሆነ ነገር የምንጠብቅ ያስመስለናል፡፡
መቅረጸ ድምጽም ሆነ ምስል ያልደረሰባቸው የአይን ምስክርም ተገኝቶ ይፋ ያላደረጋቸው ብዙ አጅግ ብዙ ዘግናኝ አረመኔያዊ ድርጊቶች በወያኔ ለመፈጸማቸው በመረጃ ከተረጋገጡት ድርጊቶቹ ተነስቶ መገመት ይቻላል፡፡እነዚህ ሰዎች ለሥልጣን የበቁት የመረጃ ማስተላለፊያው ጥበብ እንዲህ ባለልተስፋፋበትና ባልተራቀቀበት ዘመን ቢሆን ምን ያደርጉ ነበር ብላችሁ አስባችሁ ታውቃላችሁ፡፡የሚሰሩት ብቻ ሳይሆን በር ዘግተው በምስጢር የሚነጋገሩት ድምጽ ከምስል እየሾለከ ለአለም ህዝብ አይንና ጆሮ ሲበቃ የማያስደነግጣቸው፣ የማያሳፍራቸውና የማያስፈራቸው (ለነገሩ ማን ሰው ብለው) ወያኔዎች በድብቅ የሚሰሩት ሁሉ ተደብቆ የሚቀር ቢሆን የአረመኔነታቸው መጠን የክፋታቸው ደረጃ  የአገዛዛቸው ግዞት እስከምን ይደርስ አንደነበር መገመት አይገድም፡፡
ጎምቱ ጋዜጠኞች ውሻ ሰው ነከሰ ዜና አይሆንም ሰው ውሻ ቢነክስ ግን ትልቅ ዜና ነው ይላሉ፡፡ የአባባሉ ምንነት ግልጽ ነው፡፡ ውሻ ሰው መንከሱ የተፈጥሮው፣ የባህሪው፣ የሚጠበቅበት ተግባሩም ስለሆነ  ነው ዜና የማይሆነው፡፡ ሰው ግን ውሻ ቢነክስ  ያልተለመደ ብቻ ሳይሆን የማይጠበቅና የማይገመት አዲስ አስገራሚ ክስተት  በመሆኑ ነው ትልቅ ዜና የሚሆነው፡፡
ወያኔም ማሰሩ፣ መግደሉ፣ ማሰቃየቱ፣ መዋሸቱ ፣ማታለሉ ሰው በሀሰት መወንጀሉ ወዘተ  ለሥልጣን የበቃበትና ሀያ አራት ዓመታትም ለመግዛት የቻለበት የተፈጥሮ ባህሪይው እና ተግባሩ  በመሆኑ በዚህ መልክ የሚፈጽማቸው ድርጊቶች ለጋዜጠኞች ዜና ሊሆኑ ቢችሉ አንኳን ለእኛ ለኢትዮጵያውያን  አዲስ ክስተት የሆኑ ያህል ሊያስገርሙን ሊያስደንቁንም ሆነ ሊያስደደነግጡን  አይገባም ነበር፡፡ ምነው ቢሉ እየረሳናቸው ካልሆነ በቀር አብረውን ያሉ ናቸውና፡፡
ይልቁንስ ከወያኔ አንጻር ለመገናኝ ብዙኃን ትልቅ ዜና ሊሆን ከኢትዮጵያውያን አልፎ የኢትዮጵያን ጉዳይ (ለራሳቸውም ዓላማም ሆነ ለህዝቡ ጥቅም ሲሉ) በቅርብ ለሚከታተሉ አለም አቀፍ ግለሰቦች ቡድኖችና መንግሥትታ አስገራሚ ክስተት ሊሆን የሚችለው፡፡
  • ሀያ አራት አመት የተጓዝንበት መንገድ ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ እየወሰደን እንዳልሆነ ስለተገነዘብን  መሰረታዊ ለውጥ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል ቢባል፤
  • ለዘመናት አብረውን የዘለቁ ሀገራዊ ችግሮችን እየቆፈሩ  አዳዲስ ልዩነቶችን መፍጠር የዛሬ መንገዳችንንም ሆነ  የነገ ግባችንን ከማሰናከሉም በላይ ኢትዮጵያን አንደ ሀገር ለማቆየት አስጋቸሪ የሚያደርጉ በመሆናቸው በእርቅ እልባት ሰጥቶ ሀገራዊ መግባባት መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበናል ቢባል፤
  • የገደለ ያስገደለ፣ የሰረቀ የተባበረ፣ በህዝብ ሀብት የከበረ፣ ከህግ በላይ ያደረ፣ወዘተ ለፍትህ ቀርቦ የህግ የበላይነትን በተግባር ለማረጋገጥ የሚያስችሉ  ርምጃዎች መታየት ቢጀመሩ፣
  • የመገናኛ ብዙሀን ሰራተኞች አፋሽ አጎንባሽ መሆናቸው ቀርቶ እውነትን አነፍናፊ፣ የባለሥልጣናትን ፊት እያዩና ትንፋሽ እያዳመጡ የሚሰሩ ሳይሆን የሙያቸውን ነጻነት አክብረው ለህሊናቸው ታማኝ ሆነው መስራት የሚችሉበትን አሰራር ተግባራዊ  የማድረግ ጅምር ቢታይ፤
  • ክልሎች በህገ መንግሥቱ የሰፈረው ሙሉ ነጻነታቸው ተጠብቆ ከህውኃት የሞግዚት አስተዳደር ተላቀው ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸውን በተግባር የሚያረጋግጥ ጅማሮ ቢታይ ፤
  • አባልም ሆነ አጋር የሚባሉት በህውኃት ተፈጥረው በህውኃት የሚዘወሩት ድርጅቶች የአገልጋይነት ዘመናቸውን ፈጽመዋል ተብሎ  በራሳቸው መቆም የሚያስችላቸው እንቅስቃሴ ቢጀመር፡፡
  • በድርጅት ታጥሮ በታማኝነት ተወስኖ ሀገር መምራት አንዳማይቻል የሀያ አራት አመት ልምዳችን አስተምሮናል፣ ስለሆነም ከዚህ በኋላ ሀገር መምራት በእውቀትና ሁሉን አሳታፊ በማድረግ  መሆን እንለበት ተገንዝበናል  ተብሎ ይህንኑ ገቢራዊ ማድረግ የሚያስችል ተግባራዊ ርምጃ  ቢታይ፡፡ ሌላም ሌላም ተመሳሳይ ነገር ከወያኔ ሰፈር ቢታይ ቢሰማ ትልቅ አስገራሚና ማራኪ ድንቅ ዜና ይሆናል፡፡ከዚህ ውጪ መልካም አስተዳደር የፍትህ መጓደል እያሉ ማላዘንም ሆነ  ይቅርታ እንጠይቃለን ማለት ሸብረክ ያሉ መስሎ ግዜ መግዣ የወያኔ የባህሪው  ተግባር ነውና ሊደንቀን አይገባም፡፡
ነገር ግን ወያኔ ያልፈጠረበትን በምክርም በመከራም ሊቀበለው ያልቻለውን ይህን ቅዱስ ተግባር በምን ተአምር ፈጽሞት ይህ  እውነት ሆኖ ለመስማት እንበቃለን! አይታሰብም፡፡ ወያኔዎች ይህን ለማድረግ አንደገና መፈጠር ይኖርባቸዋል፡፡ እኛስ ትናንትን እየረሳን በየግዜው የሚገጥሙንን የወያኔን የባህርይ ድርጊቶች  እንደ አዲስ  ከማየት ለመላቀቅ እና ትግሉን በምሬትና በወኔ ለማጥበቅ  እንደገና መፈጠር ይጠይቀን ይሆን?
ትናትን እየረሱ የእለት የእለቱን አዲስ እያደረጉ መጮኹ በትግሉ ላይ ትልቅ አሉታዊ ተጽእኖ ያለው ለመሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ የበደል ሸክሙ የሚከብደን፣ የጥቃቱ ምሬት የሚመረን፣አንባገነናዊ አገዛዙ የሚያንገሸግሸን ከ እስከ አሁን ያለውን ስናስታውስ ነው፡፡ የዛሬው ሲያስለቅሰን ሲያስቆጣን ብቻ ሳይሆን የትናቱም ሲቆጠቆጠን ነው፡፡  የትናንቱን እየረሳን ለዛሬው አንድ ሳምንት እየጮኸን ከዛም ሌላ አዲስ ነገር እስኪመጣ ይህን እየረሳን  እኩል መብሰል ባለመቻላችን (ጥሬ  ብስልና የአረረ) ነው ሀያ አራት አመት ሙሉ ትግል እንጂ ለውጥ ማስመዝገብ ቀርቶ አዳዲስ ጥቃቶችን ማስቀረት፤ ተጨማሪ ጥፋት እንዳይፈጸም ማስቆም ወያኔን ከደደቢት ህልሙ ስንዝር መግታት  ያልቻልነው፡፡  እውቁ የጽሁፍ ሰው አቶ ከበደ ሚካኤል ልጆች ሆነን ባነበብነው አንድ ጽሁፋቸው ፤
ያለፈው ሲረሳኝ መጪውን ሳላውቀው
እኔ መቼ ይሆን የምጠነቀቀው፤  ብለው የነበረው  ከላይ ለተገለጸው  ለእኛ እኛነት  በቂ ገላጭ አይሆንም ትላላችሁ?

9 ስደተኞችን ደብዳቤ ጽፎ ከአሜሪካ ወሰዳቸው




“ከህወሃት በላይ በራሳችን አዝኛለሁ” ኦባንግ ሜቶ
miami
ከተለያዩ አገራት አሜሪካ ገብተው የስደት ማመልከቻ ያስገቡ 9 ኢትዮጵያውያንን ህወሃት ተረከቦ ወደ አገር ቤት እንደወሰዳቸው ታወቀ። አንዱ ራሱን ለማጥፋት ሞከሮ ነበር። ወደ ኢትዮጵያ ቢሄድም የጤናው ሁኔታ አልታወቀም። ድርጊቱን አስመልክቶ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ከህወሃት ተግባር በላይ በራሳችን አዝኛለሁ” ሲሉ ወጣቶቹን ለማዳን ያደረጉት ጥረት መረጃው ዘግይቶ ስለደረሳቸው አለመሳካቱን አመለከቱ።
“ለቤተሰቦቼ የት እንዳለሁ እንኳን ነግሬያቸው አላውቅም” ሲል የተናገረውን ወጣት ጨምሮ ህወሃት የተረከባቸው ኢትዮጵያዊያን ወግኖች አሜሪካ ለመድረስ እስከ 14 ወራት ፈጅቶባቸዋል። በብራዚል፣ በኮሎምቢያ ጫካ አቋርጠው፣ በፓናማ ወንዝ ተሻግረው፣ በሜክሲኮ አድርገው በአጠቃላይ እስከ 16 የሚደርሱ አገራትን አልፈው በተለያዩ መንገዶቸ አሜሪካ ደርሰው ጥገኝነት የጠየቁት ወገኖች ህጉ ከሚፈቅደው ውጪ ከስድስት ወር በላይ በፍሎሪዳ ጠቅላይ ቅዛት ማያሚ እስር ቤት መቆየታቸውን ለአቶ ኦባንግ በአስራ አንደኛው ሰዓት የላኩት “የድረሱልን” ደብዳቤ ያስረዳል። መረጃቸው እንደሚያመለክተው ከተለያየ የኢትዮጵያ ክፍል የመጡት ወገኖች በፍሎሪዳ እስርቤት ከአንድ ወር እስከ አመት ተኩል ድረስ በእስር ቆይተዋል፡፡
አቶ ግርማ ብሩ የሚመሩት የህወሃት የአሜሪካ ቢሮ ስደተኞቹ ቢመለሱ ምንም አይሆኑም፣ ምንም አይደርስባቸውም፣ ሰላማዊ ኑሮ መኖር ይችላሉ፣ ወዘተ በማለት በጻፈው ደብዳቤና አዘጋጅቶ በሰጠው የመጓጓዣ ሰነድ አማካይነት ወጣቶቹ ተላልፈው ሊሰጡት ችሏል።
ህወሃት በኤርትራዊነት መታወቂያ የራሱን ወገኖች ለስደት በምዕራባውያን አገራት እየላከ ኢትዮጵያውያንን ሲያሰልል፤ በባህርና በበረሃ ተንገላተው አሜሪካ የገቡትን ምስኪን ዜጎች ላይ የወሰደው ርምጃ “ዲያስፖራውን የመበቀያ አንዱ አካል ነው” ተብሏል።
“ኑሮዬ ሳይስተካከል ለቤተሰቦቼ የት እንዳለሁ እንኳን አላሳውቅሁም። እናትና አባቴ ልሙት፣ ልኑር አያውቁም፤ ከተለየኋቸው ጊዜ ጀምሮ ስልክ ሳልደውል አራት አመት ከ11 ወራት አልፈውኛል” ሲል ለአቶ ኦባንግ የድረሱልኝ ጥሪ ካሰሙት ወጣቶች አንደኛው ተናግሯል፡፡ ዘጠኙ በአንድነት ተላልፈው ከመሰጠታቸው ጥቂት ቀናት አስቀድሞ ነበር አቶ ኦባንግ ደብዳቤያቸው የደረሳቸውና ጉዳዩን የሰሙት።
“እንደሰማሁ” አሉ አቶ ኦባንግ “ወዲያውኑ ስደተኞቹን የሚወክል ጠበቃ ያዝኩ። የወጣቶቹ ከስድስት ወር በላይ መታሰር ከህግ አንጻር አግባብ ባለመሆኑና ስደተኞቹ ሊመለሱ እንደማይገባ ለማውቃቸው እንደራሴዎችና ሴናተሮች በማስረዳት የእስር ውሳኔ ላስተላለፉት ዳኛ ደብዳቤ ሊላክ የሰዓታት ዕድሜ ሲቀር መርዶውን ሰማሁ” ብለዋል፡፡
ለወትሮው ረጋ ብለው በመናገር የሚታወቁት ኦባንግ “ለአንድ ቀን ተቀደምን” ሲሉ በቁጣ ነበር ስሜታቸውን የገለጹት። የጎልጉል የአሜሪካ ዘጋቢ ያነጋገራቸው አቶ ኦባንግ ቁጣቸውን ሊደብቁ በማይችሉበት ሁኔታ “ከህወሃት በላይ በራሳችን አዘንኩ” ብለዋል። “ለምን?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም “በተመሳሳይ መንገድ ተሰድደው፣ ታስረው፣ ዛሬ በመልካም ሁኔታ ላይ ያሉ ወገኖች የ5 ሺህ ዶላር ዋስ ሆነው ልጆቹን ማስፈታት ይችሉ ነበር ። ዳሩ ምን ያደርጋል ሁላችንም መነሻችንን እንረሳለን” ሲሉ ጉዳዩን አስቀድመው የሚያውቁ ወገኖች ላሳዩት ቸልተኛነት ወቀሳ ሰንዝረዋል።
“አቶ ግርማስ ቢሆኑ” አሉ አቶ ኦባንግ “ይህን ደብዳቤ እንዴት ይጽፋሉ? ወይም ሲጻፍ እንዴት ዝም ይላሉ? የጉዞ ሰነዱ ተሰርቶ እንዲላክስ ለምን ይፈቅዳሉ? ምንም ቢሆን እርሳቸው ሳያውቁ የሆነ ነገር የለም፤ ኅሊና ካላቸው በጣም ሊያፍሩበት ይገባቸዋል፤ እርሳቸውም ሆኑ አብረዋቸው የሚሰሩት ራሳቸውን በእነዚህ ልጆች ጫማ አስገብተው ማየት ይገባቸው ነበር፤ እነርሱ አገልግሎታቸውን ሲጨርሱ እዚሁ ከነቤተሰቦቻቸው ጥገኝነት ጠይቀው ኑሯቸውን ይቀጥላሉ፤ በአየር፣ በምድር፣ በወንዝ በስንት ስቃይና መከራ እዚህ የደረሱትን ልጆች ግን ደህና አገር እንዳለው የጉዞ ሰነድ ልከው ባዶ እጃቸውን ወደመጡበት እንዲመለሱ ያደርጋሉ፤ ይህ ወራዳና አጸያፊ ተግባር ነው፤ አገሪቱን ወይ በትክክል አያስተዳድሩ ወይ አገሩን ለቅቀው የሚወጡትን የፈለጉበት እንዳይኖሩ በሩ ይዘጋሉ፤ ኅሊና አለኝ ለሚል ሰው ይህ እጅግ አሳፋሪ ነው” ሲሉ ይወቅሷቸዋል።
ከስደተኞቹ መካከል አንዱ ወጣት በአገር ውስጥ የሚካሄደው ሰቆቃ ያስመረረው ከመሆኑ የተነሳ ወደ ኢትዮጵያ ከሚመለስ በአሜሪካ እስርቤት ለመሞት እንደሚመኝ መናገሩን አቶ ኦባንግ ጠቁመዋል፡፡ “በረሃና ወንዝ ስናቋርጥ በርካታ ወንድምና እህቶቻችንን አጥተናል፤ ማንም ስለ እነርሱ ግድ ያለው የለም፤ ታዲያ ለምን ለኛ ግድ ያላቸው ለመምሰል ይሞክራሉ” በማለት እንዳወራላቸው አቶ ኦባንግ ጠቅሰዋል፡፡
አገር ቤት ስራ አለመኖሩን፣ ችጋር፣ ረሃብና ድርቅ ዜጎችን እየጠበሰ መሆኑንን፣ እስርና ግድያ፣ አፈና ባለበት ሁኔታ እነዚህን ምስኪኖች ሰብስቦ መውሰድ ህወሃት ዲያስፖራውን ከመበቀል ያለፈ ትርጉም እንደሌለው በመግለጽ ዜጎች ከወዲሁ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የአሜሪካ እንደራሴዎች ምክርቤት አባላት ደብዳቤ ለመጻፍ ቃል ገብተው፣ ጠበቃ ተገኝቶ ወጣቶቹን ለማስፈታት የሚያስችል ርምጃ ከመጀመሩ አንድ ቀን በፊት በተፈጸመው ድርጊት ክፉኛ ማዘናቸውን የጠቆሙት ኦባንግ ሜቶ አሁንም እስር ላይ ያሉትን ለማስፈታት ጥረታቸውን እንደሚገፉበት ተናግረዋል። ከእንግዲህ ጉዳዩ የህወሃት ወይም በዋሽንግተን ዲሲ ያስቀመጠው ጽ/ቤቱ አይደለም፤ ጉዳዩ የራሳችን ነው የሚሉት “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ “ህወሃት የጉዞ ሰነድ እያዘጋጀ የራሱ ጽ/ቤት ባደረገው ኤምባሲው አማካኝነት እየሰጠ ስደተኞች ላይ የሚፈጽመው ይህ ተግባር የሚቆምበት ሁኔታ ከእንደራሴዎች ጋር በመነጋገር ተጽዕኖ የማድረግ ሥራ” ካሁኑ መጀመሩን ሳይጠቁሙ አላለፉም፡፡
ኦባንግ ስደተኛ ወገኖች ባሉበት ሁሉ ፈጥነው በመድረስና አለኝታ በመሆን የሚታወቁ ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን ዜጎች የአደባባይ ምስክርነት በ“ቃላቸው” ብቻ የሚሰጧቸው ሰው መሆናቸው የሚዘነጋ አይደለም።