Saturday, April 30, 2016

አመት በአል ሲቃረብ ብዙ ነገር ይናፍቀኛል| በእውቀቱ ስዩም



Bewketu Seyoum – Hagere Mariam (Maryland) USA [Must Listen)

አመት በአል ሲቃረብ ብዙ ነገር ይናፍቀኛል፡፡ ከሁሉም በላይ፤ እንደ አፍላ ጉም የሚሳብ የሉባንጃ እጣን – ብረት ምጣድ ላይ የሚጤስ ቡና -የጥላሁን ገሠሠ ዘፈን -ብዙ ፍቅር- ብዙ ፈገግታ ውልውል ይለኛል፡፡ ከመከረኛ ህይወታችን ማህል ብልጭ ብሎ የሚጠፋ አመት በአል የተባለ አብሪ ኮከብ ለዘላለም ይኑር!
አመት በአል ቀን ዋናው የደስታና የክብር ምንጭ መብላትና መጠጣት ነው፡፡
ግማሽ ፈረስ ግማሽ መልአክ የሆነው ሰው የተባለው ፍጡር እስኪረካ ድረስ መጠጣት፤ እስኪጠግብ ድረስ መብላት ይፈልጋል፡፡ ግን ምንዋጋ አለው? ባለማችን፤ ይልቁንም በአገራች እንደልብ የሚገኝ ነገር ቢኖር የምግብ እጥረት ነው ፡፡ ብዙ የሚበላ ሰው የሌላውን ድርሻ እንደወሰደ ስለሚቆጠር በማኅበረብ ዘንድ የተጠላ ነው ፡፡ የተፈጥሮን ጥያቄ ባግባቡ በመመለሱ  ሆዳም አጋሰስ እየተባለ ይብጠለጠላል ፡፡ በተቃራኒው ከምግብ የሚቆጠቡ ሰዎች ይወደሳሉ ፡፡ ጾመኞች ይቀደሳሉ፡፡
የተከበረ ዜጋ በጎረቤቱ ድግስ ላይ በተጋበዘ ቁጥር እንደ የሰውነቱን ፍላጎት በማርካትና የማኅበረሰቡን የክብር መመዘኛ በማሟላት መሀል ይወጠራል፡፡ ይህንን ውጥረት የሚያረግበው ማግደርደር የተባለው፤ በመጥፋት ላይ ያለ ባህል ነው፡፡ ጋባዥ እንግዳውን አፈር ስሆንልዎ በጊዮርጊስ ”እያለ ይለማመጠዋል ፡፡ ጋሽ እንግዳ“ በቃኝ!”ኧረ በቃኝ ያለ ትንሽ ሲታገል ይቆይና ይረታል፡፡ የምበላው እርስዎ አፈር እንዳይሆኑብኝ ብየ ነው የሚል ገጽታ ተላብሶ ምግቡ ላይ ይወርድበታል፡፡ ይህ ማኅበራዊ ተውኔት ሰዎች ኩራታቸውንም ራታቸውንም እንዳያጡ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
የሆነ ጊዜ ላይ አንዱ ከገጠር ወደ ከተማ ይመጣና ከተሜ ዘመዶቹ ቤት ያንዲት ሌሊት ጥገኝነት ጠየቀ ፡፡ ማታ ዘመዶቹ አጋም የመሰለ ዶሮ አቅርበውለት እንዲበላ ጋበዙት፡፡ ሰውየው ለወግ ያህል “ ፤ አሁን በልቸ ነው የመጣሁ፤ ማርም አልስ ”ካለ በኋላ አጥብቀው እስኪያስግደረድሩት ድረስ መጠባበቅ ጀመረ:) ጋባዦች ግን በልቶ ከመጣ አናስገድደውም ብለው የራሳቸውን እየተጎራረሱ ሞሰቡን ወደ ምድረበዳነት ከቀየሩት በኋላ አነሡት፡፡ ሰውየው ባዶ ሆዱን እሪታ በሳይለንሰር አፍኖ ሲገላበጥ አድሮ ሲነጋጋ ሎንቺና ተሳፍሮ ወደ ገጠር ተመለሰ፡፡ እግሩ ገና የቤቱን ደጃፍ እንደረገጠ ሚስቱን“ አቺ! እንጀራ በጨው አምጭልኝማ ” አላት፡፡ ሚስቱ“ ዋ! በሄዱበት አገር አልበሉም እንዴ !”
ባል – “ኧሯ!አቦና ማርያም የሌሉበት አገር ህጀ ጦሜን ተደፍቸ አደርኩ እንጂ!”

ከተሜ ዘመዶቹ፤ “ ባቦ፤ በማርያም” እያሉ ለማግደርደር አለመሞከራቸው ገርሞት ነው፡፡
ባገር ቤት ጨዋታ ውስጥ ዋና ገጸባሕርይው የቆሎ ተማሪ ነው፡፡ ያገር ቤት የቆሎ ተማሪ የዶንኪሆቴ የማኪያቬሊና የካሳኖቫ ቅልቅል ነው፡፡ ገድለኝነትን ብልጣብልጥነትንና ሴትአውልነትን አስተባብሮ ይዟል ፡፡ ባንድ አመት በአል ስላውዳመቱ ብሎ ሲለምን የቤቱ አባዋራ ገብቶ እንዲጋበዝ ፈቀደለት፡፡ ራት ቀረበ፡፡ ተሜ በልቶ እንደመጥገብ ሲል ሚስትዮዋን ለማጉረስ ይንጠራራ ጀመር፡፡ አባዋራው “ተሜ አርፈህ የራስህን ብላ ፤ ሚሽቴን የማጉረስ የኔ ፋንታ ነው” ብሎ ገሰጸው፡፡ ተሜ ግን“ግዴሎትም ጌታው ላግዝዎት ብየ ነው”እያለ በባልየው ፊት በኩል አመዳም እጁን እያሳለፈ ሚስትዮዋን ማጉረስ ቀጠለ፡፡ ጉዳዩ ትንሽ እየተካረረ መጣና አባዋራውና ተሜ ትግል ተያያዙ፡፡ሚስትዮዋም በመገላገል ፋንታ ሞሰቧን አንስታ ቡናዋን እያፈላች ትግሉን በጥሞና መከታተል ጀመረች፡፡ አባዋራና ተሜ ለረጅም ጊዜ ሲታገሉ ከቆዩ በኋላ ጉልበት ወደ ተሜ እያደላ የባል መገጣጠምያ እየላላ መጣ፡፡ አባዋራው ለማሸነፍ መጣሩን ትቶ ፤ እሱንም አካባቢውንም ሳይጎዳ የሚወድቅበትን ስትራቴጂ መንደፍ ጀመረ፡፡ በተሜ ብብት መሀል ሆኖ፤ ባጭር ባጭሩ እየተነፈሰ ሚስቱን ቁልቁል እያየ “ንሽማ እቃውን አነሳሽው” አላት፡፡
ሚስት ምድጃውን እያራገበች “ሊወድቁ እንዳይሆን?”ስትል ፡፡
“አይ ነብራሬ እና አንቺ ባመጣሽው እዳ ተገትሬ ልደር?
አመት በአሉ ከገላጋይ ኣልባ ጠብ የጸዳ ይሁንልዎት!

ደቡብ ሱዳን ከ125ቱ ኢትዮጵያውያን ህፃናትና ሴቶች 32ን ከአጋቾቹ ተረከብኩ አለች – 93ቱ የት ናቸው? * የጋምቤላው ክልል ፕሬዚዳንት መረጃው የለኝም አሉ

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 

Gambela

(ዘ-ሐበሻ) ከሁለት ሳምንት በፊት የሙርሌ ጎሳ አባላት ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያንን ገድለው 125 የሚሆኑ ህፃናትን እና ሴቶችን አፍነው ከወሰዱ በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት ‘ሕጻናቱ ያሉበትን ቦታ ደርሼበት ከብቤያለሁ” የሚል ዜና አሰምቶን ነበር:: ከበባው ቀናት አስቆጠረ:: ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን የት አሉ? እያሉ ሲጠይቁ ከረመ:: ያሉበትን ቦታ ከብቤያለሁ ያለው መንግስት ልጆቹን ለማስለቀቅ ድርድር ውስጥ ገባሁ ይለን ጀመር::
ዛሬ አሶሲየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ደግሞ ከታፈኑት 125 ህፃናትና ሴቶች መካከል 32ቱን የደቡብ ሱዳን መንግስት ማግኘቱን አስታውቋል:: የደቡብ ሱዳን ቦማ ግዛት አስተዳዳሪ አቶ ኦጋቾ ቻን ሊኩአንጎሌ በሚባል ሶስት መንደሮች ህጻናቱን እንደተረከቡ ሲገልጹ በቅርቡም 32ቱ ህፃናት ወደ ጁባ ሄደው ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ ሲሉን አስተያየታቸውን ለአሶሲየትድ ፕሬስ ሰጥተዋል:: እንደ ዜናው ዘገባ አፋኞቹ ህፃናቱን ሊኩአንጎሌ የተባለው መንደር ውስጥ ህጻናቱን ሳይለቋቸው አልቀረም::
እኚሁ አገረ ገዢ ቀሪዎቹን 93 ህፃናትና ሴቶች ካሉበት ቦታ ለማስለቀቅና ለማሰባሰብ እንሞክራለን” ብለዋል::
በሌላ ዜና ዋሽንግተን ፖስት እንደዘገበው የጋምቤላው ክልል ፕሬዚዳንት ጋትሉክ ቱት ስለልጆቹ መገኘት የሚያውቁት መረጃ የላቸውም:

የፋሲካ ገበያ | የዶሮ፣ የፍየል፣ የበግ፣ የሰንጋ፣ የቅቤና የእንቁላል ዋጋ ትንተ

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 
ዘንድሮ የትንሳኤ በአል ገበያ ምን ይመስላል? | የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገባ ከአዲስ አበባ
በተለያዩ የአዲስ አበባ የገበያ ስፍራዎች ተዟዙረን የበዓል ገበያ ዋጋን ለመቃኘት እንደሞከርነው፤ በአብዛኛው ከዓምና ተመሳሳይ የበዓል ገበያ ዋጋ ጋር ተቀራራቢ ነው፡፡ በአቃቂ ቄራ ገበያ የበሬ ዋጋ ከ5 ሺህ እስከ 22 ሺህ ብር ድረስ ሲሆን ዓምና በተመሳሳይ በዓል የበሬ ዋጋ ከ8 ሺህ ብር እስከ 25 ሺህ እንደነበረ ይታወሳል፡፡
sheep
በአቃቂ ቄራ፡- የበግ ዋጋ ከ700 ብር እስከ 3500 ብር ሲሆን በዓምና የፋሲካ ገበያም በግ ከ900ብር እስከ 3500 ብር ተሸምቷል፡፡ በአቃቂ የቁም እንስሳት ቄራ ገበያ፣ ከፍተኛው የፍየል ዋጋ 7ሺህ ብር መሆኑን ከነጋዴዎች የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡
በገበያው ቋሚ የበግና የፍየል ነጋዴ የሆነው ወጣት መስፍን ይልማ፤ በግና ፍየሎችን ከአዳማና አርሲ አካባቢ አምጥቶ እንደሚሸጥ ገልፆ፤ ዘንድሮ ገበሬው በግና ፍየል ለነጋዴው እየሸጠበት ያለው ዋጋ ከአምናው ጋር ሲነፃፀር በአማካይ እስከ 200 ብር ቅናሽ ማሳየቱን ተናግሯል፡፡

ገበሬው ለመጪው ክረምት የሰብል ምርት የሚያስፈልገውን ማዳበሪያ መግዣ የሚሆን ገንዘብ ለማግኘት የትንሳኤ በዓል የከብት ገበያን እንደመልካም አጋጣሚ እንደሚጠቀምበት ይኸው ነጋዴ ገልጿል፡፡
በአዲስ አበባ ዋናው ቄራ ገበያ የሃረር ሰንጋ በሬዎች፡-
  • ከ18 ሺህ ብር እስከ 25 ሺህ ብር እየተሸጡ ሲሆን
  • በሰውነት አቋማቸው አጫጭር የሆኑት የጅማ ሰንጋዎች ደግሞ ከ6 ሺህ ብር እስከ 10ሺህ ብር እንደሚገኙ ታውቋል፡፡
  • በግ በቄራ አካባቢ ባሉ ገበያዎች መካከለኛው፡- ከ1300 ብር እስከ 2ሺህ ብር፣
  • ሙክት በግ እስከ 5 ሺህ ብር ይገኛል፡፡
የዶሮ ዋጋ
  • ዝቅተኛው 130 ብር፣
  • ከፍተኛው 400 ብር ሲሆን
    እንቁላል
  • – በነጠላ 3 ከ50፣
  • – ቅቤ በኪሎ፣
  • – ከ180 ብር እስከ 240 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
  • በአስኮ ገበያ ዶሮ ከ250 ብር እስከ 350 ብር፣
  • እንቁላል በነጠላ 3 ብር 50፣
  • ቅቤ በኪሎ ከ180 ብር እስከ 250 ብር፣
  • አይብ ከ65-75 ብር በኪሎ ይሸጣል፡፡
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት በበኩሉ፤ 5ሺህ የሚሆኑ የእርድ እንስሳትን የሚያቀርብ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 2500 በሬዎች፣ 2300 ደግሞ በግና ፍየሎች እንደሆኑ ገልጿል፡፡
ከድርጅቱ ባገኘነው መረጃ መሰረት፤ ለበዓሉ ድርጅቱ በራሱ የመሸጫ ሱቅ የበግ ስጋ በኪሎ 130 ብር ይሸጣል፡

Friday, April 29, 2016

የአማራ ህዝብ በጸጸት የሚተርከው የቅኝ ገዥነት ንስሃ የለውም!


amhara
                ፕሮፌሰር ባዬ ይማም
ለአፍታ ያክል ቆም ብለን እጅግ ከመዘውተሩ የተነሳ እየቸከ የመጣውን “የአማራ የበላይነት” ሐተታ ቅቡልነት በታሪካዊ ሃቆች ማንጸሪያነት ስንመርምር፤ አስቀድሞ የበላዮቹ አማሮች እነማን ናቸው? በዚህ ቡድን ውስጥ አባልነት እንዴት ይገለጣል? የአማራ ባህል ምንድነው? ባህል ሌሎች ቅሬታዎችንና በደሎችን መሸፈኛ ትዕምርት ቃል ነውን? ወይንስ ባህል አንድ ህዝብ በሌላው ላይ የበላይ መሆኑን የሚያመላክት ቃል ነውን? በደቡብ የግዛት መስፋፋት ስለተደረገባቸው አካባቢዎች በጅምላ እንደሚነገረው በስልጣን ላይ የነበረው ሰው ሁሉ አማራ ነው ብሎ ማስረገጥና ማረጋገጥ ይቻላልን? የሚሉ መሰረታዊ ጥያቄዎች በአእምሮአችን ያጭራሉ፡፡ ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት 

          መጣጣርም ስለአማራ ትክክለኛውን ታሪካዊ እውነት ለመግለጥና ለመረዳት ያግዛል፡፡ 
ብዙ ጊዜ “የምኒልክ ታሪካዊ ድራማ መሪ ተዋንያንና ተጠቃሚዎች በዋነኛነት አማሮች” እንደሆኑ ይነገራል፡፡ ይህ አገላለጽ በእርግጥ ብዙሃኑ አማራ በጥቂቱ እንኳን ቢሆን ስማቸው የተለጠፈበት የፖለቲካ፣ የማህበራዊና የኢኮኖሚ ስርዓት ተጠቃሚዎች ናቸው ማለት ይሆንን? በዚህ አውድ ውስጥስ አማራ በትክክል ማንን ያመለክታል? ጎጃሜዎችን፣ ጎንደሬዎችን፣ ወሎየዎችን ወይስ የሸዋን ሰዎች?
የአማራ መንግስት በሚሉት ስርዓት ውስጥ ሸዌ አማሮች አቢይ ተጠቃሚዎች ተደርገው እንደሚታዩ የብሄረተኞችን ጽሁፎች ያገላበጠ አንባቢ ሁሉ አያጣውም፡፡ ይህ ሲባልስ ብዙሃኑ የሸዋ አማራ የጥቅመ ብዙው ገዥ መደብ አባል ነው ማለት ይሆንን? በየትኛውም መንገድ አልነበረም፡፡
ሌላው ቀርቶ በአብዛኛው የመንግስት አመራር መዋቅር ተሹመው፣ አብዛኛውን የኢኮኖሚ ምንጮች ተቆጣጥረው፣ ብዙውን የአገሪቱን የግዛት ክልሎች ይገዙ የነበሩ፣ በደቡብ አውራጃዎች ሰፋፊ ሁዳዶች የነበሯቸውና ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴያቸው አዲስ አበባን ማዕከል አድርገው የመሰረቱ ነበሩ ተብሎ ቢታሰብ እንኳ የሸዋ መኳንንቶች ከአማራ ህዝብ እጅግ በጣም ጥቂቱን እጅ (አንድ መቶኛ) እንኳን የሚሸፍኑ አልነበሩም፡፡ 
በተቃራኒው ብዙሃኑ የሸዋ አማራ በድህነት የሚኖር ስልጣን አልባና እንደማንኛውም ቡድን በስርዓቱ የተመዘበረ ነበር፡፡ እንዲያውም “የሸዋ አማራ” በአንዳንድ ሁኔታዎች በደቡባዊው የሃገሪቱ ክፍል “ተጨቋኝ ከነበሩት ህዝቦች” እጅግ የከፋ ህይወት ይመራ እንደነበር የታሪክ ሰነዶች ያስረዳሉ፡፡
እንቆቅልሽ የሚሆነው ከችግርና ከዘራፊዎች ጋር እየተናነቁ ህይወታቸውን ባቆዩ ስለምን ጎጃም፣ ጎንደር፣ ሸዋና ወሎ ቅኝ ገዥዎችና ጨቋኞች ተደርገው በጅምላ ተፈረጁ ነው፡፡ ይልቁንም እጅግ በርካታ የሆነውን የአማራ አርሶ አደር ቅኝ ገዥ አድርገው የሚያቀርቡት ይዞታችንን አጥተናል ከሚሉ ብሄረተኞች ርካሽ ወዳጅነትን ለመሸመት የሚሹ ፀረ አማራ አቋም ያላቸው ጸሃፊዎች ናቸው፡፡
አማራ ሌሎች ህዝቦችን ቅኝ ገዝቷል የሚል የሃሰት አሉባልታቸውን ቢያናፍሱም የስርዓቱ ተጠቃሚ አድርገው በሚከሱትና በሚወቅሱት አብዛኛው የአማራ አርሶ አደር ቀዬ የሚታየው ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ እውነታ ፍጹም የተለየ ነው፡፡ በአካባቢው የተካሄደው የግምገማ ሪፖርትም እንደሚያመለክተው የገጠር ልማትን በተመለከተ የተሻለ እድገት አይታይም፡፡ ለምሳሌ በአማራ አካባቢ በሸዋ መንዝና ግሼ፣ ተጉለትና ቡልጋ እና መርሃቤቴ በትምህርት፣ በመንገድ ልማት፣ በጤና ማዕከላት ወዘተ ከሌላው የኢትዮጵያ ክፍል በባሰ እጅግ ኋላ ቀር ናቸው፡፡
የአማራ ቅኝ ገዥነት ፅንሥ ሀሳብ አቀንቃኞች ደጋግመው ወደሚያናፍሱት “የአማራ የባህል የበላይነት ወይም ጭቆና” ትኩረታችንን ስናዞርም እውነታው የተለየ መልክ አይኖረውም፡፡ “የባህል የበላይነት” የሚለው አገላለጽ ለመሆኑ በተለይ የባህሉ “አስፋፊዎች” ራሳቸው የህዝቦችና የባህሎች ውህደት ውጤት በሆኑበት ሁኔታ ከሌሎች ያልተቀየጠ የአንድ ነገድ ባህል ሊባል የሚችል ንጹህ ባህል አለን? የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ የአማራ ባህልስ ለሌሎች ግንኙነትና ልውውጥ ላደረገባቸው ባህሎች መጥፋትና መዋጥ ስጋት ሆነዋልን? ይህ ሁኔታስ በደቡብ ባሉት ልዩ ልዩ ባህሎች ላይ ተንጸባርቋልን? ለመሆኑ የሌሎች ባህሎች ተጽዕኖ የማይጋባበት ምንም ሳይለወጥ በነባር መልኩና ይዞታው ሊኖር የሚችል ባህልስ አለን?
አስመሮም ለገሰ “የባህል ልውውጥ ሂደት አንድ ገጽታና መልክ ያለው ስዕል ተደርጎ አይታይም፣ ለምሳሌ የአፋን ኦሮሞ ተናጋሪዎች አማራ ሆኑ ብሎ ከማጠቃለል፣ ይልቁንስ ሁኔታው ውስብስብና አያሌ የባህል ቅርጾች በሚያደርጉት የእርስ በእርስ መስተጋብር ውስጥ ፍጹም አዲስ ባህል የሚወለድበት ሂደት ነው” በማለት ይገልጻል ፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታም፣ ክላፓም “የአማራ ባህል የነገደ-ብዙ ባህል እምብርት ነው” ማለቱም በረጅሙ የአገር-ብሄር ምስረታ ሂደት በህዝቦችና በባህሎች መካከል በተደረጉ የሃሳብ፣ የልምዶች፣ የሸቀጦች ወዘተ ልውውጥ ሂደትና አብሮ መኖር ውስጥ የተፈጠረውን የባህሎች መዛነቅ መግለጹ ነው፡፡
ከእነዚህ ሁኔታዎች ስንነሳም ‹‹የአማራ የበላይነት›› የሚለው አተያይ በታሪክ እውነታና ሃቅ ያልተመሰረተ ምናባዊ ልቦለድና የፈጠራ ተረታ ተረት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ይህ ተረት አንድም አፍራሽ በሆነ መንገድ የኢትዮጵያን ታሪክ በአውሮፓ ታሪክ መነጽር ለመመልከት ከመጣጣር፣ ያለበለዚያም ይሁነኝ ብሎ የታሪክ ሃቆችን በመበረዝና በተሳሳተ መንገድ በመተርጎም የፖለቲካ አጀንዳን ከግብ ለማድረስ ከሚደረግ ጥረት የመነጨ ነው፡፡
እውነቱ መገለጽ ካለበት ደግሞ የአማራ ማህበረሰብ በቅኝ ግዛት ፅንሥ ሀሳብ አቀንቃኞችና በጀሌዎቻቸው ከተለጠፈበት መጥፎ ገጽታ በተጻራሪ ጠንካራ ሰራተኛ፣ ሰላም ወዳድ፣ ተባባሪና ታጋሽ ህብረተሰብ ነው፡፡ ቅኝ ገዥ ሆኖም አያውቅም፣ የበደላቸው ወገኖች ስለሌለም በጸጸት የሚተርከው የቅኝ ገዥነት ንስሃ የለውም፡፡
ስለዚህም የአማራ ህዝብ ያልስራው እና በውሸት የተቀባው የታሪክ ጥላሸት ሊነጻ፣ ያለ ግብሩ የተጫነበት የገዥነት አመል አለው የሚል ውግዘት ሊረሳና ሊቆም፣ በምትኩም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ያለው ትክክለኛ ቦታና ያበረከታቸው ታላላቅ ተግባራት ሊነገሩለት ይገባል፡፡



Wednesday, April 27, 2016

የቀድሞ የጋምቤላ ፕ/ት 9 ዓመት ተፈረደባቸው (በእጅ ጽሁፋቸው የጻፉትና ምስጢር የያዘው የክስ መቃወሚያቸው እጃችን ገብቷል)

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 
okello

ዘ-ሐበሻ) የኖርዌይ ዜግነት እንዳላቸው የሚነገርላቸውና ደቡብ ሱዳን ላይ ታፍነው ተወስደው የታሰሩት የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦኬሎ አኳይ “አገርን ለመገንጠል” በሚል በቀረበባቸው ክስ የ9 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው:: ኦኬሎ ከፍርድ በፊት ለሚዲያ ይድረስልኝ በሚል የላኩትና ለፍርድ ቤቱም በእጅ ጽፉፋቸው አስገብተውት የነበረው የክስ መቃወሚያ ዘሐበሻ እጅ ደርሷል:: ይዘነዋል::
ከኦኬሎ ጋር በተባባሪነት የተቀሰሱት ዴቭድ ኡጁሉ 9 ዓመት; ኡቻን ኦፔይ 7 ዓመት; ኡማን ኝክየው 7ዓመት; .ኡጁሉ ቻም 7ዓመት; ኦታካ ኡዋር 7ዓመት እና ኡባንግ ኡመድ 7 ዓመት ተፈርዶባቸዋል::

በጋምቤላ ውጥረቱ እየተባባሰ መሆኑ ተገለጸ (የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር ዜናዎች)

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 
ሚያዚያ 18 ቀን 2008 ዓ.ም.ዜና (April 26, 2016 NEWS)
# በጋምቤላ ውጥረቱ እየተባባሰ መሆኑ ተገለጸ
# ለጥጥ ልማት በማለት ብድር ወስደውና ደን መንጥረው የነበሩ ግለሰቦች ጠፉ ተባለ
# የትንሣዔ በዓልን አስታኮ ወያኔ የሸማቾች ማህበራት ሱቆች እያቋቋመ ነው
# የጄኔራሉን ገዳዮች ባስቸኳይ እንዲይዙ የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ለጦር ኃይሉ መመሪያ ሰጡ
# አልሸባብ በባይደዋ የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ጦር ሰፈርን ወርሮ ጉዳት አደረሰ
# የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በሱማሊያ የገባውን ድርቅና ረሃብ ለመቋቋም የምግብ እርዳታ ያስፈልጋል አሉ
#ሬክ ማቻር ጁባ ገቡ

ሚያዚያ 18 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø ጋምቤላ 18 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ባለው የደቡብ ሱዳን የጀዊ ስደተኞች ሰፈር የፈነዳው ግጭትና ግድያ ትላንትም ቀጥሎ እንደነበር በቦታው ያሉ ምስክሮች ገልጸዋል ። በቦታው የሰፈሩት ስደተኞች መቶ በመቶ የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ የሪያክ ማሻር ተከታዮችና የኑዌር ተወላጆች ሲሆኑ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን ሾፌር የነበረው ኢትዮጵያው ሁለት ስደተኛ ህጻናትን በመኪና ገጭቶና ገድሎ በመሰወሩ ኑዌሮቹ በሰፈሩ ያሉትን ኢትዮጵያውያን ለመግደል ተነስተው ብዙዎችን እንደገደሉ ይታወቃል ። ከተገደሉት ውስጥ የስደተኛው ኮሚሽን ኢትዮጵያዊ ሰራተኞችም እንዳሉበት ታውቋል። ጀዊ የአንዋኮች አካባቢ ስትሆን ወያኔ ኑዌሮችን በዚያ ያሰፈረው ለተንኮል ነው ተብሎም ተጋልጧል። ወያኔ ከግድያው በኋላ ዜጎችን ለመከላከል ምንም እርምጃ ባለመውሰዱ ኢትዮጵያውያኑ ተደራጅተው የስደተኛውን ሰፈር ማጥቃታቸው ታውቋል። የሟቹ ቁጥርም ቀላል አልሆነም ። የተባበሩት መንግስታት የስድተኛ ኮሚሽን ሰራተኞቹን ከጀዊ አካባቢ አሽሽቷል። ግጭቱ ገና አልበረደም ሲል ዛሬም የደረስ ዜና ያረጋግጣል ።
Gambela
ወያኔ ለዘረፋና ለስርቆት እንዲያመቸው ከ 100 ሺ ሄክታር በላይ የጋምቤላ መሬትን ለጥጥ እርሻ በማለት ለንግድ ሸሪኮቹ በመስጠትና ለልማትም በማለት 3 ቢሊዮን ብድር በመፍቀድ የጥጥ ምርትን እናሳድጋለን በማለት ፕሮፓጋንዳውን ካሰራጨ ወዲህ የጥጥ ምርቱም ሳይኖር ልማቱም ሳይካሄድ ደን ተጨፍጭፎ ከቆየ በኋላ በብድር የተሰጠው ገንዘብ ለምን ተግባር እንደዋለ እንኳ ለማወቅ አለምቻሉ ተገልጿል። ለጥጥ ልማት በማለት መሬት ወስደው ደን መንጥረው ገንዘብ ተበድረው ጠፉ የተባሉ ሰዎችና ኢንቬስተሮች እነማን እንደሆኑ ባይገለጽም ወያኔ ምርመራና ማጣራት ጀምሬያለሁ ብሏል። ጉዳዩን የተከታተሉ ወገኖች ግን ዘረፋውና የተፈጥሮ ወድመቱ በወያኔ አባላትና በንግድ ሸሪኮቻቸው መፈጸሙን ይናገራሉ።
Ø በአባይ ወንዝ ግድብና አጠቃቀም ዙሪያ ወያኔና ግብጽ የገቡበትን የፖሊቲካና የዲፕሎማሲ ውዝግብ ለማብረድ በወያኔ ፓርላማ አፈጉባዔ የሚመራ አንድ የልኡካን ቡድን ግብጽንና ሱዳንን መጎብኘቱ ይታወሳል። የጉብኝቱ ዓላማ የታሰበለትን ግብ ይምታ አይምታ ባይታወቅም በወቅቱ የነበረውን የዲፕሎማሲ ውጥረት ግን ሳያለዝበው እንዳልቀረ ተገምቷል፡፤ ወያኔ ከሱዳን ጋር መልካም ወዳጀነት ፈጥሮ በድንበር አካባቢ ለም መሬቶችን አሳልፎ ከሰጠና ሱዳንም በአገሩ የሚገኙ የወያኔ ተቃዋሚዎችን እያፈነ ለወያኔ ለመስጠት ጥረት በሚያደርግበትና በሁለቱ አገሮች መካከል የድንበር ጥበቃ ውል ተፈርሞ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የሱዳን ሕዝብ ዲፕሎማሲ የተባለ ቡድን የወያኔን ባለስልጣኖችን እንደሚያነጋግር ተገልጿል። ጉብኝቱ ግንቦት 1 ቀን 2008 ዓም የሚጀመር ሲሆን የዲፕሎማሲው ቡድን ከወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው ጀምሮ ከሌሎች የወያኔ ባለስልጣኖችን ያናገጋራል ተብሏል፡፤
Ø መጭውን የትንሳዔ በዓል አስታኮ የወያኔ አገዛዝ ሱቆችን በማደራጀት አባ ወራዎችን በቡድን እየመደበ እንደሚያሰማራ ታውቋል። ከአስራ አምስት እስከ ሃያ የሚደርሱ አባወራዎች በአንድና በሁለት ሱቆች ሸቀጦች እንዲሸጡ በማደራጀትና በማስገደድ ነዋሪዎንና የነጋዴው ህብረተሰብን ለማጋጨት እየተሞከረ መሆኑ ተገልጿል። ሱቆቹ በዋናነት ስኳርና ዘይት የሚያቀርቡ ሲሆን ሌሎች ሸቀጦችንም ሊጨምሩ እንደሚችሉ ተነግሯል። የወያኔ አገዛዝ በመላ ኢትዮጵያ ላንሳራፋው የኑሮ ውድነት ተጠያቂ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም የችግሩ መነሻና ምንጭ የነጋዴው ህብረተሰብ እንደሆነ አድርጎ በማቅረብ ነጋዴዎችን ከሕዝብ ጋር ለማጋጨት የሸማቾች ማህበራትን ማቋቋሙ ይታወቃል። የፋሲካ በዓልን ተንተርሶ እንደ ቅቤ እንቁላል ዶሮ በግና በሬዎች የመሳሰሉ የምግብ አቅርቦቶች ዋጋ ጭማሪ እያሳየ መሆኑ ታውቋል።
Ø ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ለወያኔ ማስረከብ የለመደበት የኬንያ መንግስት የታይዋን ተወላጅ ሆነው በህገወጥነት የወነጀላቸውን የታይዋን ተወላጆች አስሮ ለሀገራቸው ሳይሆን ለቻይና ማስረከቡ ተጋለጠ። ቻይና ታይዋን ግዛቴ ናት ብትልም ቻይናና ታይዋን ሁለት የተለያዩ ሀገሮች ሆነው እንድሉ ይታወቃል። ወያኔ በበኩል ኬንያ እንደ የመን የሚመጡ ተቃዋሚዎችን አግታ እንድታስረክብ ዝርዝር ስሞችን ሰጧል ተብሎም መረጃ አለ ።
Ø ከጥቂት ቀናት በፊት በብሩንዲ አንድ የጄኔራል ማእርግ ያላቸው ከፍተኛ ባለስልጣን ከነባለቤታቸው ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን ገዳዮችን አፈላልገው እንድይዙ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለወታደሮቻቸው የአንድ ሳምንት የጊዜ ገደብ ያለበት ጥብቅ መመሪያ የሰጡ መሆናቸው ታውቋል። ፕሬዚዳንቱ ለሟቾቹ ቤተሰቦች ሀዘናቸውን የገለጹ ሲሆን የአገሪቱ የጦር ኃይልም አንድነቱን አጠናክሮ ሁኔታውን በቁጥጥር ስር እንዲያደርግ ተማጽነዋል። የፕሬዚዳንቱ ትእዛዝ በብሩንዲ እየተካሄደ ያለውን ግድያ ያፋፍማል የሚል ስጋት ፈጥሯል። የብሩንዲ የእርስ በርስ ግጭት ከጀመረ ወዲህ የመንግስት ባለስልጣኖች ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች ሲገደሉ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ደግሞ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የጅምላ ግድያ እያካሄዱ ከመሆናቸውም በላይ በርካታ ሰዎችን አስረው ሰቆቃዊ ድርጊት እየፈጸሙባቸው መሆኑ ይነገራል።
Ø በሱማሊያ ከዋናዋ ከተማ ከሞጋዲሾ ሰሜን ምዕራብ 250 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ከባይደዋ ከተማ አጠገብ በሚገኘው የአፍሪካ ህብረት እና የሱማሊያ መንግስት የጦር ካምፕ ላይ አልሸባብ ጥቃት ሰንስዝሮ ቢያንስ 20 ወታደሮችን የገደለ መሆኑ ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል። ከተወሰነ የተኩስ ልውውጥ በኋላም የአፍሪካ ህብረት የሰላም አሰከባሪ ሃይሎች እና የሱማሊያ ወታደሮች የጦር ሰፍሩን መልሰው መቆጣጠራቸው ተነግሯል። የአልሸባብ አጥቂዎችም ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ቢገልጽም ከአልሸባብ በኩል የተሰማ ዜና የለም።
Ø መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና የሰብአዊ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ በሱማሊያ የገባውን ከፍተኛ ድርቅና ረሃብ ለመቋቋም አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ድርጅቶቹ በጋራ መግለጫቸው ላለፉት አራት አመታት በሱማሊያ ዝናም በመጥፋቱ ምክንያት ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ መሰደዱን ገልጸው ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ከፍተኛ እልቂት ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል። ከስድስት ዓመት በፊት በሱማሊያ በገባው ድርቅ ምክንያት ከ250 ሺ ሰው በላይ የሞተ መሆኑን አስታውሰው ተመሳሳይ የሕዝብ እልቂት እንዳይደርስ ከፍተኛ እርዳታ መሰብሰብ አለበት ብለዋል።
Ø ከጥቂት ቀናት በፊት ከአንድ የቱርክ የንግድ መርከብ ላይ በባህር ላይ አፋኞች ተጠልፈው ተወስደው የነበሩ ስድስት የመርከቡ ሰራተኞች የተለቀቁ መሆናቸውን የንግድ መርከቡ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ሚያዚያ 3 ቀን 2008 ዓም. ማንነታቸው ያለታወቀ የባህር ላይ አፋኞች መርከቧ ላይ በመውጣቱ ካፕቴኑ የሚገኝበትን ስድስት ሰዎች በቁጥጥር ስር ማድረጋቸው የታወቀ ሲሆን ማክሰኞ ሚያዚያ 18 ቀን 2008 ለቀዋቸዋል ተብሏል። የተለቀቁት የመርከቧ ሰራተኞች በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ መሆናቸው ቢነገርም ለመለቀቃቸው ካሳ መከፈሉ እና አለመከፈሉ የተገለጸ ነገር የለም። በዚህ ዓመት ብቻ በናይጄሪያ ወደብ አካባቢ ከ32 በላይ የመርከብ ጠለፋዎች የተካሄዱ መሆናቸው ከተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት አካባቢ የተገኙ ዜናዎች ይጠቁማሉ።
Ø የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ ሪክ ማቻር ለአንድ ሳምንት ያህል ጉዟቸው ካዘገዩ በኋላ በዛሬው ቀን ጁባ ገብተዋል። የአማጽያኑ ድርጅት ቀደም ብሎ ባወጣው መግለጫ ሚስተር ማቻር ዛሬ ሚያዚያ 18 ቀን ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ጁባ የሚገቡ መሆናቸውን ገልጾ የነበረ ሲሆን በታቀደው መሰረት ለምክትል ፕሬዚዳንቱ ቦታ ለመያዝ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ተብሏል። ሚስተር ማቻር ጁባ ይገባሉ ተብሎ ታቅዶ የነበረው ሚያዚያ 10 ቀን የነበረ ሲሆን ከዚያ በኋላ በተደጋጋሚ በታቀዱት ቀናት ወደ ጃባ ባለመለሳቸው በዓለም አቅፉ ህብረተሰብ በሌሎች ላይ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሮ እንድነበር አይዘነጋም።

Saturday, April 23, 2016

Ethiopians struggle for freedom from back home to the US. Capital

BBN Documentary (Presented by Sadik Ahmed

https://youtu.be/RumfOOfIFs4

በጋምቤላ ሕዝብ ለተቃውሞ ወጣ – “መንግስት ግድያውን ለፖለቲካ ፍጆታና ኦሮሚያን እና ጎንደርን ለማረጋጋት ተጠቅሞበታል” – ጋምቤላ አልተረጋጋችም

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 


13076784_10205648164656023_6561978623060851611_n
(ዘ-ሐበሻ) በጋምቤላ “መንግስት የለም ወይ?” ያሉ ነዋሪዎች ሰሞኑን የተፈጸመውን ግድያ በማውገዝና መንግስትም ይህንን የሕዝብ ሞት ለራሱ የፖለቲካ ፍጆታ አዎሎታል በሚል ሕዝቡ በነቂስ አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን ሲያሰማ መዋሉን ለዘ-ሐበሻ የደርሰው መረጃ አመለከተ::
“ልጆቻችን ይመለሱ…. በሃገራችን ሰላም አጣን… መንግስት በኛ ሞት የፖለቲካ ድል ማግኘቱን ያቁም…” እና ሌሎችንም መፈክሮች ሲያሰሙ የነበሩት የጋምቤላ ነዋሪ ሰልፈኞች መንግስትን ሲያወግዙ ውለዋል::
ሕፃናቱን ለማስለቀቅ ከብቤያለሁ እያለ ሲፎክር የነበረው የኢትዮጵያ መንግስት ወታደር እስካሁን ልጆቹን ባያስለቅቅም የትናንቱን ገድያ ተቃውመው ለሰልፍ የወጡትን ኢትዮጵያውያን ግን ዛሬ ጋምቤላ ላይ ሲቀጠቅጥና ለመበተንም ሲሞክር ታይቷል::

gambela

በጋምቤላ የተለያዩ ከተሞች በአሁኑ ወቅት መረጋጋት አለመኖሩን የሚገልጹት የአካባቢው ምንጮች ማን ከየት መጥቶ ገድሎ እንደሚሄድ እንደማይታወቅና ሕዝቡም እርስ በራሱ ተፈራርቶ እንደሚገኝ ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል::
በጋምቤላ ጉዳይ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት የታህሳስ 13 መታሰቢያ ንቅናቄ ተወካይ አቶ ኦዶል ኦዶል ለዘ-ሐበሻ በሰጡት አስተያየት የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት የሰሞኑን ግድያ የፖለቲካ ትርፍ ማግኛ አድርጎታል ብለዋል:: እንደ እርሳቸው አባባል መንግስት እየነገረን ያለው ትንሹን ግድያና በተለይም ሙርሌዎች ያደረሱትን እንጂ ከዛ በፊት ከ15 ቀናት በፊት ስለሞቱት ሰዎች የነገረን ነገር የለም ብለዋል::: እንደ ኦዶል ገለጻ መንግስት በኦሮሚያና በጎንደር የተነሳበትን ሕዝባዊ ቁጣ ለማብረድና ሃሳብን ለማስቀየር የሙርሌዎችን ግድያ ከመጠቀሙ በላይ ምንም ያደረገው ነገር የለም ብለዋል::
በተለይም በትናንትናው ዕለት በጋምቤላ በአሰቃቂ ሁኔታ ስለተገደሉት 15 ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ጠይቀናቸው “ገዳዮች ናቸው የተባሉት ሰዎች የገደሉት አማሮችን እና ኦሮሞዎችን ብቻ መርጠው ነው; ይህም ማን ከበስተጀርባው እንዳለ ያሳየናል” ብለውናል::
አቶ ኦዶል ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት የጋምቤላ አክቲቭስቶች ሕዝቡ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ መረጃዎችን ለሕዝብ ቶሎ ቶሎ ማድረስ አለባቸው ብለዋል:: ሕዝቡ መንግስት የሚለውን ብቻ በመስማት መንግስት አሸናፊ እንዳይሆን መረጃዎችን ከፎቶዎች ጋር በማውጣት ማጋለጥ ይገባቸዋል ብለዋል::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ ትናንት ጃዊ በተባለ የስደተኞች ጣቢያ ስለተገደሉት ኢትዮጵያውያን ጉዳይ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጋትሏክ ቱት ኩዃት ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ የሞቱትን ቁጥር ወደ 10 አሳንሰውታል:: ለትናንቱ ግድያ መነሻም ሴቭ ዘችልድረን የተባለ የግብረሰናይ ድርጅት መኪና በስደተኞቹ ካምፕ ላይ በደረሰበት አደጋ የሁለት ስደተኞች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ ነው ሲሉ ተናግረዋል:: ስደተኞቹ ከመኪና አደጋው ጋር ተያያዥነት በሌላቸው 10 ሰዎች ላይ ግድያ መፈጸማቸውንም ገልጸዋል::
ጋምቤላ ተወጥራለች…. ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን እንዳገኘች ትመለሳለች:

የወያኔ አቅጣጫ የማስቀየር ፖለቲካ በዳላስ (የዳላስ ፎርትወርዝ ኢትዮጵያውያን ፎረም)


d24af016-c583-4552-bd62-6ade75040889

ከዳላስ የፖለቲካ እና ውይይት አዘጋጅ ስብስብ:
መከራ ከማይደርቅባት አገራችን ኢትዮጵያ የሚጎርፈው ዘግናኝ ለአይን እና ለጆሮ የሚሰቀጥት ዜናን ያላየ ወይንም ያላዳመጠ የአለም ህብረተሰብ አለ ለማለት ያስቸግራል። ለአለፉት ስድስት እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ወራት በኦሮሞ ወገኖቻችን የተጀመረው የሰላማዊ አመጽ እንደቀጠለ ነው። ለዚህ ሰላማዊ ጥያቄ በወያኔ እየተመለሰ ያለውም ግድያና ጭፍጨፋ መሆኑን አይተናል እያየንም ነው። በሰሜን ኢትዮጵያ በወልቃይት፣ በጸገዴ፣ በጸለምት እና በሰሜናዊ የወሎ ክፍለ ሀገር የትግራይ አዋሳኝ በነበሩ ቀበሌወች ያለፈቃድ ወደትግራይ ከተከለሉ በኋላ የነበረው የህዝብ ማጉረምረም ወደ አደባባይ ወጥቶ የማንነት ጥያቄ የተጀመረበት ጊዜ ነው። ወያኔ እራሷ በፈጠረችው የዘር እና የማንነት ፖለቲካ ስትያዝ ወደአመጽ በመውሰድ ሕዝብን ማሰር መግደል እና ዳብዛ ማጥፋቱን ቀጥላበታለች።፡የወልቃይት እና የጸገዴ ሕዝብ ለአለፉት 25 እና ከዚያም በላይ ለሆኑ አመታት ሕዝብን በጥይት ጨርሶ መሬቱን ወደ ትግራይ ለመቀላቀል በጠባቧ ጎጠኛ ቡድን የተዘየደው እና በግድ የተከለለው ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ከመቸውም በላይ ገዝፎ የወጣበት እና ከዚህችው ጠባብ ብሄርተኛ ድርጅት ጋር ግብግቡ የፋመበት፣ ጥያቄውን ያነሳው ሕዝብ ሰላሙን አጥቶ የሚሰቃይበት ወቅት ላይ ነው።
ከሁሉም በላይ የአለምን ሕዝብ አይንና ጀሮ የሳበው አሳዛኝ ርሐብ ወያኔ ልትደብቀው በማትሽልበት ግዝፈት አይኑን አፍጦ የወጣበት እና 14 ሚሊዮን ህዝባችን ዳግም ለምጽዋት ሰጭ ደላሎች የተዳረገበት፣ በአንጻሩም ቁጥረ ብዙ ወገን ዙሪያ ገባው ጨልሞበት መድረሻ አጦ በማለቅ ላይ ያለበት ጊዜ ነው። ይህ ሁሉ ግፍ ሳያንስ በሰሞኑ በጋንቤላ ወገኖቻችን የደረሰው ፍጅት መልስ ከማንም በላይ ይፈልጋል። ለመሆኑ ጭፍጨፋው በውጭ ሰርጎ ገብ ተፈጸመ ማለቱስ የቱን ያክል እውነትነት ሊኖረው ይችላል? ቢሆንም እንኳን የዜጎችን ደም ለማፍሰስ ከጥይት የቀደመ ፍጠት ያለው የአጋዚ ጦር እና መንግስት ነኝ ባዩ ወያኔ መራሹ ምን እየሰራ ነበር? ቢያንስ አንድ Liaison Officer ጁባ ያስቀመጠ መንግስት፣ የአየርና የምድር ጦር በቅርብ በራሪ ድንበር ጠባቂ ሄሊኮፍተሮች ጋር የታጠቀ እንዴት ለቀናት የተጓዙ የውጭ ሰርጎ ገቦች ዜጎችን ሲጨፈጭፉ ምን ያክል ስውርነት ቢኖራቸው ነው ወዘተ። የሚሉት ጥያቄወች ሁነኛ መልስ ቢሹም መልስ ሰጭ እንደማይኖር ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠንቅቆ የተረዳው ጉዳይ ሆኗል።

ከላይ የተዘረዘሩትን ግዙፍ ብሄራው ቀውሶች ምንም እንኳን መደበቅ የሚቻል ባይሆንም ወያኔው የፖለቲካ ጨዋታውን ወደ ውጭው ዜጋ በማዞር በሰሞኑ በብዙ የአውሮፓ እና የሰሜን አሜሪካ ከተሞች በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን ዜናው ለዳላሶችም ደረሰን። ከዚህ በፊት ወደዚሁ በመምጣት አፍሮ የተመለሰው ደመቀ መኮነን የተባለ የወያኔው ምክትል ምናምን በኤፕሪል 24/2016 እነድሚመጣም የወያኔው ደጅ ጸኝወችና ተጠቃሚወች በማሰራጨት ላይ ባሉት ወረቀት ለማወቅ ችለናል። ይህ ግለሰብ የአገራችንን ምእራባዊ ክፍል ለሱዳን ፈርሞ እንደሰጠም የተነገረለት ጉደኛ ተላላኪ ነው። በዚህ አያበቃም። እርሱ ከቤተሰቡ ጋር ከወሎ ክፍለ ሀገር ወደ መተከል ጎጃም ተዛውሮ ያደገበትን ቀበሌ እያወቀ ዜጎች ወደክልላችሁ ተብለው ፍዳ ሲቀበሉ፣ በአገራቸው ስደተኞች ሆነው ሲንጓለሉ በስራቱ ባለው ውክልና እና ስልጣን እንኳን የት ወደቃችሁ ያላለ ግለሰብ እንደሆነ አገር ያወቀው ጸሀይ የሞቀው ታሪኩ ነው። እናም ወደ ዳላስ የሚመጣበትም የፖለቲካ ጨዋታ የአማራ ልማት በሚል ፌዝ የተጃጃለ ከተገኘም ጨው ለማላስ አለያም ያው የአገሪቱን የገዘፉ እና አደባባይ የወጡ ችግሮችን አስቀይሮ አጀንዳ ለመስጠት እንደሆነ አይዘነጋም።
ማሳሰቢያ በዳላስ እና ፎርትወርዝ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ
ይህን የወያኔ አቅጣጫ አስቀያሪ አጀንዳ ባለማወቅ ወደዚህ ስብሰባ ለመሄድ የተጠራችሁ (የተጋበዛችሁ) የአገራችንን ሁኔታ እና በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል በጥሞና እንድትመረምሩ እናሳስባለን። የዳላስ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ኮሚውኒቲ ማህበር በተጠራ ለወገን ደራሽ ድጋፍ World Vision ለተባለ አለማቀፍ የእርዳታ አሰባሳቢ እና አድራሽ ድርጅት $62,000.00 አሰባስበው ባለፈው እሁድ ገንዘቡን ለተጠቀሰው ድርጅት በኮሚውኒቲው ሊቀመንበር እንዳስረከቡ አይተናል። ይህ በጎ ለወገን ደራሽ ተግባር በተሰራበት ከተማ እና ሳምንት ለወገኖቻችን እልቂት ምክንያት የሆነው የስርአቱ ተላላኪ በጠራው ስብሰባ መገኘት ህሊና ላለው እና አዙሮ ለሚያይ የሚመጥን ተግባር እንዳይደለ ሁሉም እንዲረዳልን እናሳስባለን።
በዳላስ እና ፎርት ወርዝ ለምትኖሩ አክቲቪስቶች እና አገር ወዳድ ወገኖች ሁሉ በምንኖርበት ከተማ የታቀደው የወያኔ ስብሰባ አንድም ዘረኝነትን ያስቀደመ መደለያ ሲሆን። ሌላም ወገን ከወገኑ የሚለያይ ብሎም በውስጥ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ለመሸፈን የታቀደ የወያኔ መላ ወይንም ፌዝ ስለሆነ ሁሉም እንዲያወግዘው ቅስቀሳ እንድታደርጉ በትህትና እናሳስባለን። በቦታውም ተገኝቶ የወያኔውን ተልእኮ አሳፍሮ መመለስ ይጠበቅብናል።

Friday, April 22, 2016

አባባ ተስፋዬ ምንም አልሆኑም

ababa tesfaye

(ዘ-ሐበሻ) በርካታ የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ወደ ዝግጅት ክፍላችን እየደወሉና እየጻፉ “ስለ አበባ ተስፋዬ የሚወራው እውነት ነው ወይ?” ሲሉ ጥይቀውናል:: ዘ-ሐበሻ ወደ አዲስ አበባ የተለያዩ የዜና ምንጮቿ ጋር ደውላ ለማረጋገጥ እንደቻለችው አባባ ተስፋዬ ላይ እንደሚወራው አይደለም:: አባባ ተስፋዬ ትናንት ከተሸለሙና መልካም ቀን ከማሳለፋቸው በስተቀር በሰላም እየኖሩ ነው:: ወደቀ ሲባል ተሰበረ የሚሉ ወገኖች በሶሻል ሚድያዎች አባባ ተስፋዬ እንዳረፉ አድርገው ቢያስወሩም እርሳቸው ግን በሕይወት አሉ::
አባባ ተስፋዬ በአሁኑ ወቅት 93ኛ ዓመታቸው ሲሆን ትናንት እርሳቸውን በሕይወት እያሉ ለመዘከር በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ የ10 ሙያዎች ባለቤት መሆናቸው ተወስቷል:: ከ10 በላይ ሙያ ባለቤት እንደሆኑም በዝክር መድረኩ ላይ ተወስቷል። ተዋናይ፣ ድምጻዊ፣ የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋች፣ የውዝዋዜ አሰልጣኝ፣ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅ፣ ደራሲ (የልጆች ተረት)፣ ተረት ተናጋሪ፣ የዜማና ግጥም ደራሲ፣ የምትሃት ባለሙያ እንዲሁም ሌሎችም::
ረዥም ዕድሜ ይስጥልን

Wednesday, April 20, 2016

የአማራ ምሁራን ፣ የወገናችሁን እርም ትበሉ ዘንድ እንዴት ተቻላችሁ?! – ልዩ ልዩ ካርታዎችን የያዘ መረጃ

Filed under: News Feature,ነፃ አስተያየቶች | 

የአማራ ምሁራን ፣ የወገናችሁን እርም ትበሉ ዘንድ እንዴት ተቻላችሁ?!

በቅርቡ የግል የምርምር ጥናቴን ለማካሄድ ፈለጌ ይጠቅሙኛል ያልኳቸውን መረጃዎች ፍለጋ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለስልጣን (CSA) ድረ-ገፅን ተመልከቼ ነበር፡፡ በዚህ አጋጣሚ ነበር ‘Atlas on Selected Welfare Indicators of Ethiopian Households’ የሚለው ሰነድ ላይ አይኔ ያረፈው፡፡ በCSA ና በአለም አቀፍ ባለሙያዎች ትብብር በ2004 GC የተሰበሰበን መረጃ አጠናቅሮ የያዘ ሲሆን፤ በሀገሪቱ ውስጥ ባሉ ክልልና ዞኖች ደረጃ  ስለ ህብረተሰቡ ማህበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ ነባራዊ ሁኔታ መረጃ እንዲሰጥ እና በመንግስት ደረጃም ለፖሊሲ ዝግጅትና ትንተና እንዲያገለግል ተብሎ የተዘጋጀ ቁልፍ ሰነድ ነው፡፡ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሳይንሳዊ ማጣቀሻዎችን ከማካተት ውጭ፣ ሰነዱን እንደወረደ አቅርቤላችኋለሁ፡፡ እስኪ አንብቡና እናንተው ፍረዱ። 
  1. የጤና ባለሙያዎች እገዛና ክትትል አገልግሎት ተደርጎላቸው የሚወልዱ ነፍሰጡር እናቶች (Delivery Attendance in Modern Way
Amhara
ይህ ካርታ  በወሊድ ጊዜ በአዋላጅ ነርሶች ድጋፍ ያገኙ እድሜያቸው ከአምስት አመት በታች የሆኑ ሕፃናትን ማህበረሰባዊና ክልላዊ ንፅፅር ያሳያል፡፡ በወሊድ ጊዜ  በባለሙያ መታገዝና ጥሩ እንክብካቤ ማግኜት ለእናትና ልጅ ጤንነት  አንዱ መሰረታዊና በጣም አስፈላጊ እንደመሆኑ መጠን አገልግሎቱ በሌሎች የማህበረሰብ ክልሎች በሚገባ እንዲተገበር ተደርጓል።
ከካርታዉ በግልፅ እንደሚታየዉ በአማራ ክልል በአዋላጅ ነርሶች ድጋፍ የሚፈፀም ወሊድ ከ6  በመቶ  በታች ነዉ፤ ይህም ከሀገሪቱ በጣም አስከፊ ደረጃ ላይ ያለ ነዉ፡፡ ይህ ፖሊሲያዊ አሰራር አዲስ ለሚወለዱ አዳጊህጻናት ሞት ያለዉን አስተዋጽኦ  ለመረዳት  ሰው ሆኖ ከመፈጠር ያለፈ ህሊና አይጠይቅም።  በአማራ ክልል ያለዉ አዲስ የተወለዱ ህጻናት ሞት ከሀሪቱ በጣም ከፍተኛ መሆኑን በ 2013 GC አቶ/ ዶ/ር መኮንን እና ሌሎችአጋሮቹ  ይህን አስከፊ ሁኔታ በሳይንሳዊና በመጀመሪያ ደረጃ መረጃ ላይ ተመርኩዘው በፃፉትና በአለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ስምና ተቀባይነት ባለዉ BMC ጆርናል የታተመዉን የጥናት ጽሑፍ እንደምሳሌ መዉሰድ ይቻላል፡፡ ምናልባትም ይህ ጉዳይ ለአማራ ህዝብ ቁጥር መቀነስ (በ1999 ዓ.ም ህዝብ ቆጠራ መሰረት) አንዱ ምክንያት መሆኑ ብዙወችን ማስማማቱ አይቀርም።
  1. የልጆች ጤናማ ያልሆነ አሰተዳደግ መኖር (Prevalence of Stunting)
Amhara 2

ከእድሜ ጋር የተመጣተነ የልጆች እድገት (በተለይም ቁመት) ከጤናማ አመጋገብ ጋር የሚያያዝ ጉዳይ ነዉ፡፡ ይህ ካርታ በኢትዮጵያ ያለዉን ጤናማ ያልሆነ እድገት ያላቸዉን ልጆች ስርጭት ያሳያል፡፡ በዚህም  በአማራ ክልል ያለዉ የሕጻናት መጎሳቆል ከሀገሪቱ የማህበረሰብ ክልሎች በጣም የከፋ ደረጃ ላይ መሆኑን ያሳያል፡፡
ለረጅም ጊዜ  የተመጣጠነ ምግብ አለማገኘትና በችግር ማቅ እንዲወድቁ መደረጉ የማመዛዘን ችሎታ እና እዉቀት የመሻት ብቃትን እንደሚጎዳ በሳይንስ የተረጋገጠ እውነታ ነው (ለምሳሌ Kar et al. 2008) ፡፡ ምንም እንኳ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንድምታው/ተጽኖው ትንሽ ሊመስል ቢችልም በረጅም የጊዜ ሂደት ሲደመር ግን ውጤቱ እጅግ በጣም አሳሳቢ ነው፤ በተለይ የወደፊቱ ትውልደ አማራ የሆኑ ሃገር ተረካቢ  ሕጻናት የህልውና ሁኔታ ሲታሰብ፡፡
  1. የልጆች መቀጨጭ (Prevalence of underweight)
Amhara 3

የልጆች ከእድሜያቸዉ ጋር የተመጣጠነ ክብደት መኖር  የጤናማ አመጋገብን መኖር አመላካች ነዉ፡፡ ይህ ካርታ በክልሎች ያለዉን የልጆች ጤናማ ያልሆነና ከተፈለገዉ ክብደት በታች የመሆን ንፅፅራዊ ምጣኔን ያሳያል፡፡ በዚህም በአማራ ክልል ያለዉ የልጆች መቀጨጭ በጣም ከፍተኛና ከሀገሪቱ በጣም በአስከፊ ደረጃ ላይ ያለ ነዉ፡፡ ይህም ከላይ የተጠቀሰውን ችግር ጥልቀት የሚያጠናክር ነው፡፡
  1. የቤተሰብ ኑሮ ደረጃ (The proportion of households preferring current living standard)
Amhara 4

ይህ ካርታ በክልሎች መካከል ያለዉን የኑሮ ደረጃ ያሳያል፡፡ ከሌሎች ጋር ሲነፃፀር በአማራ ክልል ያለዉ በጣም የተበደለና ባሊህ ባይ ተቆርቋሪ ወገን ያጣ መሆኑን የሚያሳይ አሳዛኝ ሁኔታ ነዉ፡፡
  1. መረጃ ተደራሽነትና ሀገራዊ ውሳኔ ሰጭነት – Information access: particularly Radio Ownership
እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በማደግ ላይ ባሉ ሀገሮች ካሉት የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች መካከል ሬዲዮ በጣም ጠቃሚዉና ዝቅተኛው ነዉ፡፡ ይህ ካርታ በክልሎች መካከል በአባወራ ደረጃ ያለዉን የሬዲዮ ሰርጭት ያሳያል፡፡በአማራ ክልል ከአስር አባወራዎች መካከል በአንዱ እንኳን ሬዲዮ ያለዉ ማግኘት አይቻልም፤ ይህም ከሌሎች ክልሎች አንፃር ሲታይ በጣም ወደኋላ እንዲቀርና ለሀገራዊ ጉዳዮች እንዳይሰጥ የተደረገ መሆኑን ያሳያል፡፡
በዚህ የመረጃ ዘመን እንደ ሬዲዮ ያሉ በጣም በቀላሉ ሊገኙ የሚችሉ የመረጃ  ምንጮችን ማግኝት እንዳይችል  መደረጉ በብዙ መልኩ ተፅእኖ አድርሶበት ይገኛል ፡፡  ለምሳሌ፣ የአማራ ክልል በዚህ ሁሉ ችግር ውስጥ ተተብትቦ እያለ (ከላይ ከሌሎቹ ክልሎች በባሰ ሁኔታ ኑሮው እንደመረረው ቢገልፅም) ምናልባትም የመረጃ እጥረት በክልሉ ለሚታየው   ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ መልስ አለመስጠት ራሱ የሆነ ተፅዕኖ ማድረሱ  አልቀርም፡፡
ከሌሎች ጋር ሲወዳደር በክልሉ የ HIV/AIDS መተላለፊያና መከላከያ መንገዶች ግንዛቤ አለመኖር (በተመሳሳይ ሪፖርት የተገለፀ) ፤ እንዲሁም ከላይ እንደተገለፀዉ የነፍሰ ጡሮች የጤና ባለሙያ አገልግሎት ያለማግኘት ችግር ጋር ተዳምሮ የቫይረሱን ከእናት ወደልጅ የመተላለፍ እድል ከፍተኛ መሆኑን ይገፃል፡፡ ይህም ጉዳይ ለአማራ ህዝብ ቁጥር መቀነስ (የ1999 ዓ.ም ህዝብ ቆጠራ ይመልከቱ) አንዱ መሆኑን ብዙወች ከመስማማት አልፈው በየመድረኩ  በመረጃ አስደግፈው ማቅረባቸው የ፡amhara 5

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከጋምቤላ ታግተው የተወሰዱት 125 ህፃናት ያሉበትን ቦታ መክበቡን አስታወቀ

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 



File Photo

(ዘ-ሐበሻ) ባለፈው ሳምንት ከደቡብ ሱዳን እንደመጡ በተነገረላቸው የሙርሌ ጎሳ በመጡ ታጣቂዎች ታግተው የተወሰዱት ህፃናት ያሉበትን ስፍራ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ማወቁን እና መክበቡን አስታወቀ::
የመንግስት ሚድያዎች ዛሬ እንደዘገቡት ከኢትዮጵያ ታግተው የተወሰዱት ህፃናት በአሁኑ ወቅት ጆር እና ቆቅ በተባሉ አካባቢዎች እንደሚገኙ ሲገለጽ በዚህም አካባቢ መከላከያ ሰራዊትቱ ህፃናቱን ለማስልቀቅ በታጣቂዎቹ ላይብ ጥቃት ከፍተው አካባቢውን መክበባቸውን አስታውቀዋል::
በጋምቤላ በነዚህ ታጣቂዎች ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ ስትዘግብ ቆይታለች:: ከዚህ በተጨማሪም 125 ህፃናት እና ከ2 ሺህ በላይ ከብቶችም መወሰዳቸው መዘገቡ አይዘነጋም::

Tuesday, April 19, 2016

ከመቀሌ የመጣ ከባድ መኪና እና ወደ አላማጣ የሚጓዝ ሚኒባስ ተጋጭተው የ25 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 


bus

(ዘ-ሐበሻ) በየቀኑ መልካም ዜና የማይሰማባት ሃገር እየሆነች በመጣችው ዛሬም ከባድ አደጋ ተከስቷል:: በቅርቡ በጋምቤላ ክልል ያለቁት ወገኖቻችን ሃዘን ሳይቆርጥልን ዛሬ ደግሞ ሌላ አሳዛኝ ዜና ተከስቷል:;
የአይን እማኞች እንደሚገልጹት ዛሬ በሰሜን ወሎ በቆቦ ከተማ እጅግ አሳዛኝ የመኪና አደጋ ደርሷል:: አደጋው የተከሰተው በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 10 ሰዓት ሲሆን የአደጋው መነሻም የሁለት መኪኖች ግጭት ነው::
የአይን እማኞች እንደሚናገሩት ከመቀሌ ከተማ ሸቀጣ ሸቀጥ የጫነ ከባድ መኪና ከነተሳቢው ወደ ወልዲያ ሲጓዝ የነበረና ከቆቦ ወደ አላማጣ 16 ተሳፋሪዎችን ጭኖ የሚሄድ በተለምዶ አባዱላ የሚባለው የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ቆቦ ከተማ ላይ ተጋጭተው እስካሁን የ25 ሰዎች ሕይወት አልፏል::
በዚህ መኪና አደጋ እግረኞች እና በሳይክል የሚጓዙ ሰዎችም ሕይወት መጥፋቱ ተዘግቧል:: ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እናቀርባለን:

Monday, April 18, 2016

Ethiopian regime has a 25-years-long bloody legacy

Filed under: News,Opinion | 

By Degeufe Hailu
“Nations cannot realise the full promise of independence until they fully protect the rights of their people,” Barrack Obama, president of the United States, said on tour to Kenya and Ethiopia last year. This is ironic, because on that trip he failed to criticise human rights abuses by the Ethiopian government, which he hailed as “democratically elected”
- See more at: http://www.zehabesha.com/ethiopian-regime-has-a-25-years-long-bloody-legacy-2/#sthash.PtPqPeId.dpuf


eprdf-tplf

Ethiopians are very familiar with the government’s attempts to oppress any opposition. The Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) government took power in 1991. All opponents are persecuted as terrorist collaborators.
Today, Ethiopia stands as a nation in contempt of human rights. According to the Committee to Protect Journalists, Ethiopia has the second highest number of journalists forced into exile between 2010 and 2015 after Syria.
Evidence of the denial of freedom of expression includes the arrest and incarceration of Zone 9 bloggers in 2014. Their name is a reference to the eight divisions of the infamous Kaliti Prison — suggesting that Ethiopia as whole is effectively the jail’s ninth division. The arrest of the bloggers for publication of news and opinion pieces that were critical of the government and its repressive entourage exposed the country’s non-existent due process.
Last June, Andargachew Tsige, the secretary-general of Ginbot 7, a group banned for allegedly advocating the armed overthrow of the Ethiopian government, was deported to Ethiopia from Yemen while in transit to Eritrea. This transfer violated international law prohibiting sending someone to a country where they are likely to face torture.
Tsige has been detained without access to family members, legal counsel or consular representation, which he is entitled to as a British citizen. His detention location, to date, is unknown.
Terrorising those who publically criticise the government’s endeavours, however, is not limited to media outlets. In April 2015, peaceful protests in Oromia over the government’s planned expansion of the Addis Ababa municipal boundary were met with excessive force, including shootings. Many protesters perished, while others continue to be detained without charge.
Protest against displacement from land and family is not new to Ethiopia.
Under the “villagisation program” 1.5 million rural people have been relocated under the guise of improving their access to basic services. One example of this forced displacement is in the Gambella region, for which relocation was accompanied by insufficient compensation and consultations, and violence including beatings and arbitrary arrests. This was just in the first-year of the “villagisation program”.
In subsequent years, 200,000 indigenous persons from 240,000 hectares of land in the lower Omo Valley were displaced without compensation or consultation, due to the government’s development of sugar plantations. The clearance of land, sold to foreign interests, year-in year-out has lined the pockets of the government, without regard for the region, or the Ethiopian people in general.
Inherent in this inculcating of terror, is the need to maintain the status quo. This is evident in the landslide victory in June 2015 of the ruling party and its insipid allies. The Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front, a rebrand of the TPLF, overwhelmingly ejected the only opposition parliamentarian from office.
“This result was completely expected, there is no multi-party system in Ethiopia. It’s just fake,” said Taye Negussie, a sociology professor at Addis Ababa University.
President Obama’s visit to Kenya and Ethiopia was to whitewash a continent.
US collaboration with the TPLF, a party that has expelled all opposition and is dedicated to a reign of pure terror, has a long history — Obama and three of his predecessors have visited.
The people in the Horn of Africa can live in harmony and in peace, and flourish through the development of a stable region, without the need for foreign interference.
The mission to oust the oppressive regime in Ethiopia, is aimed to stop a culture of fear and suspicion, especially if we want to enter into a serious problem-solving dialogue.
We need to be united participants of the political process and not the subjects of a repressive and terrorising government, to address our problems genuinely and solve them definitively.
- See more at: http://www.zehabesha.com/ethiopian-regime-has-a-25-years-long-bloody-legacy-2/#sthash.PtPqPeId.dpuf

ዮናታን ወልዴና ባህሩ ደጉ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተፈተው ከሰዓታት በኋላ ማዕከላዊ እስር ቤት ታሰሩ


Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 



Bahiru-Deguyonatan-tesfaye (1)
(ዘ-ሐበሻ) ላለፉት 647 ቀናት በሽብር ወንጀል ተከሰው እስር ቤት የነበሩትና ባለፈው አርብ በከፍተኛው ፍርድ ቤት በነፃ እንዲለቀቁ የተፈረደላቸው ባህሩ ደጉ እና ዮናታን ወልዴ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተፈተው ከተለቀቁ በኋላ ከሰዓታት በኋላ እንደገና ተይዘው ማዕከላዊ መታሰራቸው ተሰማ::
ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሁለቱም ወጣቶች በማዕከላዊ እስር ቤት ይገኛሉ:: እነዚሁ እስረኞች ለምን እንደገና እንደታሰሩ የታወቀ ነገር የለም: