Monday, June 30, 2014

የተቃዋሚ አባላትን ማሰር ማወከብና ማፈናቀሉ ቀጥሏል

በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የሚኖሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አባሎች የሆኑት
- አቶ ሞላ ገረመው
- አቶ ብርሃኑ ገረመው
- አቶ ካሳሁን እንዳለ ከረቡዕ ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ የተቃዋሚ አባል
በመሆናቸው ብቻ የሚያርሱትን መሬት ቀምተው አሳርሰውባቸዋል፡፡ ለምን እንቀማለን ዜጎች አይደለንም ወይ ብለው ተቃውሞ
ሲያሰሙ ከፓርቲው ለቃችሁ ካልወጣችሁ መሬታችሁ አይመለስም በማለት የቀበሌው ሊቀመንበር አቶ ፀጋዬ ጎሹ አስፈራርተዋቸዋል፡፡
እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም በይልማና ዴንሳ ወረዳ (አዴት) የሚገኙ የመኢአድ አባላት ላይ እስርና አፈና የተፈጸመ ሲሆን አቶ በቃሉ
ደፋሩ የተባሉ የወረዳው አባል ከሳምንት በፊት በፖሊስ ተይዘው እስካሁን ፍ/ቤት አልቀረቡም፡፡
በዚሁ ወረዳ – አቶ አትገኝ እምሬ እንዲሁም
- ቄስ ይሁን ዘለቀ ከሐሙስ ሰኔ 19ቀን 2006ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት አይታወቅም ሲሉ የመኢአድ
የህ/ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡

የግንቦት 7ቱ ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ታሰሩ

andargachew
(ዘ-ሐበሻ) የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አባልና በአስመራ የሚገኘውን የግንቦት 7 ትግል ይመሩታል የሚባሉት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መታሰራቸውን ግንቦት 7 ባወጣው መግለጫ 

አስታወቀ።እንደ ግንቦት 7 ንቅናቄ መግለጫ ከሆነ አቶ አንዳርጋቸው ላለፉት አንድ ሳምንታት በየመን ታግተው የሚገኙ ሲሆን ለማስለቀቅ የተደረገው ጥረትም አልተሳካም። አቶ አንዳርጋቸው ወደ የመን የተጓዙት ለትራንዚት እንደሆነ የገለጸው የንቅናቄው መግለጫ የየመን መንግስት እኚህን የትግል ሰው ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፎ እንዳይሰጥ ስጋት እንዳለበት አስታውቋል

Hiber Radio: ኦነግ ያለውን መከፋፈል አስወግዶ በአንድ አመራር እታገላለሁ አለ* (በሳዑዲ አረቢያ የምህረት አዋጅ ዙሪያ ልዩ ዘገባ)


ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ሰኔ 22 ቀን 2006 ፕሮግራም
<...የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ ለመከታተል ነው ፍ/ቤት የሄዱት ።የፓርቲያችንን የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ኦናታን ተስፋዬን ከጣቢያ ደብድበው ነው የለቀቁት የፓርቲው የሴቶች ጉዳይ አባል ምኞት መኮንንም ብሔርሽን ካልተናገርሽ ብለዋታል በአጠቃላይ ከዞን ዘጠኝ አባላት ጋር ግንኙነት አላችሁ ልትበጠብጡ ነው የመጣችሁት ብለዋቸው ነገ ተመልሰው ማዕከላዊ እንዲቀርቡ ቀጠሮ ሰትተው ነው አስረው የለቀቋቸው...> ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከፍ/ቤት ግቢ ታስረው ስለተወሰዱት ሁለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሰዎች ለህብር ከሰጡት መግለጫ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)
የዓለም ዋንጫ ሰሞነኛ ውሎ ከአስገራሚ ክንውኖችና አጓጊ ውጤቶቹ ጋር (ልዩ የስፖርት ዘገባ)
ለመንግስት ሰራተኛው ይጨመራል የተባለው ደሞዝና ተከትሎት የመጣው ኢኮኖሚያዊ ጣጣ(ልዩ ወቅታዊ ዘገባ )
<...በምህረት አዋጁ የሚካተቱ በሳውዲ እስር ቤት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እስረኞች ጉዳያቸውን የሚከታተልላቸው የጉዞ ሰነድ የሚያዘጋጅላቸው ይፈልጋሉ ። ለዚህ ቆንስላው የሚመለከተው አካል ትኩረት ሰጥቶ መስራት አለበት...>
ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ የሳውዲ ንጉስ የሰጡትን የምህረት አዋጅ አስመልክቶ ካደረግንለት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)
የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ፌዴሬሽን እውን ለኢትዮጵያውያን በእኩል ይሰራል? የቬጋስ ቡድን አወዛጋቢ ውሳኔን አስመልክቶ ውይይት ከሚመለከታቸው ወገኖች ጋር(ሙሉውን ያዳምጡ)
ዜናዎቻችን
የዞን ዘጠኝ አባላትን ጉዳይ ለመከታተል ሔደው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታስረው ተለቀቁ
የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊው ታስሮ በፖሊስ ተደብድቧል
ኦነግ በውስጡ ያለውን መከፋፈል አስወግዶ በአንድ አመራር ስር ለመታገል መወሰኑን አስታወቀ
አረና የተከለከለውን የተቃውሞ ሰልፍ በመቀሌ ደግሞ ሊጠራ ነው
ግብጻዊቷ ጋዜጠኛ በካይሮ የኢትዮጵያው አገዛዝ አምባሳደር ላይ ስልክ መዝጋቱዋ መነጋገሪያ ሆነ
የተባበሩት መንግስታት የኤርትራን የሰባዊ መብት ጥሰት እመረምራለሁ ማለቱ የአቶ ኢሳያስ መንግስትን አስቆጣ
ከአጥኚው ቡድን በስተጀርባ ኢትዮጵያና አሜሪካ አሉበት ሲሉ አገሪቱ ባለስልጣናት ይከሳሉ
በሳውዲ እስር ቤት ካሉ ኢትዮጵያውያን እስረኞች መካከል የሰሞኑ የአገሪቱ ንጉስ የምህረት አዋጅ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ቆንስላው አፋጣኝ ትብብር እንዲያደርግ ተጠየቀ
ሌሎችም ዜናዎች አሉ
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

Sunday, June 29, 2014

በአ.አ ዩኒቨርሲቲ 52 ተማሪዎች በ”ዲሲፕሊን” ሰበብ ፖለቲካዊ ክስ ተመሰረተባቸው (ዝርዝራቸውን ይዘናል)

 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመብት ጥያቄ አንስተው በሃገራዊ ጉዳይ ነቃ ያለ ተሳትፎ የሚያደርጉ 52 ተማሪዎች ላይ የዲሲፕሊን ክስ መመስረቱ ተሰማ። የዲሲፕሊን ክስ የተመሰረተባቸውን ተማሪዎች ስም ዝርዝር የያዘውን ወረቀት በማህበራዊ ድረገጾች ላይ የለቀቁት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ክሱ የተመሰረተባቸው ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ በ2 ሰዓት በተማሪዎች ጽ/ቤት እንዲገኙ ት ዕዛዝ ተሰጥቷል።
ምናልባትም እነዚህ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ትኩረት አድርገው የሚንቀሳቀሱት ተማሪዎች ላይ በዲሲፕሊን ሰበብ ፖለቲካዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚችል የቅርብ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ያስታወቁ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ይህን እርምጃ ከወሰደ ሌላ የተማሪዎች አመጽ እንዲነሳ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ታዛቢዎች ይናገራሉ።
በዲሲፕሊንክ ክስ ሰበብ የፖለቲካ እርምጃ ሊወሰድባቸው የተዘጋጁት ተማሪዎች ስምዝርዝር የሚከተለው ነው፦
students 1

በአ.አ ዩኒቨርሲቲ 52 ተማሪዎች በ”ዲሲፕሊን” ሰበብ ፖለቲካዊ ክስ ተመሰረተባቸው (ዝርዝራቸውን ይዘናል)

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመብት ጥያቄ አንስተው በሃገራዊ ጉዳይ ነቃ ያለ ተሳትፎ የሚያደርጉ 52 ተማሪዎች ላይ የዲሲፕሊን ክስ መመስረቱ ተሰማ። የዲሲፕሊን ክስ የተመሰረተባቸውን ተማሪዎች ስም ዝርዝር የያዘውን ወረቀት በማህበራዊ ድረገጾች ላይ የለቀቁት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ክሱ የተመሰረተባቸው ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ በ2 ሰዓት በተማሪዎች ጽ/ቤት እንዲገኙ ት ዕዛዝ ተሰጥቷል።
ምናልባትም እነዚህ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ትኩረት አድርገው የሚንቀሳቀሱት ተማሪዎች ላይ በዲሲፕሊን ሰበብ ፖለቲካዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚችል የቅርብ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ያስታወቁ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ይህን እርምጃ ከወሰደ ሌላ የተማሪዎች አመጽ እንዲነሳ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ታዛቢዎች ይናገራሉ።
በዲሲፕሊንክ ክስ ሰበብ የፖለቲካ እርምጃ ሊወሰድባቸው የተዘጋጁት ተማሪዎች ስምዝርዝር የሚከተለው ነው፦
students 1

[የዞን 9 ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ] – ‹‹ያለ ፈቃድ መሬቱንም ፎቶ ማንሳት አይቻልም›› ፖሊስ

ጌታቸው ሽፈራው ከአዲስ አበባ
የጦማሪያኑን የፍርድ ውሎ የሚከታተለው ሰው ዛሬም እንደወትሮው በጠዋት ነው የተገኘው፡፡ አራት ሰዓት ካለፈ በኋላ የጦማሪያኑ ጠበቃ ‹‹መዝገብ ቤቷ ስለሌለች ነገ ከሰዓት ተብሏል›› ብለው ሲነግሩን በርካታ ህዝብ በተገኘበት አንዲት መዝገብ ቤት በመቅረቷ ብቻ የፍርድ ውሎው እንዲራዘም መደረጉ ገርሞን ስለጉዳዩ እያወራን ለጥቂት ደቂቃዎች ግቢው ውስጥ ቆየን፡፡ ከደቂቃዎች በኋላ ደግሞ እየመጡ ነው ተባለ፡፡
የውሎው ትዕይንት እዚህ ላይ ነው የተጀመረው፡፡
ሶስቱም ጦማሪያን ሲመጡ ህዝቡ በጭብጨባ ተቀበላቸው፡፡ በድንገት እዚህ እዚያ የሚራወጡት ፖሊሶች ወደተሰበሰበው ሰው እየሮጡ በመምጣት የሰማያዊ ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ አባል የሆነችውን ምኞት መኮንንን ‹‹ፎቶ ግራፍ አንስተሻል፡፡›› በሚል ማንገላላት ጀመሩ፡፡ በኃይል እየጎተቱ ሲወስዷትም ዮናታን ተስፋዬ ‹‹እኔን ውሰዱኝ›› ብሎ ምኞትን በኃይል እየገፈተሩ የሚወስዱት ፖሊሶች መሃል ገባ፡፡ ፖሊስ ግን እሱንም ማንገላላት ጀመረ፡፡ እሱንም አብረው ወሰዱት፡፡ ምኞትና ዮናታን ጦማሪያኑን ተከትለው ችሎቱ ወደሚገኝበት ቦታ ከተወሰዱ በኋላ ፖሊሶቹ ህዝቡ እንዲበተን ማስፈራራት ጀመሩ፡zone9-e1398747809895

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/31736

ከምእራብ ወለጋ ዞን ከጊምቢ ወረዳ እንዲሁም ከቀሌም ወለጋ ዞን የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ንብረታቸው ተዘርፎ ከአካባቢው እንዲወጡ ከተደረገ በሁዋላ፣ ችግራቸውን ለአማራ ክልል ርእሰ ማስተዳድር እንዲሁም ለፌደራሉ መንግስት ቢያመለክቱም የሚሰማቸው ማጣታቸውን ገልጸዋል።
ኢሳት ካነጋገራቸው የተፈናቃዮች ተወካዮች መካከል አንዳንዶች እንደገለጹት የአማራ ክልልም ሆነ የፌደራሉ መንግስት በክልሎች ጉዳይ ጣልቃ አንገባም በሚል ምክንያት ለጥያቄያቸው መልስ ለመስጠት ፈቃደኞች አልሆኑም። ከመንግስት የሚሰጠው መልስ ተስፋ እንዳስቆረጣቸውም ተፈናቃዮች ገልጸዋል

የሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ኪሳራ በሚነሶታ!  እውን አላሙዲ የገንዘብ ድጋፋቸውን ይቀጥሉ ይሆን?

የሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ኪሳራ በሚነሶታ!  እውን አላሙዲ የገንዘብ ድጋፋቸውን ይቀጥሉ ይሆን?