Wednesday, December 16, 2015

ጎንደር‬ የሚገኙት ባለስልጣናት ለሁለት ተከፍለው በመተማ ሸዲና አርማጭሆ ህዝቡን በመማፀን ላይ ናቸው

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ) በጎንደር‬ የሚገኙት የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ ባለስልጣናት በአሁኑ ሰዓት ለሁለት ተከፍለው ወደ መተማ ሸዲና አርማጭሆ አቅንተው ህዝቡን በመማፀን ላይ ናቸው፡፡
በትናንትናው ዕለት በጎንደር ጎሃ ሆቴል በነበረው ስብሰባ ላይ ገዱ አንዳርጋቸው የጎንደር ህዝብ በስርዓቱ ላይ ማመፁን ባፋጣኝ የማያቆም ከሆነ የክልሉ ልዩ ኃይል እና ፌደራል ፖሊስ ጦር ተቀናጅተው የማያዳግም የኃይል እርምጃ እንደሚወስዱ እሱ የሚመራውን ክልል አስተዳደር አቋም አስታውቋል፡፡


abay Tsehaye

በዛሬው ዕለት አባይ ፀሐዬ፣ ደመቀ መኮንን እና አምባቸው /የክልሉ ምክትል አስተዳዳሪ/ ወደ መተማ ሸዲ አምርተው በቦታው ያገኙትን ጥቂት ህዝብ ከአንገት በላይ የሆነ ጉንብስ ለመዋረድ እየጣሩ ይገኛሉ፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታም እንዲሁ በረከት ስምዖን፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ሙሉጌታ ወርቁ /የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር/ እና የክልሉ ልዩ ሃይል አዛዥ የሆነው ሰው ወደ አርማጭሆ ዘልቀው ከህዝብ ጫማ ስር በመውደቅ ላይ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ አጋንት፣ ጠንቋይ፤ ተብለው ዛሬም በወያኔዎች ተሰደቡ። – ከተማ ዋቅጅራ


ከተማ ዋቅጅራ
ከተማ ዋቅጅራ
ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ መቼስ የማንሰማው ነገር የለም 25 አመት ሙሉ በትግዕስቱ ታግሶዋቸው  የተቀመጠውን ህዝብ በየተራ እየተነሱ ማንቋሸሽ፣ መስደብ አላቆሙም። አሁንም እንኳን ሞት በራፋቸው ላይ ቆሞ መጥፊያቸው ግቢያቸው ገብቶ ስድባቸውን ቀጥለዋል። ይሄ የሚያሳየው ደግሞ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያላቸው ጥላቻ ካልጠፉ በስተቀር እንደማይተውት የሚያሳይ ነገር ነው።
የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር የኢትዮጵያን ወጣቶች ቦዘኔ፣ ፍንዳታ፣ በማለት ሲያጥላሉ እና ሲሳደቡ አሻንጉሊቶቹ  የፓርላማ  አባላት ያጨበጭቡና ይስቁ ነበር። የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ባገኘው አጋጣሚ እንደማይፈልጋቸው ሲነግራቸው ኖሯል። ህዝቡ እንዳልመረጣቸው ቢያስውቃቸው ምን ታመጣላችሁ በሚል እያንቋሸሹ፣ እየሰደቡ የጭቆና አገዛዛቸውን ቀጥለውበታል። ህዝብን የሚያክል ነገር መሪ በተባሉት አካል ቦዘኔ እየተባሉ በአደባባይ ሲሰደቡ የሚያሳፍር ቢሆንም ህዝቡ ግን ቦዜኔ ያለው ቤተ መንግስት ነው በማለት የቦዘኔ ጥርቅም ያለው ያለ እውቀታቸው እና ያለ ህዝብ ፍላጎት ተመርጠናል በማለት የተሰገሰጉበት መሆናቸውን ይነግራቸው ነበር።
በ97 የቅንጅት ሰልፍ ግዜ አጋዚ በሰላማዊ ሰው ላይ በወሰደው ኢሰባአዊ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ወያኔዎች የተወሰደው እርምጃ ትክክል ነው ባንክ ሊዘርፉ ሲሉ የነበሩ እና የተለያየ የሽብር ስራ ሊሰሩ የነበሩት ናቸው እርምጃ የተወሰደባቸው በማለት ከመጸጸት ይልቅ ያልተገባ ስም እየሰጡ መግደላቸውን እንደ ትክክለኛ ስራ አድርገው ሲነግሩን ህዝባችን ጥርሱን ነክሶ ዝም ከማለት ውጪ ምንም ያደረገው ነገር አልነበረም። ወያኔዎች የኢትዮጵያ ህዝብን በማንቋሸሽ እና በመስደብ የታወቁ ናቸው። በተቃራኒው ደግሞ የትግራይ ህዝብ ደግሞ በወያኔዎች አገላለጽ ወርቅ ትውልድ እንደሆኑ ይነግሩናል። ይሄ ደግሞ አንደኛ ዜጋ እና ሁለተኛ ዜጋ እንደሆንን አልገባን ከሆነ በግልጽ ነግረውን  እየሰሩበት ይገኛሉ።ለዚህ ነው ህዝባችንን ወራዳ፣ ፍንዳታ፣ ቦዘኔ ሌላም ሌላም እያሉ የሚሰድቡት። ዛሬ ደግሞ  በለመደው የስድብ አፋቸው አጋንት፣ጠንቋይ ብለው  ህዝባችንን በግልጽ በአደባባይ ሰድበውታል። ይሄ የሚያሳየው ለወያኔዎች የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ሰው አለመቁጠራቸው ነው። የሰው ልጅን አጋንት ተብሎ መሳደብ ያስቀጣል ወደፊትም ተጠያቂም ያደርጋቸዋል። ዛሬ ስልጣን ላይ ነይ ብለው በስልጣናቸው ተጠቅመው የፈለጉትን መናገርና መስራት እንችላለን ተብሎ ህዝብን የሚያል ማዋረድ ህዝብን ማንቋሸሽ አቋማቸው ሁሌም የማይለወጥ መሆናቸውን አሳውቀውናል እኛም ካወቅን ሰነበትን።  ህዝቡ ሲነሳ ነደድ እሳት እንደሆነ አልተገነዘባችሁ ይሆንን? ህዝብ ሆ ብሎ ተነስቶ እንደሚያጠፋችሁ ዘንግታችሁታል። ህዝብን ንቆ፣ አዋርዶ፣ አንቋሾ መኖር እንችላለን ብላችሁ ካሰባችሁ ዶክተር መራራ ጉዲና እንደተናገሩት እነሱ ከጫካው ወጡ እንጂ ጫካው ከነሱ አልወጡም የሚለው አገላለጽ ይገልጻችኋዋል። ዛሬም ከ25 አመት በኋላ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያላችሁ ጥላቻ አለመጥፋቱን በግልጽ ነግራችሁናል። ዛሬም የኢትዮጵያን ህዝብ ለመስደብ እና ለማጥፋት  እንደማይመለሱ በእርገጠኝነት አሳይታችሁናል።
እንግዲህ ዛሬ ያልነቃህ ካለህ ንቃ ያልተነሳህ ካለህ ተነስ። ኦፒዲኦ፣ ብአዴን፣ ደህዴን የሚባሉት ድርጅቶች ቀድመን እንደተናገርነው ደግመንም ደግመንም እንዳሳሰብነው የወያኔ መጠቀሚያ እንጂ ምንም የማይሰሩ በአገሪቷ ላይ ስልጣን የሌላቸው የሆድ አደር ጥርቅም እንደሆኑ ብዙሃኖቹ አስረግጠው ተናግረዋል። በየትኛውም አካባቢ ትዕዛዝ የሚያስተላልፉት ውሳኔ የሚሰጡት የክልሎች መንግስት ተብዬዎች ሳይሆን ወያኔዎች ናቸው። ከዚህ  መስመር በኋላ ኦፒዲኦ ነው የሚመለከተው ከዚህ መስመር በኋላ ብአዴን ነው የሚመለከተው ከዚህ መስመር በኋላ ደህዴን ነው የሚመለከተው በማለት ሁሉም አንድ ሆነው እንዳይሰሩ ለመለያየት የተጠቀመበት እንጂ ምንም የማይፈይዱ የወያኔ መጠቀሚያ የሆኑ አጥር እና ድርጅቶች ናቸው። ይሄንን አጥር እና የወያኔ ሴራ  ለአንደ እና ለመጨረሻ ግዜ መሰበሪያው ሰአት አሁን ነው። በአጥር ከልሎ አንዱ ወደ ሌላው እንዳይመጣ አንዱ ለአንዱ አጋር እንዳይሆን እናንተ አይመለከታችሁም ሁሉም የራሳቸው አስተዳዳሪ ስላላቸው ማንም ከራሱ ክልል ውጪ አይመለከታችሁም በሚል ሰበብ አራርቆ ወያኔ ግን ሁሉም ክልሎች ውስጥ በዋነኝነት እየሰራ ህዝባችንን አለያይቶ በተነጠል እያጠፋን ስለሆነ ነገሮችን በጥልቀት እና በብልጠት የምናይበት ግዜ ነው። ወያኔ ያስቀመጠው አጥር በማፍረስ ፍቅር አሸናፊ ነው አንድነት ሃይል ነው የኛ ጠላት ወያኔ ነው ብለን የከፋ ነገር ሳይመጣ አንድነታችንን በግልፅ እናውጅ። በአገር ቤትም በውጪም የምትኖሩ የተቃዋሚ ኃይሎች አንድ ነን ብላችሁ በአንድነት ተሳሰሩ በአንድነት ቁሙ ስለ አንድነት ዘምሩ ያኔ በአንድነት የተሳሰረ ህዝብ በአንድነት የፍቅር መዝሙርን ሲያሰሙ የወያኔ ምሶሶዎች ይፈርሳሉ ዛሬ አጋንት ብሎ ህዝባችንን የሰደቡ በፍቅር እና በአንድነት ስንቆም የእግዚአብሔር ኃይል ለብሰን የተሳዳቢዎችን አፋቸውን የመዝጋት ስልጣን እናገኛለን። የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ንቁ እንንቃ ሁሉም ህብረተሰብ አንዱ ለአንዱ ዘብ ይቁም አንዱ ለአንዱ መከታው ይሁን። ሁላችንም ሳንለያይ በመደጋገፍ ለወያኔ ሴራ ክፍተት ባለመስጠት ብንሰራ በአጭር ግዜ ድሉን በእጃችን ማስገባት ይቻላል ሰላምን ለኢትዮጵያ ማስፈን ይቻላል።
የወያኔን ፉከራ ባዶ ፉከራ ማድረግ የምንችለው ሳንከፋፈል ስንታገል ብቻ ነው። ስድባቸውን ማጥፋት የምንችለው በአንድነት ስንነሳ ብቻ ነው። ይሄ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ መልዕክቴ ነው። ህዝባችንን ለጭፍጨፋ አናጋልጥ ለህዝባችን ነጻነትን ለማምጣት በረሃ የወረዱትንም አሰልቺ ትግል እንዲጋፈጡ አናድርጋቸው። ነጻነት ማግኘት የምንችለው በረሃም ያሉት ከተማም ያሉት በውጪም ያሉት የአንድነት ድምጽ ሲኖረን ነው። ይሄ ካልሆነ ግን ትላንትና በአደባባይ ቦዘኔ፣ ፍንዳታ፣ ወራዳ ተብለን ተሰድበንና ተገድለን በመከራ እንዳለፍን ሁሉ ዛሬም አጋንት፣ ጠንቋይ ብለውን እየሰደቡን እየገደሉን እያዋረዱን ነው። በአደባባይ እየተሰደብን በአገራችን እየተገደልን ከቄአችን ላይ እየተፈናቀልን እንዳንኖር ሰላማችንን ማምጣት የምንችለው እኛው ነን። ወያኔ እንደሆነ መቼም መለወጥ የማይችሉ ናቸው። መለወጥ ያለብን እኛው ለውጥን ፈላጊ ሰላምን ናፋቂዎቹ ነን።

የመጨረሻው ድል የፍትህ: የሰላም፡የፍቅር ነው። በዘር በክልል መከፋፈል ከመለስ ጋር ሞቷል



ቢላል አበጋዝ
ዋሽግተን ዲ ሲ
ረቡዕ ፣ ዲሴምበር 16 ቀን 2015
እንደዛሬው ወያኔ ኢህአዴግ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ግልጽ በሆነ መንገድ ፍላጎቱን በትክክል፤ የሚሄድበትን መንገድ ወለል አርጎ ያሳየበት ጊዜ የለም።ፍላጎቱ ስልጣን፤ዘዴው በጭካኔ መርገጥ፤ ይህ ካልሰራ አገር መበተን ነው።ይህን ማንም አሽቃባጩ ማንም ይቅርታ ጠያቂው ሊከላከልበት የሚችለው አይደለም።ከዚህ ወዲያ በጭካኔ የመርገጥ ተግባሩን ይበረታበታል እንጂ የሚቀንስው አይደለም።የህዝቡን እምቢተኝነት “የሽብርተኛ” ማለቱ የምዕራቡን ዓለም እገዛ ለማግኘት፤ከተጠያቂነትም የሚድን መስሎት ነው።

abebe Gelaw

የህወሃት ማከላዊ ኮሚቴ በሁለት ተከፍሎ ይህም ማለት ለህዝቡ እምቢተኝነት ፖለቲካዊ መፍትሄ መስጠትና እንደወትሮው በጭካኔ መርገጥ ላይ ቢዶልት፤ጨፍጭፍ፤ እርገጥ የሚለው ክፍል ያቸነፈ መሆኑ በኦሮሚያ ወታደራዊ አዋጅ መታወጁ አመላካች ነው።የሚሄድበትን መንገድ ወለል አርጎ ያሳየበትም ይኸው ነው።
ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሀይሎች ዛሬ የሚሰሩት ስተት ቢኖር በኦሮሞ ኢትዮጵያ የተነሳውን አመጽ አንዱ ክፍል የተወሰነ፤የኦሮሞ ብቻ አድርጎ ማሰብ፤ኦሮሞች የሆኑ ደግሞ የብቻ ትግላቸው አድርገው ካዩት ነው።እኒህ ዳር ና ዳር ያሉ የጽንፈኝነት ሰለባ አመለካከቶች ለወያኔ የሚመቹ የኢትዮጵያን ህዝብ ለቀጣይ ባርነት ይሚዳርጉ ናቸው።የወያኔ ኢህአዴግ ፍላጎቶችች ጋር የሚናበቡ ጽንፎች ናቸውና።
የህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ትግል መራመድ እነዚህን ከላይ ያነሳኋቸውን ጽንፈኝነቶች እያከሸፈ ወያኔ ጋር መጋፈጥ ይኖርበታል። ደስ የሚያሰኘው ወጣቱ እኒህን ጽንፎች እያከሸፈ መሆኑ ነው። እኒህ ጽንፎች በኦሮሞው በኩል የዛሬው ጉዳት፤ሞትና ስቃዩ ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ ያለፈ ታሪክን ይዘው ለጥርጣሬ በር ይከፍታሉ።በአማራው በኩል ያሉት ጽንፈኞች ደግሞ አማራው ሲበደል ኦሮሞው መቸ አገዘ ይላሉ።በዚህ ክርክር የጋምቤላው የአፋሩ የሶማሉ የደቡቡ በደል መነሳቱ ይቀራል።በዚህ መሃል ወያኔ ኢህአዴግ ፋታ ያገኛል ማለት ነው።ወያኔ ኢህአዴግን የሚጥለው አገር አቀፍ ህዝባዊ አመጽ ነው።አንድ ባንድ ተራ በተራ ለገጠሙት ብርታት የለውም ማለት ወያኔ ላይ የዋህ ግምት ማድረግ ነው።
ወያኔ ኢህአዴግ በህዝቦች መካከል ክፉ ልዩነቶችን ቢያጣ እራሱ በጥረቱ ያሰናዳቸዋል።ይቀምማቸዋል።በጎንደር እያደረገ ያለውን በክልል ውስጥ ክልል መፍጠርን፤የቅማንት ህዝብን ጥያቄ ማራገብን ማመልከት ብቻ ይበቃል።እንዲህ ያሉትን ዘዴዎች ትቶ ለምን ከነጭርሱ ኤርትራ ወረረችኝ አይልም ?ይህንም ይላል።ግን ትልቅ ካርዱ ሰለሆነ ያቆየዋል። ኤርትራን ይተነኩስ እንደሆን እንጂ ኤርትራ ኢትዮጵያን የምትወርበት ምክንያት ዛሬ የለም።ኤርትራ የኢኮኖሚ ችግርዋን መልክ ማስያዝ ላይ እንዳለች እየተነገረ ከሆነ ቆይቷል።
አፍጥጠው ያሉት የቀይ ባህር ባሻገር ሀብታም አረብ አገሮች ዛሬ ወያኔን በገለልተኝነት አቌም ያዩታል እንጂ ለወያኔ ኢህአዴግ መሰናበት አይጨነቁም።እንዲያውም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አገር ወዳድ መንግስት ሳይቆም የኔ የሚሉት ሀይል ከዚህ ወያኔ ሊያራግበው ከሚመኘው እሳት መሃል እንዲወጣላቸው የኢትዮጵያን ጉዳይ መያዣ እዲኖራቸው ይፈልጋሉ።ይህን ደግሞ የሚገልጸው ከየመን በኋላ ሀብታም አረብ አገሮች ፈርተዋል።ሰግተዋል።ምንም ከማድረግ አይመለሱም።ኢትዮጵያ የወትሮ ምኞታቸው፤የወትሮም ስጋታቸው ናትና። የህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ትግሉን የሚያዛንፉ ሌላ ሀይሎች እነሱ ናቸው እላለሁ።ጠላት ወያኔ ኢሃዴግ ብቻ አይደለም።
ዛሬ በኢትዮጵያ ወያኔ ህወሃት በግድያ፤ በድብደባ ሊገታው የማይችለው አመጽ ተነስቷል።ከኢትዮጵያ ውስጥም ይሁን ከውጭ ዜጎች ስጋት ባለበት መንፈስ ሁኔታውን እየተከታተሉ ነው። የወያኔ የፖሊስና ወታደራዊ ሀይል በትንሹ እንኳን ቢነቃነቅ የወያኔ ህልውና የመጨረሻዎቹ ሰዓቶች መድረሳቸው አመላካች ነው።ወያኔ ይህን ያህል በቋፍ ነው። ያውቀዋል።ጥያቄው የአሁኑ የየካቲት 1966 ዓም ድጋሚ ይሆን ? ነው።
ወያኔ መግደል ይችላል።የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት የዴሞክራሲ ትግል ሊገታ ግን አይችልም።የፋሺስት ኢጣሊያ ጭፍጨፋን ታዝቦ ለታሪክ ያቆየው አንድ የሁንጋሪያ ሰው የፋሺስ ኢጣልያ የአረመኔ ድርጊት ኢትዮጵያ በሚለው መጽሀፉ መጨረሻ እንዲህ ብሏል “በደምና በስቃይ ላይ የተገነባ፤በደምና በገጠጠ ውሸት ላይ የተመረኮዘ ይወድቃል።ከመቸውም ጊዜ በበለጠ የመጨረሻው ድል የፍትህ: የሰላም፡የፍቅር ነው።”
ድል ለዲሞክራሲያዊ ሀይሎች ሁሉ!
ኢትዮጵያ በአንድነትዋ በነጻነት ለዘለዓለም ትኑር