Thursday, February 25, 2016

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስተር በአንዳርጋቸው እና በሌሎችም ጉዳዮች ለመነጋገር ወደ አዲስ አበባ ሊያቀኑ ነው

(ዘ-ሐበሻ) የመን ላይ በሕወሓት መንግስት ተጠልፈው በአዲስ አበባ ባልታወቀ ቦታ ታስረው እየተሰቃዩ የሚገኙት ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌን በተመለከተ እንዲፈቱ ያሳዩት ባህሪ ለዘብተኛ ነው በሚል የብሪታኒያ ታዋቂ ግለሰቦችና የፓርላማ አባላት ያካተተ የ135ሺ ፌርማዎችን ለጠቅላይ ሚንስትሩ ዴቭድ ካሜሮን ካስገቡ በኋላ ጠቅላይ ሚንስትሩ በቅርቡ ለጉብኝት ወደ አዲስ አበባ እንደሚሄዱ የሃገሪቱ ሚድያዎች ዘገቡ

Andargachew Tsige David Cameron




ዴቭድ ካሜሮን በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ጉብኝት በተመለከተ የብሪታኒያ የኢሚግሬሽንና ዜጎች እንዲሁም ተጓዳኝ ጉዳዮችን የሚከታተለው ሆም ኦፊስ ምክትል ቋሚ ፅሃፊ የሆኑት ኦሊቨር ሮቢንስ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር በመዲናችን አዲስ አበባ እየተወያዩ እንደሚገኙ ምንጮች አስታውቀዋል::
ዴቭድ ካሜሮን ወደ ኢትዮጵያ ሲሄዱ የአቶ አንዳርጋቸውን መለቀቅ እንደ አንድ አጀንዳ እንደሚያነሱት የሚጠበቅ ሲሆን ይህም በዚህ ጉዳይ ለዘብተኝነት አሳይተዋል በሚል ለደረሰባቸው ወቀሳ ምላሽ ለመስጠት ነው የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች አሉ::
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በኢትዮጵያ የት ታስረው እንደሚገኙ ባይታወቅም በቅርቡ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር የሆኑት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ “በአባታቸው እየተጎበኙ” እንደሚገኙ መረጃ አለን ብለዋል:: አቶ አንዳርጋቸውም በቅርቡ ከ እስር ካልተለቀቁ የአ እ ምሮአቸው ሁኔታ አስጊ እንደሆነ የ እንግሊዝ ዲፕሎማቶች መግለጻቸውን ዘ-ሐበሻ መዘግቧ አይዘነጋም::

No comments:

Post a Comment