Thursday, September 29, 2016

በብር ሸለቆ ወታደራዊ ካምፕ የአማራ እስረኞች በከባድና በተከለከሉ አፍዝ አደንግዝ መርፌ መድኃኒቶች እንደሚሰቃዩ መረጃዎች አመለከቱ



screen-shot-2016-09-29-at-7-07-53-am





ክሙሉቀን ተስፋው


መስከረም 19, 2009 ዓ.ም አስደንጋጭ እና አሳሳቢ
በብር ሸለቆ ወታደራዊ ካምፕ የሚገኙ ወገኖቻችን በከባድና የተከለከሉ አፍዝ አደንግዝ መርፌ መድኃኒቶች እንደሚሰቃዩ መረጃዎች አመለከቱ። ብር ሸለቆ የታሰሩ የዐማራ ወጣቶች በግዴታ በመርፌ እንዲወስዱ የተደረገውን መድኃኒት ምንነት የሚያስረዳ ምስል ትናንት ወጥቷል። በዚሁ መሠረት የዐማራ ሀኪሞች ማኅበር መድኃኒቱን በተመለከተ የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥቷል።
ሁሉም የሰውነት ጡንቻወች እንዲዝሉ ወይም አላግባብ እንዲወጠሩና የፈለጉን አሰቃቂ ድርጊት ለመከወን (አስንፎ ለመምታት፣ ለማንጠልጠል፣ ለመግደል..) የሚያስችሉ አፍዝ አደንግዝ(Sedative Hypnotic) የሆኑትን የመርፊ መድኃኒቶች በግዳጅ እየተውጉ ነው። ዲያዘፓም እና ዲልትያዘም (Diazepam Diltiazem) ጥቂቶቹ ናቸው። እነዚህ መድኃኒቶች ለሚያስፈልገውና በሃኪም ትዛዝ ብቻ የሚሰጡ፡ ከፍተኛ ቁጥጥርና ክትትል የሚያስፈልጋቸው ናቸው። ከመጠን በላይ(Over Dose)ና ለማያስፈልገው ከተወጉ የመናገር ችግር፡ የሰውነት ክፍል መዛል: አለመታዝዝ (Dyskinesias): እረፍት መንሳት(akithsia)፡መደበት(Depression) ጭንቀት እና መተንፈስ ኣለመቻል ያስከትላሉ። በብዛትና በተክታታይ ከሆነ የልብ መድከም፡ የደም ማነስ፡ ሾክ፡የሚጥል(Sezure)፡ ራስን ማሳት(Coma)ና ሞት ያመጣሉ። የሳይኮሎጅ ማስቀየር ‘Psychologic Dislocation’ ና ፍላጎት ማሳጣትም ጉዳቶች ናቸው። ቆዳ ላይ ከፈሰሱ የቆዳ ላይ ቁጣ፡መላላጥ፡ እብጠት፡እንፊክሽን፡የቆዳ ጋንግሪንና ሞት የመጨረሻወቹ ናቸው።
ናዚውና ኢሰብዓዊ ህውሃት ኣካላዊ ስቃይ ንጹሃን ላይ እንደሚያደርስ ለማንም ግልጽ ነው። ኣስደንጋጩ የህክምና ማስቃያ ግን ኣማራው ላይ የመጀመሪያው ሳይሆን ኣይቀርም። የሚያስፈራው የህክምና ሰወች (የናዚ ዶክተሮች) ለዚህ ኦፕሪሽን መሳተፋቸው ነው።


ይህ ኢሰባዊነትና አለማቅፋዊ የህክምና ሰነምግባርን የጣሰ ሆኖኣል። ሰውን በግፍ ኣለመጉዳት ’Do Not Harm’ ፡ፍቃደኛ ለሆኑ ብቻ ‘Authonomy’ ፡ የሚጠቅም ሲሆን ብቻ ‘Beneficience ’ ወዘተ የሚሉት ቃለ-ማህላ(Physicians Oath) ተክደው በ’ናዚ ሃኪሞች’ ህዝባችን እየተስቃየ ነው ። የአማራና የኢትዮጵያ ሃኪሞች ይህን ጉዳይ ባስቸኩይ ለ’ Federal Ministry of Health of Ethiopia, FMHACA, UN Human Rights ‘ ማድረስና እልባት ማግኘት ኣለበት።
መረጃውን በጥንቃቄ እየያዝን ተግጅወችን እንርዳ። መልእክቱን ለአለም አናሰራጭ







No comments:

Post a Comment