Sunday, October 2, 2016

ከእሬቻው ጭፍጨፋ በኋላ የአምቦ ሕዝብ ተነሳ | የተቆጣው ሕዝብ በርካታ የመንግስት መኪኖችን አቃጠለ



ambo


 (ዘ-ሐበሻ) የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ኦሮሞዎችን እና አማሮችን በ እሬቻ በዓል ቢሾፍቱ ላይ ዛሬ ከጨፈጨፈና ከ500 በላይ የሰው ሕይወት ካጠፋ በኋላ በአምቦ ሕዝብ በቁጣ ተነሳ:::
በአምቦ በተነሳው ሕዝባዊ አመጽ ሕዝቡ ቁጣውን በመንግስት ንብረቶች ላይ እርምጃ በመውሰድ እየገለጸ ነው:: እንደዘ-ሐበሻ ዜና ምንጮች ገለጻ ከሆነ በአምቦ በርካታ የመንግስት መኪኖች እና አንዳንድ መስሪያ ቤቶች በ እሳት ወድመዋል:: ይህን ተቃውሞ ሊያረግቡ በመጡ የሕወሓት ወታደሮች ላይም እርምጃ መውሰድ የጀመረ ሲሆን ወታደሮች እየሸሹ መሄዳቸው ተሰምቷል::
በአምቦ መንገዶች መዘጋጋታውም ተሰምቷል::
የአምቦ ሕዝብ እጅጉን ከመቆጣቱም ባሻገር በሌሎች የኢትዮጵያ ክልል ከተሞችም እንዲሁ ይህው ሕዝባዊ ተቃውሞ እንደሚቀጥል ይጠበቃል::

No comments:

Post a Comment