Monday, October 3, 2016

ለኦሮሞ ኢትዮጵያዊያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን(ከአማራ ተጋድሎ ግብረ ኃይል በዉስጥ መስመር የተላከ)

14355189_1776743355901679_4397046954836303499_n
በትላንትናው ዕለት በቢሾፍቱ ከተማ ሲከበር በነበረው አመታዊ የእሬቻ በአል ላይ ለመታደም ከመላው ኦሮሚያና ከተለያዩ የሀገራችን አባቢዎች በመጡ ተሳታፊዎች ላይ የህዝባዊ ወያነ ሀርነት ትግራይ ጦር በፈፀመው አስከፊ የጦር ወንጀል ቁጥራቸውን ለመገመት የሚያዳግቱ ወገኖቻችንን ተነጥቀናል፡፡ በዚህም የወገኖቻችን ህልፈተ-ህይወት የተሰማን ሀዘን በጣም ጥልቅ ነው፡፡ የእነዚህ ኦሮሞ ወንድሞቻችን ሞት የእኛም የአማራዎች ሞት፡ የፈሰሰው ደማችውም የእኛም ደም መሆኑን እደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ በቃላት ሳይሆን አብረን በመሞትና ደማችንን በማፍሰስ አንድ መሆናችንን አረጋግጠናል፡፡ ወደፊትም በልበ-ሙሉነት እጅ ለእጅ ተጣምረን በፍፁም ወንድማማችነትና መተማመን መንፈስ ይሀንን ሰው-በላ የወንበዴ ጥርቅም ከላያችን ላይ በማሽቀንጠር ለዘለዓለሙ እንዳይነሳ በመቅበር ለሁላችንም የኢትዮጵያ ህዝቦች እኩል የምትሆን አዲስ ቤት በመገንባት በደም የተሳስረውን አንድነታችንን ዳግም የምናድስበት ቀን እሩቅ አይሆንም፡፡ የኦሮሞ ህዝብ ሞትና ደም መፍሰስ የአማራ ህዝብም ሞትና ደም መሆኑን በድጋሜ እያረጋገጥን ወደፊት በሚጠብቀን መራራ የነፃነት ትግል ጉዞ ትላንት የወደቁትን ዜጎቻችን በማሰብ በድል እንገሰግሳልን፡፡
ኢትዮዽያ ለዘላለም ትኑር!!
#AmharaResistance

No comments:

Post a Comment