Monday, October 13, 2014

Hiber Radio: በአሜሪካ አንድ ሐበሻ ኢቦላ ይኖረዋል በሚል ተጠርጥሮ ተያዘ፤ ኢቦላ አለብኝ ብሎ የቀለደው አሜሪካዊ ከአውሮፕላን ለመውረድ ተገደደ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
የህብር ሬዲዮ ጥቅምት 2 ቀን 2007 ፕሮግራም !
<... የዓለም ባንክ የሚሰጠው ገንዘብ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለልማት ጥቅም አይውልም። ጥቂቱም ፍትሃዊ በሆነ መንገድ አይደለም የሚውለው ኢትዮጵአ ትግራይ ብቻ አይደለችም ። ገንዘቡ ለጭቆና ሕዝብ ለማፈናቀል እየዋለ መሆኑን ከ78 አገሮች ከመጡ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ባሉበት ጉባዔ ተገኝቼ ባንኩ የሚሰጠው ብድር ለሰብዓዊ መብት ጥሰት መዋሉን ገልጫለሁ ትልቅ መድረክ ነበር ጉዳያችን ትኩረት አግኝቷል ።የተለያዩ አገራት ጋዜጠኞችም የኢትዮጵያን ጉዳይ አንስተው... >>
አቶ ኦባንግ ሜቶ በዓለም ባንክና አይ.ኤፍ.ኤም ዓመታዊ ጉባዔ ላይ ተገኝተው ስላቀረቡት ተቃውሞ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ምላሽ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)
<<...የኢቦላ መተላለፊያን በደንብ ማወቅ የጥንቃቄ እርምጃ መውሰድ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ። እስካሁን የሞቱት በኢቦላ የተያዙና የህክምና ሰዎችም ቢሆን በቀጥታ ከኢቦላ ጋር ግንኙነት ያላቸው ጋር የተገናኙ ያስታመሙ ናቸው ...የኢቮላ ጉዳይ ለአገሬም ለኢትዮጵያ ያሰጋኛል ። እንደ አሜሪካ በቂ አቅም ስለሌለ...>>
ዶ/ር ኤፍሬም መኮንን ኢቦላና ትኩረት ሊያገኙ የሚገባቸው የጥንቃቄ እርምጃ አስመልክቶ ከሰጡን ሙያዊ ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡት)
በዳላስ ከቤቷ ወጥታ ዛሬም ድረስ ዱካዋ ስላልተገኘው ኢትዮጵያዊቷ ወ/ሮ አልማዝ ጉዳይ (ልዩ ቃለ መጠይቅ ከጋዜጠኛ ዘውገ ቃኘው ጋር ከዳላስ ሙለውን ያዳምጡት)
የኬኒያው ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ውሎ (ልዩ ዘገባ)
ዜናዎቻችን
በአሜሪካ አንድ ሐበሻ ኢቦላ ይኖረዋል በሚል ተጠርጥሮ ተያዘ
ኢቦላ አለብኝ ብሎ የቀለደው አሜሪካዊ ከአውሮፕላን ለመውረድ ተገደደ
የኢቦላ በሽተኞች በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ላይ መገኘታቸው ተገለጸ
አገዛዙን የፈሩ የህክምና ባለሙያዎች በይፋ አልናገርም ብለዋል
መኢአድ በጋምቤላ ፣በሱማሌ እና በጉራ ፈርዳ የተፈጸመውን የዘር ማጥፋት አስመልክቶ የተቃውሞ ሰልፍ ሊጠራ መሆኑን ገለጸ
በሱማሌ ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ ሰራዊት የሆኑ የጦር መሳሪያዎች በሕገወጥ እየተሸጡ ነው
አልሸባብ ከሽያጩ ሰፊ ትርፍ ማግኘቱ ተገለጸ
የቀድሞው መንግስት ባለስልጣን ሌ/ኮሎኔል ደበላ ዲንሳ <<ሞቶ መኖር>>(ዱአኒ ጂራቹ) መጽሐፍ ተመረቀ
ኢ/ር ግዛቸው ከአንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንትነታቸው በፈቃዳቸው ለቀቁ
አቶ በላይ ፈቃዱ አዲሱ የአንድነት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል
በደቡብ ኢትዮጵያ ኑሯቸውን በአደን ያደረጉ 24 ሰዎች ሰሞኑን በተከፈተባቸው ጥቃት ተገደሉ

No comments:

Post a Comment