Tuesday, October 21, 2014

Hiber Radio: ኢትዮጵያ የኢቦላ ተጠርጣሪዎችን ናሙና ወደ ኬኒያ እንደምትልክ አንድ የአገሪቱ ባለስልጣን ገለጹ; * ካራቱሪ በኪሳራ ሳቢያ መሬቱን አሳልፎ እየሸጠ መሆኑ ተጋለጠ

የህብር ሬዲዮ ጥቅምት 9 ቀን 2007 ፕሮግራም !
<... የተሰደድነው ጋዜጠኞች ደህንነታችን ዛሬም ስጋት ላይ ነው...ገደኛህን አስታመህ ሞቶ እሱኑ ሬሳውን እንኳን ለመሸኘት ለስንብት ዕድል ስትነፈግ ያሳዝናል። አገዛዙ ያው የለመደወን ነው ያደረገው ውሸት ስራቸው ነው። ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹርቤ እንደማናችንም በጫና ነው ስራውን ያቆመው እና የተሰደደው እነሱ ግን በአስከሬኑ እንኳን ፕሮፖጋንዳ ሊሰሩበት ነው። ይህ ያሳዝናል።ወቅታዊ ምላሽ ለሰጡ ወገኖቻችን ግን... >>
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ የቃል ኪዳን መጽሔት ባለቤትና ማኔጂንግ ዳይሬክተር በስደት ካለበት ኬኒያ የአገዛዙ ሰዎች እንዴት በሞት የተለየውን የሙያ አጋሩን እንኳን መሰናበት እንደከለከሉት ለህብር ሬዲዮ ከሰጠው ምላሽ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)
<... በምርጫ አሁን ያለው ስርዓት ይወርዳል የሚል ዕምነት የለኝም። በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ተቃዋሚዎችን ተስፋ እያስቆረጥኩ አይደለም። ግን ምርጫ እንገባለን አንገባም ሳይሆን አስቀድመው የሁኔታዎች ትንተና ጥናት መስራት አለባቸው ። የምርጫ ህጎቹን ስታይ ፣የምርጫ አስፈጻሚውን ስትመለከት ሁኔታው ግልጽ ነው።...በምርጫ 2002 ሕዝቡ ሳይመርጥ 99.6 በመቶ አሸነፍን ተብሏል አሁን እንደውም የመለስን ራዕይ እናሳካለን በሚል መቶ በመቶ ለመጠቅለል ነው የሚሰሩት ። በዕኔ ዕምነት ከጠየከኝ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ በምርጫ ከስልጣን ማውረድ አይቻልም...>
አቶ ኤርሚያስ ለገሰ የቀድሞ በስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ(ሙሉውን ያዳምጡት)
ኢቦላ እና ዛሬም ያልተቀረፈው ስጋት በአሜሪካ (ልዩ ዘገባ)
ዜናዎቻችን
ኢትዮጵያ የኢቦላ ተጠርጣሪዎችን ናሙና ወደ ኬኒያ እንደምትልክ አንድ የአገሪቱ ባለስልጣን ገለጹ
ሰፊ መሬት በኢትዮጵያ ያለው ካራቱሪ በኪሳራ ሳቢያ መሬቱን አሳልፎ እየሸጠ መሆኑ ተጋለጠ
በኢትዮጵአ በስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ በምርጫ ማውረድ እንደማይቻል የስርዓቱ የቀድሞ ሚኒስትር አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ገለጹ
አቶ ሌኒጮ ለታ ምክትላቸውን ተከትለው አዲስ አበባ በቅርብ ቀን እንደሚገቡ ድርጅታቸው አስታወቀ
የዶ/ር ዲማ ነጎ ኢትዮጵአ መግባት አነጋጋሪ ሆኗል
ኤርትራ ውስጥ የመንግስት ለውጥ ያስፈልጋል ያሉ አንድ የተባበሩት መንግስታት ኤክስፐርት ስልጣናቸውን ለቀቁ
ኤርትራ አልሸባብን ሳይሆን የኢትዮጵያን ትጥቅ ያነሱ ተቃዋሚዎች እንደምትረዳ ተገለጸ
ሌሎችም ዜናዎች አሉ
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--

No comments:

Post a Comment