Friday, September 25, 2015

በሕዝብ ጫና የሕወሓት መንግስት የአቡነ ጴጥሮስን ሐውልት ወደ ቦታው ሊመልስ ነው

abune_petrosየአቡነ ጴጥሮስን ሐውልት ከስፍራው በልማት ስር አንስቶ ታሪክን ሊያጠፋ ነበር ተብሎ ሲተች የነበረው የሕወሓት አስተዳደር ሕዝቡ በአደባባይ ይህን ታሪክ ሐውልት እንዲመልስ ባደረገው ጫና መሰረት ወደ ቦታው ሊመልስ መሆኑ ተሰማ:: መንግስታዊው ራድዮ ፋና “የአደባባይ ዲዛይን ስራ እየተገባደደ በመሆኑ የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት በቅርቡ ወደ ቀድሞ ስፍራው እንደሚመለስ ተገለፀ” በሚል ዜናውን ቢያስነብብም ሕዝቡ አሁንም ሐውልቱ እስኪመለስ ድረስ ተቃውሞውን እንደሚቀጥል ታውቋል:: በተለያዩ ሶሻል ሚድያዎችም ሐውልቱ ቦታው እስኪመለስ እንጮሓለን የሚሉ መል ዕክቶች እየተሰራጩ ነው:: መንግስታዊው ራድዮ ፋና ስለሐውልቱ ወደ ቦታው ሊመለስ መሆኑን እንደሚከተለው ዘግቦታል:: እንደወረደ እነሆ:- አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2008 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት የሚያርፍበት አደባባይ ዲዛይን ዝግጅት የመጨረሻ ምእራፍ ላይ የደረሰ በመሆኑ ግንባታ ተካሂዶ ሀውልቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ቀድሞ ስፍራው እንደሚመለስ የፌደራል የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ደስታ ገለፁ። አቶ ዮናስ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ ሀውልቱ የሚያርፍበት አደባባይ ገፅታ እና ይዘት ምን መምሰል አለበት ለሚለው የመጨረሻ መልስ ለመስጠት የቀላል ባቡሩ ስራ የሚጀምርበት ጊዜ ሲጠበቅ ቆይቷል። ይህም ያስፈለገው ባቡሩ በሚንቀሳቀስበት ወቅት የሚፈጠረውን ንዝረት አጥንቶ የአደባባዩን ዲዛይን ማጠናቀቅ ስላስፈለገ ነው ብለዋል። አደባባዩ ሊኖር የሚችለውን ንዝረት በተግባር ተፈትሾ መገንባቱ ወደፊት ሀውልቱ ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስበት ያደርጋልም ነው ያሉት። - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46910#sthash.QiEq1E2e.dpuf       ታሪካዊው የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ሲነሳለፈው እሁድ ቀደም ሲል ሀውልቱ የነበረበትን ስፍራ የሚያካልለው የሰሜን-ደቡብ የአዲስ አበባ የቀላል ባቡር መስመር አገልግሎት በመጀመሩ የንዝረት መጠኑን በተመለከተ መረጃዎች እየተሰበሰቡ መሆናቸውን አቶ ዮናስ አስረድተዋል።
መረጃ የመሰብሰቡ ስራ እንዳበቃም የአደባባይ ዲዛይኑ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ይገባል፤ ከዚያም ሀውልቱ በቀድሞ ስፍራው ይተከላል ብለዋል።
ለአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት ግንባታ ሲባል 2005 ዓመተ ምህረት ሚያዚያ ወር ላይ የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ከቆመበት ተነቅሎ በብሔራዊ ሙዚየም
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46910#sthash.QiEq1E2e.dpuf

No comments:

Post a Comment