Tuesday, January 26, 2016

በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች ግድግዳዎች ላይ የተቃውሞ ጽሑፎች ተጽፈው አደሩ


(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች በሚገኙ ግድግድዎች ላይ በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት የሚቃወሙና ጥያቄም የሚጠይቁ መፈክሮች ተጽፈው አደሩ:: በተለይ መንግስት ያሰራቸውን የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ፍርድ የሚቃወም; በሃገሪቱ በተቃዋሚዎች ላይ የሚሰጡ ፖለቲካዊ ፍርዶችን የሚቃወሙ; በኦሮሞ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ግድያ የሚያወግዙና ሌሎችም መፈክሮች በትላልቁ በግድግዳዎች ላይ ተጽፈው አድረዋል::
ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ተቃውሟቸውን በስርዓቱ ላይ ቢያሰሙም በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የሕዝቡን ጥያቄ ወደ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚል አሁንም በርካታ ጋዜጠኞችን; የሃይማኖት መሪዎችን; የፖለቲካ ሰዎችን አስሮ በማሰቃየት እንዲሁም በመግደልም ላይ ይገኛል::
በአዲስ አበባ ግድግዳዎች ላይ ተጽፈው ያደሩ ተቃውሞዎችን በፎቶ ይመልከቱ::

addis ababa1addis ababaaddis ababa 3addis ababa2

ፍ/ቤቱ በአቶ ዮናታን ተስፋየ ላይ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ



‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› ዮናታን ተስፋየ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለ2ኛ ጊዜ የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል፡

yonatan Tesfaye
ዛሬ ጥር 17/2008 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበው አቶ ዮናታን ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም በሚል የጠየቀበትን ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ ለየካቲት 15/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ አቶ ዮናታን ተስፋየ የዋስትና መብቱ እንዲከበርለት ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡
ፖሊስ በአቶ ዮናታን ላይ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ሲጠይቅ ‹‹የቴክኒክ መረጃዎችን መሰብሰብ ይቀረናል፤ ያልተያዙ ግብረ አበሮችንም አሉ›› የሚል ምክንያት ማቅረቡን የተጠርጣሪ ጠበቃ ገልጸዋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ በጠበቃ እና በቤተሰቦቹ እንዳይጎበኝ እንደተከለከለና ከታሰረበት ክፍል መታፈን የተነሳ የጤና እከል ቢገጥመውም ህክምና እንዳላገኘ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን አድምጦ በጠበቃውም ሆነ በቤተሰቦቹ እንዲጎበኝ እንዲፈቀድለትና ህክምናም እንዲያገኝ ትዕዛዝ መስጠቱን ከጠበቃው ለማወቅ ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ከችሎት ሲወጣ በስፍራው ለነበሩት ቤተሰቦቹና ወዳጆቹ ያለውን ፍቅር ገልጾ ‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› በማለት ጮክ ብሎ ሲናገር ተደምጧል፡

Wednesday, December 16, 2015

ጎንደር‬ የሚገኙት ባለስልጣናት ለሁለት ተከፍለው በመተማ ሸዲና አርማጭሆ ህዝቡን በመማፀን ላይ ናቸው

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ) በጎንደር‬ የሚገኙት የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ ባለስልጣናት በአሁኑ ሰዓት ለሁለት ተከፍለው ወደ መተማ ሸዲና አርማጭሆ አቅንተው ህዝቡን በመማፀን ላይ ናቸው፡፡
በትናንትናው ዕለት በጎንደር ጎሃ ሆቴል በነበረው ስብሰባ ላይ ገዱ አንዳርጋቸው የጎንደር ህዝብ በስርዓቱ ላይ ማመፁን ባፋጣኝ የማያቆም ከሆነ የክልሉ ልዩ ኃይል እና ፌደራል ፖሊስ ጦር ተቀናጅተው የማያዳግም የኃይል እርምጃ እንደሚወስዱ እሱ የሚመራውን ክልል አስተዳደር አቋም አስታውቋል፡፡


abay Tsehaye

በዛሬው ዕለት አባይ ፀሐዬ፣ ደመቀ መኮንን እና አምባቸው /የክልሉ ምክትል አስተዳዳሪ/ ወደ መተማ ሸዲ አምርተው በቦታው ያገኙትን ጥቂት ህዝብ ከአንገት በላይ የሆነ ጉንብስ ለመዋረድ እየጣሩ ይገኛሉ፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታም እንዲሁ በረከት ስምዖን፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ሙሉጌታ ወርቁ /የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር/ እና የክልሉ ልዩ ሃይል አዛዥ የሆነው ሰው ወደ አርማጭሆ ዘልቀው ከህዝብ ጫማ ስር በመውደቅ ላይ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ አጋንት፣ ጠንቋይ፤ ተብለው ዛሬም በወያኔዎች ተሰደቡ። – ከተማ ዋቅጅራ


ከተማ ዋቅጅራ
ከተማ ዋቅጅራ
ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ መቼስ የማንሰማው ነገር የለም 25 አመት ሙሉ በትግዕስቱ ታግሶዋቸው  የተቀመጠውን ህዝብ በየተራ እየተነሱ ማንቋሸሽ፣ መስደብ አላቆሙም። አሁንም እንኳን ሞት በራፋቸው ላይ ቆሞ መጥፊያቸው ግቢያቸው ገብቶ ስድባቸውን ቀጥለዋል። ይሄ የሚያሳየው ደግሞ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያላቸው ጥላቻ ካልጠፉ በስተቀር እንደማይተውት የሚያሳይ ነገር ነው።
የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር የኢትዮጵያን ወጣቶች ቦዘኔ፣ ፍንዳታ፣ በማለት ሲያጥላሉ እና ሲሳደቡ አሻንጉሊቶቹ  የፓርላማ  አባላት ያጨበጭቡና ይስቁ ነበር። የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ባገኘው አጋጣሚ እንደማይፈልጋቸው ሲነግራቸው ኖሯል። ህዝቡ እንዳልመረጣቸው ቢያስውቃቸው ምን ታመጣላችሁ በሚል እያንቋሸሹ፣ እየሰደቡ የጭቆና አገዛዛቸውን ቀጥለውበታል። ህዝብን የሚያክል ነገር መሪ በተባሉት አካል ቦዘኔ እየተባሉ በአደባባይ ሲሰደቡ የሚያሳፍር ቢሆንም ህዝቡ ግን ቦዜኔ ያለው ቤተ መንግስት ነው በማለት የቦዘኔ ጥርቅም ያለው ያለ እውቀታቸው እና ያለ ህዝብ ፍላጎት ተመርጠናል በማለት የተሰገሰጉበት መሆናቸውን ይነግራቸው ነበር።
በ97 የቅንጅት ሰልፍ ግዜ አጋዚ በሰላማዊ ሰው ላይ በወሰደው ኢሰባአዊ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ወያኔዎች የተወሰደው እርምጃ ትክክል ነው ባንክ ሊዘርፉ ሲሉ የነበሩ እና የተለያየ የሽብር ስራ ሊሰሩ የነበሩት ናቸው እርምጃ የተወሰደባቸው በማለት ከመጸጸት ይልቅ ያልተገባ ስም እየሰጡ መግደላቸውን እንደ ትክክለኛ ስራ አድርገው ሲነግሩን ህዝባችን ጥርሱን ነክሶ ዝም ከማለት ውጪ ምንም ያደረገው ነገር አልነበረም። ወያኔዎች የኢትዮጵያ ህዝብን በማንቋሸሽ እና በመስደብ የታወቁ ናቸው። በተቃራኒው ደግሞ የትግራይ ህዝብ ደግሞ በወያኔዎች አገላለጽ ወርቅ ትውልድ እንደሆኑ ይነግሩናል። ይሄ ደግሞ አንደኛ ዜጋ እና ሁለተኛ ዜጋ እንደሆንን አልገባን ከሆነ በግልጽ ነግረውን  እየሰሩበት ይገኛሉ።ለዚህ ነው ህዝባችንን ወራዳ፣ ፍንዳታ፣ ቦዘኔ ሌላም ሌላም እያሉ የሚሰድቡት። ዛሬ ደግሞ  በለመደው የስድብ አፋቸው አጋንት፣ጠንቋይ ብለው  ህዝባችንን በግልጽ በአደባባይ ሰድበውታል። ይሄ የሚያሳየው ለወያኔዎች የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ሰው አለመቁጠራቸው ነው። የሰው ልጅን አጋንት ተብሎ መሳደብ ያስቀጣል ወደፊትም ተጠያቂም ያደርጋቸዋል። ዛሬ ስልጣን ላይ ነይ ብለው በስልጣናቸው ተጠቅመው የፈለጉትን መናገርና መስራት እንችላለን ተብሎ ህዝብን የሚያል ማዋረድ ህዝብን ማንቋሸሽ አቋማቸው ሁሌም የማይለወጥ መሆናቸውን አሳውቀውናል እኛም ካወቅን ሰነበትን።  ህዝቡ ሲነሳ ነደድ እሳት እንደሆነ አልተገነዘባችሁ ይሆንን? ህዝብ ሆ ብሎ ተነስቶ እንደሚያጠፋችሁ ዘንግታችሁታል። ህዝብን ንቆ፣ አዋርዶ፣ አንቋሾ መኖር እንችላለን ብላችሁ ካሰባችሁ ዶክተር መራራ ጉዲና እንደተናገሩት እነሱ ከጫካው ወጡ እንጂ ጫካው ከነሱ አልወጡም የሚለው አገላለጽ ይገልጻችኋዋል። ዛሬም ከ25 አመት በኋላ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያላችሁ ጥላቻ አለመጥፋቱን በግልጽ ነግራችሁናል። ዛሬም የኢትዮጵያን ህዝብ ለመስደብ እና ለማጥፋት  እንደማይመለሱ በእርገጠኝነት አሳይታችሁናል።
እንግዲህ ዛሬ ያልነቃህ ካለህ ንቃ ያልተነሳህ ካለህ ተነስ። ኦፒዲኦ፣ ብአዴን፣ ደህዴን የሚባሉት ድርጅቶች ቀድመን እንደተናገርነው ደግመንም ደግመንም እንዳሳሰብነው የወያኔ መጠቀሚያ እንጂ ምንም የማይሰሩ በአገሪቷ ላይ ስልጣን የሌላቸው የሆድ አደር ጥርቅም እንደሆኑ ብዙሃኖቹ አስረግጠው ተናግረዋል። በየትኛውም አካባቢ ትዕዛዝ የሚያስተላልፉት ውሳኔ የሚሰጡት የክልሎች መንግስት ተብዬዎች ሳይሆን ወያኔዎች ናቸው። ከዚህ  መስመር በኋላ ኦፒዲኦ ነው የሚመለከተው ከዚህ መስመር በኋላ ብአዴን ነው የሚመለከተው ከዚህ መስመር በኋላ ደህዴን ነው የሚመለከተው በማለት ሁሉም አንድ ሆነው እንዳይሰሩ ለመለያየት የተጠቀመበት እንጂ ምንም የማይፈይዱ የወያኔ መጠቀሚያ የሆኑ አጥር እና ድርጅቶች ናቸው። ይሄንን አጥር እና የወያኔ ሴራ  ለአንደ እና ለመጨረሻ ግዜ መሰበሪያው ሰአት አሁን ነው። በአጥር ከልሎ አንዱ ወደ ሌላው እንዳይመጣ አንዱ ለአንዱ አጋር እንዳይሆን እናንተ አይመለከታችሁም ሁሉም የራሳቸው አስተዳዳሪ ስላላቸው ማንም ከራሱ ክልል ውጪ አይመለከታችሁም በሚል ሰበብ አራርቆ ወያኔ ግን ሁሉም ክልሎች ውስጥ በዋነኝነት እየሰራ ህዝባችንን አለያይቶ በተነጠል እያጠፋን ስለሆነ ነገሮችን በጥልቀት እና በብልጠት የምናይበት ግዜ ነው። ወያኔ ያስቀመጠው አጥር በማፍረስ ፍቅር አሸናፊ ነው አንድነት ሃይል ነው የኛ ጠላት ወያኔ ነው ብለን የከፋ ነገር ሳይመጣ አንድነታችንን በግልፅ እናውጅ። በአገር ቤትም በውጪም የምትኖሩ የተቃዋሚ ኃይሎች አንድ ነን ብላችሁ በአንድነት ተሳሰሩ በአንድነት ቁሙ ስለ አንድነት ዘምሩ ያኔ በአንድነት የተሳሰረ ህዝብ በአንድነት የፍቅር መዝሙርን ሲያሰሙ የወያኔ ምሶሶዎች ይፈርሳሉ ዛሬ አጋንት ብሎ ህዝባችንን የሰደቡ በፍቅር እና በአንድነት ስንቆም የእግዚአብሔር ኃይል ለብሰን የተሳዳቢዎችን አፋቸውን የመዝጋት ስልጣን እናገኛለን። የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ንቁ እንንቃ ሁሉም ህብረተሰብ አንዱ ለአንዱ ዘብ ይቁም አንዱ ለአንዱ መከታው ይሁን። ሁላችንም ሳንለያይ በመደጋገፍ ለወያኔ ሴራ ክፍተት ባለመስጠት ብንሰራ በአጭር ግዜ ድሉን በእጃችን ማስገባት ይቻላል ሰላምን ለኢትዮጵያ ማስፈን ይቻላል።
የወያኔን ፉከራ ባዶ ፉከራ ማድረግ የምንችለው ሳንከፋፈል ስንታገል ብቻ ነው። ስድባቸውን ማጥፋት የምንችለው በአንድነት ስንነሳ ብቻ ነው። ይሄ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ መልዕክቴ ነው። ህዝባችንን ለጭፍጨፋ አናጋልጥ ለህዝባችን ነጻነትን ለማምጣት በረሃ የወረዱትንም አሰልቺ ትግል እንዲጋፈጡ አናድርጋቸው። ነጻነት ማግኘት የምንችለው በረሃም ያሉት ከተማም ያሉት በውጪም ያሉት የአንድነት ድምጽ ሲኖረን ነው። ይሄ ካልሆነ ግን ትላንትና በአደባባይ ቦዘኔ፣ ፍንዳታ፣ ወራዳ ተብለን ተሰድበንና ተገድለን በመከራ እንዳለፍን ሁሉ ዛሬም አጋንት፣ ጠንቋይ ብለውን እየሰደቡን እየገደሉን እያዋረዱን ነው። በአደባባይ እየተሰደብን በአገራችን እየተገደልን ከቄአችን ላይ እየተፈናቀልን እንዳንኖር ሰላማችንን ማምጣት የምንችለው እኛው ነን። ወያኔ እንደሆነ መቼም መለወጥ የማይችሉ ናቸው። መለወጥ ያለብን እኛው ለውጥን ፈላጊ ሰላምን ናፋቂዎቹ ነን።

የመጨረሻው ድል የፍትህ: የሰላም፡የፍቅር ነው። በዘር በክልል መከፋፈል ከመለስ ጋር ሞቷል



ቢላል አበጋዝ
ዋሽግተን ዲ ሲ
ረቡዕ ፣ ዲሴምበር 16 ቀን 2015
እንደዛሬው ወያኔ ኢህአዴግ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ግልጽ በሆነ መንገድ ፍላጎቱን በትክክል፤ የሚሄድበትን መንገድ ወለል አርጎ ያሳየበት ጊዜ የለም።ፍላጎቱ ስልጣን፤ዘዴው በጭካኔ መርገጥ፤ ይህ ካልሰራ አገር መበተን ነው።ይህን ማንም አሽቃባጩ ማንም ይቅርታ ጠያቂው ሊከላከልበት የሚችለው አይደለም።ከዚህ ወዲያ በጭካኔ የመርገጥ ተግባሩን ይበረታበታል እንጂ የሚቀንስው አይደለም።የህዝቡን እምቢተኝነት “የሽብርተኛ” ማለቱ የምዕራቡን ዓለም እገዛ ለማግኘት፤ከተጠያቂነትም የሚድን መስሎት ነው።

abebe Gelaw

የህወሃት ማከላዊ ኮሚቴ በሁለት ተከፍሎ ይህም ማለት ለህዝቡ እምቢተኝነት ፖለቲካዊ መፍትሄ መስጠትና እንደወትሮው በጭካኔ መርገጥ ላይ ቢዶልት፤ጨፍጭፍ፤ እርገጥ የሚለው ክፍል ያቸነፈ መሆኑ በኦሮሚያ ወታደራዊ አዋጅ መታወጁ አመላካች ነው።የሚሄድበትን መንገድ ወለል አርጎ ያሳየበትም ይኸው ነው።
ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሀይሎች ዛሬ የሚሰሩት ስተት ቢኖር በኦሮሞ ኢትዮጵያ የተነሳውን አመጽ አንዱ ክፍል የተወሰነ፤የኦሮሞ ብቻ አድርጎ ማሰብ፤ኦሮሞች የሆኑ ደግሞ የብቻ ትግላቸው አድርገው ካዩት ነው።እኒህ ዳር ና ዳር ያሉ የጽንፈኝነት ሰለባ አመለካከቶች ለወያኔ የሚመቹ የኢትዮጵያን ህዝብ ለቀጣይ ባርነት ይሚዳርጉ ናቸው።የወያኔ ኢህአዴግ ፍላጎቶችች ጋር የሚናበቡ ጽንፎች ናቸውና።
የህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ትግል መራመድ እነዚህን ከላይ ያነሳኋቸውን ጽንፈኝነቶች እያከሸፈ ወያኔ ጋር መጋፈጥ ይኖርበታል። ደስ የሚያሰኘው ወጣቱ እኒህን ጽንፎች እያከሸፈ መሆኑ ነው። እኒህ ጽንፎች በኦሮሞው በኩል የዛሬው ጉዳት፤ሞትና ስቃዩ ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ ያለፈ ታሪክን ይዘው ለጥርጣሬ በር ይከፍታሉ።በአማራው በኩል ያሉት ጽንፈኞች ደግሞ አማራው ሲበደል ኦሮሞው መቸ አገዘ ይላሉ።በዚህ ክርክር የጋምቤላው የአፋሩ የሶማሉ የደቡቡ በደል መነሳቱ ይቀራል።በዚህ መሃል ወያኔ ኢህአዴግ ፋታ ያገኛል ማለት ነው።ወያኔ ኢህአዴግን የሚጥለው አገር አቀፍ ህዝባዊ አመጽ ነው።አንድ ባንድ ተራ በተራ ለገጠሙት ብርታት የለውም ማለት ወያኔ ላይ የዋህ ግምት ማድረግ ነው።
ወያኔ ኢህአዴግ በህዝቦች መካከል ክፉ ልዩነቶችን ቢያጣ እራሱ በጥረቱ ያሰናዳቸዋል።ይቀምማቸዋል።በጎንደር እያደረገ ያለውን በክልል ውስጥ ክልል መፍጠርን፤የቅማንት ህዝብን ጥያቄ ማራገብን ማመልከት ብቻ ይበቃል።እንዲህ ያሉትን ዘዴዎች ትቶ ለምን ከነጭርሱ ኤርትራ ወረረችኝ አይልም ?ይህንም ይላል።ግን ትልቅ ካርዱ ሰለሆነ ያቆየዋል። ኤርትራን ይተነኩስ እንደሆን እንጂ ኤርትራ ኢትዮጵያን የምትወርበት ምክንያት ዛሬ የለም።ኤርትራ የኢኮኖሚ ችግርዋን መልክ ማስያዝ ላይ እንዳለች እየተነገረ ከሆነ ቆይቷል።
አፍጥጠው ያሉት የቀይ ባህር ባሻገር ሀብታም አረብ አገሮች ዛሬ ወያኔን በገለልተኝነት አቌም ያዩታል እንጂ ለወያኔ ኢህአዴግ መሰናበት አይጨነቁም።እንዲያውም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አገር ወዳድ መንግስት ሳይቆም የኔ የሚሉት ሀይል ከዚህ ወያኔ ሊያራግበው ከሚመኘው እሳት መሃል እንዲወጣላቸው የኢትዮጵያን ጉዳይ መያዣ እዲኖራቸው ይፈልጋሉ።ይህን ደግሞ የሚገልጸው ከየመን በኋላ ሀብታም አረብ አገሮች ፈርተዋል።ሰግተዋል።ምንም ከማድረግ አይመለሱም።ኢትዮጵያ የወትሮ ምኞታቸው፤የወትሮም ስጋታቸው ናትና። የህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ትግሉን የሚያዛንፉ ሌላ ሀይሎች እነሱ ናቸው እላለሁ።ጠላት ወያኔ ኢሃዴግ ብቻ አይደለም።
ዛሬ በኢትዮጵያ ወያኔ ህወሃት በግድያ፤ በድብደባ ሊገታው የማይችለው አመጽ ተነስቷል።ከኢትዮጵያ ውስጥም ይሁን ከውጭ ዜጎች ስጋት ባለበት መንፈስ ሁኔታውን እየተከታተሉ ነው። የወያኔ የፖሊስና ወታደራዊ ሀይል በትንሹ እንኳን ቢነቃነቅ የወያኔ ህልውና የመጨረሻዎቹ ሰዓቶች መድረሳቸው አመላካች ነው።ወያኔ ይህን ያህል በቋፍ ነው። ያውቀዋል።ጥያቄው የአሁኑ የየካቲት 1966 ዓም ድጋሚ ይሆን ? ነው።
ወያኔ መግደል ይችላል።የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት የዴሞክራሲ ትግል ሊገታ ግን አይችልም።የፋሺስት ኢጣሊያ ጭፍጨፋን ታዝቦ ለታሪክ ያቆየው አንድ የሁንጋሪያ ሰው የፋሺስ ኢጣልያ የአረመኔ ድርጊት ኢትዮጵያ በሚለው መጽሀፉ መጨረሻ እንዲህ ብሏል “በደምና በስቃይ ላይ የተገነባ፤በደምና በገጠጠ ውሸት ላይ የተመረኮዘ ይወድቃል።ከመቸውም ጊዜ በበለጠ የመጨረሻው ድል የፍትህ: የሰላም፡የፍቅር ነው።”
ድል ለዲሞክራሲያዊ ሀይሎች ሁሉ!
ኢትዮጵያ በአንድነትዋ በነጻነት ለዘለዓለም ትኑር

Sunday, November 29, 2015

የአዲስ አበባ ህፃናት ከቆሻሻ ላይ ምግብ አንስተው ሲመገቡ የሚያሳይ ቪዲዮ | ከተሜው ከተራበ ቆይቷል


  • 165
     
    Share
ስሜነህ ከሚኒሶታ

15 ሚሊዮን ሕዝብ ተርቧል ሲባል አንዳንድ የስርዓቱ ገጽታ እንዲበላሽ የማይፈልጉ ተላላኪዎች “የተራበም በርሃብ የሞተም የለም” በሚል አይናቸውን ጨፍነው ሲከራከሩ ማየት በጣም ያማል:: በቅርቡ በቢቢሲ ላይ ወጥታ ልጇ በርሃብ የሞተባት ወ/ሮ ብርቱካን እንዴት አድርገው በመሳሪያ ሃይል አስፈራርተው ልጄ በርሃብ አልሞተም እንድትል እንዳደረጓት የቀናት ት ዝታችን ነው:: ዛሬ ከዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተለቀቀውን ቪዲዮ ለትውስታ ያቀረብኩላችሁ እነዚሁ የ ስር ዓቱ መልካም ገጽታ ገንቢዎች እንዲያፍሩ በማሰብ ነው:: አሁን ድረስ በአዲስ አበባ ችግር ውስጥ ያሉ ህፃናት ከቆሻሻ መጣያ ምግብ እያነሱ ይመገባሉ:: የ ስር ዓቱ ተላላኪዎች እነዚህንስ ምን ይሏቸው ይሆን?
የሚያሳዝነው የስርዓቱ ደጋፊዎች ይህን እውነታ ለመደበቅ መሞከራቸው ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ይህን ለመለወጥ ሲሰሩና ሲጥሩ አላሰራ ማለታቸው ነው:: በቅርቡ በየሃገራቱ ያሉት የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች ያወጧቸውን መግለጫዎች ይጠቅሷል::
addis ababa
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48367#sthash.OBLQJPQ9.dpuf

ወይ እነሱ ወይ እኔ ኢትዮጵያዊ አይደለንም” | በ4 ፖሊሶች የተደበደበው ሰው | ከያሬድ ሹመቴ


Yared

ካዛንቺስ ቶታት ፊትለፊት ጫጫ ኮርነር የተባለ ቤት በር ላይ የፒያሳ ታክሲ ለመያዝ ከምሽቱ 3:30 ገደማ በርካታ ሰዋች መሀል ቆሜያለሁ። 4 ፖሊሶች ደግሞ አለፍ ብለው ቆመዋል።

እድሜው ወደ 30ዋቹ መጨረሻ የሚሆነው አንድ ሰው በፌስታል የተቋጠረ ነገር ይዞ አቀርቅሮ ይጓዛል። ፖሊሶቹ አጠገብ ሲደርስ በመሀላቸው አቋረጠ። ከመሀላቸው ልጅ እግር የሆነው ፖሊስ ሰውየውን ጎትቶ ወደ ኋላ መለሰው።
“አቤት?” አላቸው ሰውየው።
“ለምንድነው በመሀላችን ያቋረጥከው?” አለው።
“አላየኋችሁም ይቅርታ”
“እንዴት አላየኋችሁም ትላለህ” አለው ሌላው
“ምን አጠፋው” ብሎ መለሰ
“ፖሊሶች እኮ ነን” አለው አንዱ
“ፖሊስ ማለት ህዝብ ነው” አለ ቆፍጠን ብሎ
“አንተማ ሌላ ተልዕኮ አለህ” ልጅ እግሩ ተናገረ።
“በስህተት በመሀላችሁ በማለፌ ነው ተልዕኮ ያለኝ?”

ታክሲ ለመሳፈር የተሰበሰበው ሰው ከንፈሩን እየመጠጠ ፖሊሶቹን በትዝብት ሲመለከት አንደኛው ፖሊስ “በቃ ና” ብሎ ወደፊት ጎትቶ ሲወስደው ሁሉም ተከተሉት።
ከፊት 2 ከኋላ 2 ሆነው ሰውየውን ይዘውት ሲሄዱ ታክሲ ተራው ላይ መቅረት አላስቻለኝም። ተከተልኳቸው። ከፊት ያሉት ሁለቱ ፖሊሶች እንደ ጓደኛ እያወሩት ይሄዳሉ። ወደ ፈንድቃ ባህል ምሽት ጋር ከመታጠፋቸው በፊት አንድ የብረት ፍርግርግ አጥር ያለው ጊቢ በር ከፍተው ገቡ። ኮምዩኒቲ ፖሊሲንግ የሚባል ቢሯቸው ነው።
የቢሮውን በር ከፍተው ሶስቱ ፖሊሶች ወደ ውስጥ ይዘውት ሲገቡ አንደኛው በረንዳው ላይ ቆሞ አካባቢውን ይቃኛል። እኔም እንዳያየኝ ካንትራት ታክሲ አስቁሜ ዋጋ መደራደር ጀመርኩ። ፖሊሱ ሰው አለማየቱን አረጋግጦ ወደ ውስጥ ሲገባ፥ ታክሲውን ይቅርታ ብዬው ወደ አጥሩ ተጠጋሁ።
የጊቢው አጥር እና ቢሮው ብዙም ርቀት የሌለው በመሆኑ በድንብ ይታያል። የበረንዳው መብራት እንደበራ ሲሆን ከፍተው የገቡትን ቢሮ መብራት አላበሩትም። ጨለማው ክፍል ውስጥ ሰውየው በመስኮቱ በኩል ከውጭ በሚገባው ብርሀን ይታየኛል።
ከመቅጽበት በሩ ተከፍቶ አንደኛው ፖሊስ ወደ ውጭ ወጣ። በረንዳው ላይ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን መቃኘት ሲጀምር እኔም ታክሲ ጠባቂ መስዬ ቆምኩ። የሰውየውን ጩኸት ሰማሁት። የዱላ ድምጽ እና የሰውየው ጩኸት መንገደውኛውን ፊቱን ቢያስዞረውም ፖሊሱ አይኑ ፈጦ ሁሉንም ሰው ያይ ስለነበር ደፍሮ የቆመ የለም።
ጨለማ ቤት ውስጥ ለሚቀጠቀጠው ምስኪን ሰው አንጀቴ አረረ። ማድረግ የምችለው ነገር ምን እንደሆነ ጠፋኝ። የሰውየውም ድምጽ እና የዱላ ውርጂብኝ እየበረታ ሲሄድ አልቻልኩም። በፍጥነት ወደ 6ተኛ ፖሊስ ጣቢያ ሮጥኩ። የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ፖሊስ መምሪያ (6ተኛ) አሁን ካለሁበት ብዙም ርቀት የሌለው በመሆኑ በፍጥነት ደረስኩ።
ጨለማ የወረሰው ግቢ ውስጥ ተረኛ ጥበቃ ፖሊሶች አግኝቼ አዛዦች ካሉ ብዬ ጠየቅኩ። “ማንም የለም ለኛ ንገረን” አሉኝ “አይ ሀላፊ ነው የምፈልገው” አልኳቸው። ሀላፊዎች የሉም ግን የመረጃ ክፍል ሄደህ ማነጋገር ትችላለህ አሉኝና ቢሮውን አመላከቱኝ።
ጨለማውን ኮሪደር አልፌ አንደኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኘው መረጃ ክፍል ደረስኩ። አንድ ፖሊስ ብቻውን በርካታ የራዲዮ መገናኛ የድምጽ መሳሪያዎች ፊቱ ተደርድረው አንድ መዝገብ ላይ የሆነ ነገር እየፃፈ አገኘሁት።
“አስቸኳይ ጥቆማ ለመስጠት ነው” አልኩት።
“ምን ልታዘዝ” አለኝ። ፖሊሱ በጣም ትሁት ነው። የሆነውን በሙሉ ነገርኩት። ተናደደ።

በሬዲዮው መገናኛ የተለያዩ ኮዶችን እየጠራ የፖሊሶቹን ማንነት ለማጣራት ሞከረ። ተረኛ የጣቢያ አዛዡን ሞባይል ስልክ ቁጥር ጠይቆ ደወለ።
“ሀሎ … የት ነው ያለኸው?… 26 ያሉት ለምንድነው ሰው የሚደበድቡት?… ሰዋች በአካል መጥተው አባሎች ሰው እየደበደቡ ነው ብለው እየተናገሩ ነው። ጠቋሚ ሰዋቹ ‘በመሀላችን ለምን አለፍክ ብለው ነው የሚደበድቡት’ ነው የሚሉኝ…ፈጥነህ ድረስ…ቦታው ላይ ሂድ። ሰውየው ካለ ወደ ቤቱ የሚሄድበትን ወይም ወደ ህግ የሚሄድበት ነገር አድርግ። ህግ ከጣሰም በህግ ነው መቀጣት ያለበት እንጂ እንዴት በዱላ ይቀጣል?… እንደሰው አያስቡም እንዴ? ለምን አትነግሯቸውም? ሰው ለምን በመሀል አለፍክ ተብሎ ይደበደባል?…

…በባህላችን በሰው መሀል እንደማይታለፍ አስተምረኸው ታልፋለህ እንጂ ሰውን በዱላ ነው እንዴ የምታስተምረው?… እኔ ጋር ነው ያሉት የጠቆሙኝ ሰዋች… ምን?…ለምንድነው ወዳንተ ጋር የምልካቸው?… ወዳንተ ልኬ ደግሞ ልታስደበድባቸው ነው? ቶሎ ሂድና ያለውን ውጤት እኔ ጋር መጥተህ ንገረኝ።” ስልኩን ዘጋውና አመስግኖ አሰናበተኝ።
የሰውየው ነገር መጨረሻ አሳስቦኛል። እንደገና በሩጫ ትቼው ወደ ሄድኩት የኮምዩኒቲ ፖሊሲን ቢሮ አቅጣጫ ሄድኩኝ። መታጠፊያው አካባቢ ስደርስ ይህ ሰው እያነከሰ እና እየተንፏቀቀ ወደ እኔ አቅጣጫ ሲመጣ አየሁት። ያለቅሳል” ወይኔ” እያለ ግንባሩን ይደበድባል። “አይዞህ” አልኩት። “እባክህ ደግፈኝና 6ተኛ ፖሊስ ጣቢያ አድርሰኝ” አለኝ። የሆነውን በሙሉ እንዳየሁ ነገርኩትና ደግፌው ወደ ጣቢያው በድጋሚ ሄድኩ።
ፖሊስ ጣቢያው ጊቢ ውስጥ እንደገባን ሰውየው የቢሮው በረንዳ ላይ ተቀመጦ ለቅሶ እና የህመም ሲቃውን ቀጠለ። እኔን ያስተናገደኝ ፖሊስ እና የደወለለት ፖሊስ ተከታትለው መጡ። የሰውየውን ስም ጠየቁት “ዘላለም” አለ እያለቀሰ።
ዘላለም ብሶቱን በእንባ እና በለቅሶ መናገር ጀመረ።” “እኔ እኮ የተከተልኳቸው የናንተን ልብስ ስለለበሱ ነው። የፖሊስ ልብስ ባይለብሱ ኖሮ ጨለማ ክፍል ውስጥ ተከትያቸው እገባ ነበር? ህግ ቦታ እየወሰዱኝ ነው ብዬ ነው አምኜ የተከተልኳቸው። ምን አደረግኳቸው? ምን በደልኳቸው? አያውቁኝ! አላስቀይምኳቸው። ምን በድዬ ነው ምን አጠፋሁ ባልኩ የሚሰባብሩኝ?” እንባውን እየዘረገፈ ሲቃ እየተናነቀው ሲናገር ሀይለኛ ቁጣ እና ሀዘን ሆዴ ውስጥ ዘልቆ ገብቶ ጉሮሮዬን ሳግ ተናነቀኝ።
“ምን አድርጌ ነው። ለልጄ ልብስ እና ጫማ ገዝቼላት እንቅልፏን ሳትተኛ ልድረስ ብዬ ስሮጥ ጠልፈው ይቀጥቅጡኝ?!። እግዚአብሔር ፍርድ ይሰጣል እኔ ምንም አልልም እንባዬን እሱ ያብሰዋል። ምንም መናገር አልችልም ሌላ።”
ፖሊሶቹ የተመታውን እንዲያሳያቸው ባትሪ ወደ እግሩ አበሩ። ግራ እግሩ ክፉኛ አብጧል። እንባው እንደጎርፍ እየወረደ ለቅሶውን ቀጥሎ እያነከሰ ከተቀመጠበት ተነሳ። ፖሊሶቹ ነገ መጥተህ ክስ መስርት አሉት።
“እኔ ክሴ ለእግዜር ነው። እሱ ፍርድ ይስጥ። ብቻ ወይ እነሱ ወይ እኔ ኢትዮጵያዊ አይደለንም። አንዳችን ሀገር ክደናል። አይ ኢትዮጵያ! የፖሊስ ልብስ ለብሰዋል ብዬ ተከትዬ ስደበደብ እውነት ሀገር አለኝ እላለሁ? ነገም አልመጣም እናንተ ከሰማችሁኝ ይበቃኛል። ምን ፍርድ አገኛለሁ ብዬ ነው?” እንባውን እየጠራረገ ወደ ቤቱ ለመሄድ እያነከሰ መራመድ ጀመረ። ፖሊሶቹ ስልኩን ተቀበሉት። በነጋታው እንዲመጣ ቢለምኑትም ምንም ፍትህ ተስፋ እንደማያረግ ነግሯቸው እንባውን እያዘራ መሄድ ጀመረ። ከፖሊሶቹ ጋር ተሰናብቼ ደግፌው አብረን መሄድ ጀመርን።
ግማሽ መንገድ ሸኘሁት። “ወይ እነሱ ወይ እኔ ኢትዮጵያዊ አይደለንም” የሚለውን ቃል እየደጋገመ እንባውን እያፈሰሰ ወደ ቤቱ በእየተሳበ ሄደ።
፡።።።
ሀቀኛ ፖሊሶች ካላችሁ ልብሳችሁን አስከብሩ።
።።።።

እነዚህን 4 ፖሊሶች በህግ ተጠያቂ ይሆኑ ዘንድ ይህንን መልዕክት Share በማድረግ ሀላፊነትዎን ይወጡ።
።።።።
ዘላለምን ግን ቸር አምላክ ምህረቱን ያውርድለት።

- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48550#sthash.7hi3bZbP.dpuf