Monday, November 16, 2015

አውሮፓዊያኑ የ1.8 ቢሊዮን ዩሮ እርዳታ ስደተኛን ለመቀነስ ወይንስ ለማብዛት?


  • 540
     
    Share
ከተማ ዋቅጅራ 
የአውሮፓ ህብረት በማልታ ቫልታ ከተማ ላይ በስደተኛ ዙሪያ ከአፍሪካ መሪዎች ጋር ስብሰባ አድርገው ነበረ። አውሮፓዊያኑ በያዝነው አመት ታይቶ  በማይታወቅ ሁኔታ በስደተኞች በመጥለቅለቃቸው ስጋት የፈጠረባቸው ጉዳይ በመሆኑ ከአፍሪካ መንግስታት ጋር በስደተኛ ዙሪያ ተወያይተው ነበረ። እውን የአውሮፓ ህብረት መንግስታቶች እንዳሰቡት ለአንባ ገነኖች ለአፍሪካ መሪዎች የገንዘብ እርዳታ በማድረጋቸው ስደተኛን ወደ አውሮፓ መፍለሱን ያስቆሙት ይሆንን?
video-migrant-boat-capsizes-near-italy-leaving-200-people-in-the-sea
የአውሮፓ ህብረት 1.8 ቢሊዮን ብር ወጪ እናደርጋለን በማለታቸው ለአፍሪካ መሪዎች ልገሳ በማድረግ ስደተኞችን እናስቆማለን ብለው የተናገሩት ሃሳብ የአፍሪካ መሪዎች ወደግል ካዝናቸው በመክተት እና የጦር መሳሪያ በመግዛት ለአፈና ስራ በማዋል ስደተኛው የበለጠ እንዲሰደድ ከማድረግ ውጪ የሚፈይደው  አንዳች ነገር እንደሌለ ጠንቅቀን እናውቀዋለን። ለግዜው ስለ ሌሎች አፍሪካ አገር ተወት እናድርገውና በአውሮፓ ህብረቱ ስብሰባ እና የገንዘብ እርዳታ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ስላለው አንድምታ እንመልከት። የኢትዮጵያ ችግር የተወሳሰበ ነው። ያወሳሰበውም ወያኔ ነው። የአውሮፓ መንግስታትም ሆኑ የአሜሪካ  እንዲሁም ያደጉት አገራት የሚባሉት ሊያዩት ያልቻሉት ከፍተኛ የሆነ ችግር በኢትዮጵያ ውስጥ አለ። ይሄንን ግፍና ችግር በኢትዮጵያኑ ላይ የሚደርስ ስለሆነ በአገራችን መኖር ባለመቻላችን ለስደት እንዳረጋለ። ይሄም የወያኔ አንባ ገነን ገዢዎች  የሚፈጥሩት የከፋ ችግር ነው።
የኢትዮጵያ መንግስት ስለ ዲሞክራሲአዊ አሰራር ሰርቶ አያውቅም። ስለ ህዝብ ነጻነት ሰርቶ አያውቅም። ስለ አገር አንድነት እና ሰላም ሰርቶም አያውቅም። ለምዕራባዊያኖቹ ፎቆችን እና መንገዶችን እንዲሁም አንድ አንድ ነገሮችን በማሳየት በዲሞክራሲ መንገድ እየሰራው ስለሆነ ኢትዮጵያ እያደገች እንደሆነች በማስመሰል ምዕራባዊያኑን ቢያታልላቸውም ቅሉ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋ በጥቂት የወያኔ ጉሩፖች ተይዘው ህዝባችንን ለከፋ ችግር እያጋለጡ እንደሆነ አልተረዱትም። ለዚህም የአውሮፓዊያኑ መንግስታት የኢትዮጵያን ህዝብ ችግር ከማስወገድ ይልቅ ከችግር ፈጣሪ አንባ ገነን መሪዎች ጋር በመስራት አቅማቸውን በማሳደግ አንባ ገነኖቹ ወደ ከፋ  አንባ ገነንነት ስለሚሸጋገሩ በደሉን እና ግፉን መቋቋም የማይችለው ህዝብ ለስደት የሚዳረጉት በእጥፍ ከማሳደግ ውጪ የሚፈይደው ነገር እንደሌላ እናውቃለን።
ሁሉም ሰው በአገሩ በሰላም መስራት እና መኖር ከቻለ ስደትን የሚመርጥ አለ ብዬ መናገር አልችልም። እንደ ስደት በጣም አስቀያሚ ነገር የለም። ሁሉም ነገር በተወለድክበት በኖርክበት በአገር ሲሆን ደስ ይላል። አንባ ገነኖች በሚፈጥሩት ግፍ ግን ሳንወድ በግድ ስደትን እንመርጣለን። ስደተኛ ርሃብተኛ አይደለም። ስደተኛ ያልተማረ  አይደለም። ስደተኛ መኖሪያ የሌለው ቤት አልባም አይደለም። ስደተኛው ሁሉ ነገር ኖሮትና ተርፎት በአገሩ በሰላም መኖር የሚያስችል መንግስት ባለመኖሩ ሰላምዊ ኑሮን ፍለጋ የተሰደደ እንጂ።
ዛሬ ስደተኛ ብለን የናቅናቸው እና በግድ እንመልሳቸው እና ለንባ ገነን መሪዎች አሳልፈን እንስጥ ብላችሁ ስብሰባ የተሰበሰባችሁባቸው እኮ ትላንትና የአፍሪካው አባት የሚባሉት እና የአለም የኖቤል ሽልማት ተሸላሚ የሆኑት ኔልሰን ማንዴላ ስደተኘ ነበሩ። ትላንትና እኮ  በአለም ህብረተሰብ ተወዳጅ ተቀባይነት የነበራቸው ኖርዌይን በመርዳት የሚታወቁት ጀርመንን በመርዳት የሚታወቁት ጀማይካኖች በፍቅር የሚወዷቸው የአፍሪካ ህብረትን መስራች የሆኑት ኢትዮጵያዊው መሪ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስደተኛ ነበሩ። በአለማችን ላይ ተጽእኖ ፈጣሪ እና በእውቀጣቸው ከአለም ጥቂት ሰዎች መሃል የነበረው በአለም መንግስታት ዘንድ ቁጥር አንድ ተፈላጊ የነበረው በናሳ ሳይንቲስት ዘርፍ ከፍተኛ ስልጣን የነበረው ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት ቅጣው እጅጉ ስደተኛ ነበረ። ዛሬም በአለማችን ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ እንዲሁም አለማችንን ወደ ተሻለ አቅጣጫ ሊለውጧት ይችላሉ ከተባሉት አስር የአለማችን ተመራማሪዎች ሁለቱ ኢትዮጵያዊ ወንድማማቾች ስደተኞች ናቸው። በስደት ያሉት ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያን ለውጠው ከአገር አልፈው አለምን ጉድ ሊያሰኙ የሚችሉ ልጆች እንዳላት እናውቃለን። ኢትዮጵያን በአጭር ግዜ ውስጥ መለወጥ የሚችሉ የኢትዮጵያ ልጆች ግን በአንባ ገነን መሪ ጫና በሰላም መኖር ስላልቻሉ ብቻ ከአገር ተሰደው ይኖራሉ። በአገር መኖርን ጠልተው አልያም የኢኮኖሚ ስደተኞች ሆነው ሳይሆን ሰላምን ባለማግኘታቸው ነው የተሰደዱት። ዛሬም አገራቸውን እየናፈቁ እርቀው ያሉ በመቶ  ሺ የሚቆጠሩ ሙህራኖች አሏት ሳይንቲስቶች፣ ፕሮፌሰሮች፣ ዶክተሮች፣ ኢንጅነሮች፣ ወዘተ….።
Mediterranean-troubles
የኢትዮጵያ መንግስት ከአውሮፓ መንግስታት በሚረዳው ገንዘብ የህዝቡን ኑሮ  የመለወጥ ስራ የሚሰራ ሳይሆን  በንግስናው  የሚቆይበትን ነገር በመቀየስ ህዝባችንን የሚያፍንበት  የጦር መሳሪያ በመግዛት ወታደራዊ ኃይሉን እያደራጀ ህዝብን በማፈን ዲሞክራሲ የሚባል ነገር ከአገር ወደ ማጥፋቱ ተግባር እየሄደ ባለበት ሰዓት የአውሮፓዊያኑ መንግስታት ለእንደዚ አይነቱ አንባ ገነን መንግስት ብር መርዳት ማለት የኢትዮጵያን ዘጠና ሚሊዮን ህዝብ ለስደት መዳረግ እንዳይሆንባቸው በጥልቀት ቢያስቡ መልካም ይመስለኛል።
አውሮፓዊያኑ ማድረግ ያለባቸው ከአንባ ገነኖች ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማቋረጥ ጥቂት በስልጣን ላይ ላሉ ሰዎች እርዳታን ከመርዳት ይልቅ ዘላቂ መፍትሄ የሚኖረው የህብረተሰቡን የሰላም ጥያቄ ሊመለስ በሚችልበት ጉዳይ ላይ ቢያተኩሩ ኢትዮጵያ  ብሎም አፍሪካ ወደ ሰላም እና ወደ እድገት ጎዳና በማምጣት ህዝቦቿን በሰላም እጦት ከመሰደድ ሊታደጓቸው ይችሉ ነበር።
ስደተኖችን በግድ አሳልፎ  ለአንባ ገነኖች መሪ መስጠት ክቡር በሆነው በሰው ህይወት ላይ ቁማር እንደመጫወት ይቆጠራል። ስለዚህ በታላላቅ ቦታ ያላችሁ የኢትዮጵያ ልጆች በግድ ለወያኔ መንግስት ተላልፎ የሚሰጠው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ህይወቱ አደጋ ላይ እንዳለ አውቃችሁ የበኩላችሁን ነገር እንድታደርጉ አሳስባለው።
ሌላው እና ወሳኙ ሁኔታ  አውሮፓዊያኑ ጥሬ ገንዘብ ለአንባ ገነኖች ከመርዳት ይልቅ ልትረዱት ባሰባችሁት የብር መጠን ሃምሳ ሺ ይሁን መቶ  ሺ ሰው ሃይል ሊሰራበት የሚችልበትን ፋብሪካ ብትከፍበት ህዝባችንን ልትጠቅሙት ትችሉ ይሆናል እንጂ በጥሬ ገንዘብ የምትሰጡት እርዳታ  የኢትዮጵያን ህዝብ ጭቆናው እንዲበዛበት በማድረግ ሃገሩን ጥሎ  የሚሰደደው ህዝብ ከእጥፍ በላይ ታበዙታላችሁ።
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48262#sthash.6DJZ3Dpg.dpuf

No comments:

Post a Comment