Monday, November 16, 2015

እነሃብታሙ አያሌው ላይ የተጠየቀው ይግባኝ “ያስቀርባል” ተባለ * ፍርድ ቤት ቀርበው ሊከራከሩ ነው


  • 32
     
    Share
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
አቃቤ ህግ የሽብርተኝነት ክስ መስርቶባቸው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ ተበይኖላቸው በነበሩት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ላይ አቃቤ ህግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት የጠየቀው ይግባኝ ያስቀርባል ተባለ፡፡

habitamu
































ዛሬ ህዳር 6/2008 ዓ.ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በእነ ሀብታሙ አያሌው ላይ የተጠየቀውን ይግባኝ መዝገቡን መመርመሩን በመግለጽ ዝርዝር ሁኔታውን በንባብ ሳያሰማ በአጭሩ፣ ‹‹ይግባኙ ያስቀርባል ብለናል›› ብሏል፡፡
በመሆኑም ይግባኝ የተጠየቀባቸው ተከሳሾች ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሺ እና አብርሃም ሰለሞን በቀረበባቸው ይግባኝ ላይ በአካል ቀርበው የቃል ክርክር ለማድረግ ለህዳር 29/2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፡፡
የስር ፍርድ ቤት በነጻ እንዲሰናበቱ ቢበይንም፣ ሁሉም ተከሳሾች አሁንም ድረስ በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48292#sthash.3uFP26vX.dpuf

No comments:

Post a Comment