Thursday, November 5, 2015

ኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ በቡራዩ ከተማ የፊታችን እሁድ ሕዝባዊ ስብሰባ ጠራ

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) የኢሕ አዴግ መንግስት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን ተግባራዊ አደርጋለሁ በሚል እንቅስቃሴውን መቀጠሉን ተከትሎ ከሕዝብ ጋር ለመወያየት ሕዝባዊ ሰብሰባ የፊታችን እሁድ ጠራ::
ኦፌኮን ለዘ-ሐበሻ በላከው በራሪ ወረቀት (ፍላየር) ላይ እንዳስታወቀው ይህ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እና በሌሎች ወቅታዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ለመወያየት የተጠራው ስብሰባ በቡራዩ ከተማ ስታዲየም የፊታችን እሁድ የሚደረገው ከጠዋቱ ከ9 ሰዓት (በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከጠዋቱ 3 ሰዓት) ጀምሮ ይሆናል:: በዚህ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይም የድርጅቱ አመራሮች ዶ/ር መረራ ጉዲና; አቶ በቀለ ገርባና አቶ በቀለ ነጊያ እንደሚገኙ ኦፌኮን አስታውቋል::
በራሪው የጥሪ ወረቀት የሚከተለው ነው::
OFC
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48007#sthash.oEOi1JFu.dpuf

No comments:

Post a Comment