Thursday, March 31, 2016

የጋራ ፊልሚያ በዘረኛው ወያኔ ላይ! (ታደለ መኩሪያ


ታደለ መኩሪያ
ወያኔ    የአጋዚን ጦር ፣ የስለላ መረቡን፣ በሕብረተሰቡ የተጠሉ ግለሰቦችን ፣  የዘር ወርዴ  ሰለባዎችን፣ የገንዘብና የሥልጣን ጥመኞችን ይዞ ለሃያ አምሰት ዓመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ሲ ፏሏል ቆይቷል፤ በጋራ ፊሊሚያ በቃህ ሊባል ይገባዋል። የሀገራችን ክፍለ ሃገር የሆነችው  የትግራይን  ሕዝብ ስም ይዞ  በወቅቱ ደርግ  በሕዝብ ላይ ከሚያደርሰው በደል  ለመላቀቅ መቀሳቀሱ የታወቀ ነበር፤ ይሁን  እንጂ ሀገርን ለመበታተን የቆመ መሆኑ ቢታወቅ  በምንም ዓይነት  የተከዜን ወንዝ  አይሻገርም ነበር፤ እንደማይሻገሯት የወያኔ መሪዎች  ጠንቅቀው ያውቁታል። ዛሬ እንደጌኛ ሊጭኑት የተነሱት  የወልቃይት ጠገዴ፣የከፍታ ሑመራ፣ የጥልመት ሕዝብ  ባለውለታቸው ነበር፤ባጎረስኩ  እጄን ተነከስኩ ሆኖበት ፤ ዛሬ  ንብረቱን ተቀምቶ፤ እርሱነቱ ተገፎ፤  በስውር በጥይት እየተቆላ ነው፤  ልጆቹ  ከትምህርት ቤት ይልቅ  በእስር ቤቶች ታጉረው ይገኛሉ።
ወደ መሐል ሀገር ሰንመጣ፡ በየፈርጁ  ወያኔዎች   የሚያሳዩን  ትዕይንቶች እንደተመልካቹ  ይለያያሉ፤ ሆኖም ግን  ግባቸው አንድ ነው፤ ሕዝብ በጋራ  ሰለሀገሩ እንዳይመክር ማድረግ ነው።  የሚከተለውን ሃይማኖት፣  የመጣበትን የሕብረተሰብ ክፍል፣  በመጠቀም  ሕዝቡን  ለመከፋፈል  አጥብቆ ሠርተዋል፤
ከአራት ዓመት በፊት ጀምሩ ‘ድምፃችን ይሰማ’ በማለታቸው በ እስር የሚማቅቁት  የእስልምና ተከታይ ወገኖቻችን  ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ በጽናት በቆራጥነት ቆሙ እንጂ ሕልውናቸውን አሳልፈው አልሰጡም።  በእኛ ላይ እየተፈጸመ ያለው፣ ‘ቤሔራዊ በደል ነው’ በማለት የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የፍትህ እጦት ሰለባ መሆኑን በዚህ አገላለፃቸው ግለጽ አድርገውታል፤
እውነትን  ለሕዝብ በማቅረባቸው የታሰሩ ጋዜጠኞች፣ ለሰበዐዊ መብት የቆሙ፣ ግለሰቦች፣ በሰላም  ለውጥ ጠያቂዎች ሁሉ  ጭህታቸው አንድ ነው። እንደሙሰሊም ወንድሞቻችን የፍትህ ነው፤ የፍትህ ጥያቄው የእስር ቤት ብቻ ሣይሆን የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ ሆኗል።
ዛሬ በኦሮመኛ ተናጋሪው ሕዝባችን  የተነሣው የ መሬት አንቀጥቅት አመጽ የወያኔን መሪዎች የተነፈሰ ጎማ አስመስሏቸዋል። የኦሮሞ እናቶች ባዶ እጃቸውን   ሞትን ሳይፈሩ በቆራጥነት ታንክና መትረየሰ ካሰለፈው፤ ቦንብና ክላሽ ከታጠቀው፣ የአጋዚ ጦር ፊት ለፊት ተጋፍ ጠው፣ ታሪክ ሠርተዋል። የኦሮሞን ሕዝብ በአድር ባዩ  ኦፒዲዎ መነጽር ይመለከቱት የነበሩት፤ የወያኔ መሪዎች የውርደት ማቃቸውን ለብሰዋል፤ ‘ልክ እናገባችሃለን’ ባዩ  አባይ ፀሐዬ ድንፋታው  ባዶና  ግልብ የቁራ ጭሆት ሆኖ ቀርቷል።
ወያኔ  በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ ሕዝብ ላይ  አጋዚ ጦሩን አሰልፎ   የዘር ማጥፋቱን  ተልኮውን  ቢያጧጥፍም  ሕዝብ አልተበረከከም። ለፍትህ ለነፃነት ለዲሞክራሲ ለአንድነት ፊሊሚያው ከወያኔ ጋር በተባበረ ሃይሉ ቀጥሏል።
የቤገምድር ባጠቃላይ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በተናጥል፣ ከወገኔ ከትግራይ ሕዝብ ጋር አታጣሉኝን ብሎ የወያኔ መሪዎችን ቢማጠን  ጆሮ ዳባ ልበስ አሉ፣  ልመናው እንደፍረሃት ተቆጠረበት፣ ሃያ አምስት ዓመት  ዘንባባ አንጥፎ መለመኑ እንደጅል አስቆጠረው፣  በደሉና ወርደቱ  ሳይበቃው ርዕስቱን ተቀምቶ  ‘ማደሪያ  እንደጣች  ወፍ ‘ተከራተተ፣አሁን  ግን  ወርደት በቃኝ  ብሎ እራሱን  ከወያኔዎች ጥቃት ለመከላከል ‘ጓንዴ  አነሣ!  ጥያቄው የፍትህ ጥያቄ ነው።
ወያኔዎች ሀገር ለማሰተዳደር   ሕዝብን  በጎሣ  አለያይቶ በክልል ከልሎ የቀኝ ገዥዎችን መንገድ መከተላችውን  ሊገባን ይገባል፤  በሕብረተሰባችን  አነጋገር ክልል ለግጦሽ ሣር፣ ዘርም  ለገበሬ ነው ይባላል።  በዚህ  በከፋፍለህ ግዛው መመሪያችው ዜጎችን  እርስ በእርስ ማጫረሱ  አልሳካ ሲላችው፤  መጪው ትውልድ  እንደሕዝብና ሀገር ሊኖርባቸው የሚገባውን የተፈጥሮ ሐብቶቹ  ላይ  ዘምተዋል፤  የአፈር መመረዝ  ፣ የወንዞች  መበከል፣ ሆን ብሎ   ተወላጁን  ከመሬቱ አፈናቅሎ ለባአዳን መሰጠት  ትውልድን ከማጥፍት  ሀገርን   ከመሸጥ ተለይቶ የሚታይ አይደለም፤  ፈጥነን ይህንን  የወያኔ  እብደት  በጋራ   ካላስቆምነው   ከአስር ዓመት በኋላ  ሀገር አለን ብለን  ማውራት  አንችልም። የሀገራችንን ሁኔታ በጥልቀት ካየነው፣ በመግለጫ፣ በዲስኮር፣ በ ጉንጭ አልፋ  ይሰጥ  አገባ  የምንወጣው አይደልም። በእግር  ኳስ  ሕግ ‘ኳሷን ለማን እንድምታቀብላት ከመጨነቅህ  በፊት አስቀድመህ ወደ ኳሷ ተጠጋና  በቁጥጥርህ ሥር አውላት ’ ይላል ። ዛሬ ኳሷ  በኢትዮጵያ  ሕዝብ ሜዳ ላይ  ትገኛለች  ፤  በሀገር ጉዳይ  ላይ  ገለልተኛም  ቆሞ  ተመልካችም   መሆንን  ከዜጋ የሚጠበቅ  አይደለም።  በጋራ  በሀገር ሰም ተቧድኖ  ወደ መስኩ ገብቶ  ኳሷን   ከግብ  ማግባትን  ይጥይቃል።   በሀገር ጉዳይ ካታንጋና   ትሪቢዮን  ላይ   ተቀምጦ በቲፎዞነት   ማጨብጨቡ  ዋጋ አይኖርውም።
በመስኩ ላይ  ለነፃነት ለፍትህ  ለዴሞክራሲና ለአንድነት  እየሠራን  ሕብረት ፈጥረን    የወያኔን የዘረኛ አካሄድ እንፋለም!

No comments:

Post a Comment