Thursday, March 10, 2016

በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!



ምን ብዬት መጀመር ግራ አገባኝ……. የቱን አንስቼ የቱን ልተው…… ምንስ ብፅፍ የውስጤን ቁጭት ይገልፀዋል……!! በህዝባችን ላይ እለት ተዕለት  እየተፈፀመ ያለውን ግፍና ሰቆቃ እየሰማንና እያየን እስከመቼ…..በዝምታ እንኖራለን ግፉ ፅዋ ሞልቶ ፈሷል። ዜጎች በራሳቸው ሀገር፣ በራሳቸው መንደር፣ በራሳቸው ማንነት እንዳይኖሩ የሚደረግበት ሀገር ኢትዮጵያ!

Kalkidan

ትናንት በኦሮሞና በጋምቤላው ወገናችን ላየ በደረሰው ኢሰብዓዊ ድርጊት ምን ያህልን ውስጣችን ስንቃጠል እንደከረምን ከሁላችን የማንረሳው ነው። ይባስ ዛሬ ደግሞ የገደሉትን ገለው፣ያሰሩትን አስረው ፣ይህ አለበቃ ሲላቸው የሰው ልጅ ከሰው ጋር አስሮ ማሰቃየት ላይ ደርሰዋል። ይህን እኩይ ተግባር ማየቱንም ሆን መስማቱ እንዴት እንዴት ያማል…..!! “በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!”
ስማኝ ልንገርህ ወገኔ ዛሬ ሱርማ ወገናች ላይ የተፈፀመው እኩይ ተግባር ነገ በእኔና በአንተ የገዛ ቤታችን ውስጥ መተው እንደሚያድርጉት አትጠራጠር። 21 ክፍለ ዘመን ላይ እየኖረን ኑሮቻች እና ስቃያችን 18 ክፍለ ዘመን ሆኖል። ይህን ግፍና ሰቆቆ እስከመቼ በዝምታ እንደምንገልፀው!!
ጥቂቶች መብታቸውን ተከብሮ ነገር ግን ብዙሃኑ መብቱን እና ነፃነቱን ተነፍጎ የሚኖርባት ሀገር ኢትዮጵያ እየሆን ያለው በህዝባችን ላይ በእውነቱ ዝም የሚያስብል አይደለም። አሁን አሁንማ መብት ሲጠየቅ ምላሹ በመሳሪያ ሆኖል።  “በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!”
ይህን ግፍና መከራ እየሰማን፣ እየተመለከትን ስለምን ዝም አልን፣ ስለምን ዝምታን መረጥን፣ ስለምን በህዝባችን ላይ የሚደርሰውን ስቃይና መከራ ለማውገዝ አቅም አጣን፣ ስለምን የወገናችንን ሞት ሞታችን ማድረግ አቃተን፣ ስለምን መንገድ ዳር ስለሚገድሉብን ልጆች፣ እናቶች፣ ወጣቶች እንዲሁም አዛውንቶች እየሰማንና እያየን ዝምታን መረጥን!!
የእኛን ዝምታ እነሱን ካጀገነ ችግሩ እነሱ ጋር ሳይሆን እኛው ጋር ነው። ስለዚህ ስማኝ ልንገርህ ወገኔ ህወሓትን ከስልጣን ለማወረድ የእኛ ዝምታችን ሰባብረን በአንድነት ስንጮህ ነው። ተደራጅ፣ ተሰባሰብ፣ ተወያይ………..”የሀገር ጉዳይ ነውና” እንክፈል ጊዜችን፣ እንክፈል ገንዘባችን፣ እንክፈል ህይወታችን………ነፃነት ዋጋ ታስከፍላለችና ያለ መሰዋትነት ድል የለምና መከፈል ላለበት መክፈል አለበት……… “ኢትዮጵያ ደምና አጥንት የተከፈለባት ሀገር ናት” አሁንም ልንከፍል ግድ ነው!! “በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!”
በህዝቡ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የተቀጣጠለውን ህዝባዊ እንቢተኝነት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በህዝባዊ እንቢተኝነቱን እንዲሳተፍ የየበኩላችን ጥረት እናድርግ ኢትዮጵያና ህዝቦቾን ከዚህ ፋሽስት ስርዓት እንታደግ!!
“ህወሓት እስካለ ተቃውሞ አለ”
ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!!
ድል ለጭቁኑ ህዝብ!!

ቃልኪዳን ካሳሁን   (ከኖርዌ

No comments:

Post a Comment