Monday, November 10, 2014

ለአንድ ወር የጠፋችው የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ አስከሬን ከነመኪናዋ ጭቃማ ኩሬ ውስጥ ተገኘ

(ዘ-ሐበሻ) የቴክሳስ ፖሊስ ከኦክቶበር 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የጠፋችውን ኢትዮጵያዊት እናት አስከሬን ከሃይቅ ያነሰ ውሃ (ኩሬ) ውስጥ ከነመኪናዋ ገብታ ማግኘቱን አስታወቀ::
almaz
በመዲ ክሬክ የገበሬዎች ከሃይቅ አነስ ያለ ውሃ ውስጥ አንድ ቫን መኪና የተገኘ ሲሆን ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ ገብረመድህንን ሰውነት እንዳገኘ ጠቁሟል:: የወ/ሮ አልማዝ ሰውነት የተገኝበት ጭቃማ ኩሬ የሚገኘው ከምትሰራበት ቦታ በ3 ማይልስ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው:: ፖሊስ የአልማዝ ሰውነትን ከነ ሼቭሮሌት መኪናዋ እንዳገኘ ለቤተሰብ ያስታወቀ ሲሆን አሁን እንዴት መኪናው እዚያ ውሃ ውስጥ እንደገባ በምርመራ ላይ ይገኛል::
ተጨማሪ መረጃ ተመልሰን ይዘን እንመጣለን…
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--

No comments:

Post a Comment