Tuesday, November 11, 2014

ፍርድ ቤቱ በሽዋስ አሰፋ፣ በሀብታሙ አያሌው፣ በአብርሃ ደስታና በዳንኤል ሺበሽ በዋስትና ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለህዳር 11 ቀጠሮ ሰጠ

(ነገረ ኢትዮጵያ) የሽዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሽን ጨምሮ በአቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የተከፈተባቸውን የ10ሩን ተከሳሾች የዋስት ጉዳይ ለማየት ለዛሬ ህዳር 2/2007 ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ የወንጀል ችሎት በዋስትና ጉዳይ ብይን ለመስጠት ለህዳር 11/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጠ፡፡
Habtamu abrhayeshiwas daniel
በሌላ በኩል የደንበኞቹና የእሱም መብት እየተከበረ ባለመሆኑ ላልተወሰነ ጊዜ ችሎት እንደማይቆም ያሳወቀው ጠበቃ ተማም አባ ቡልጉ ተከሳሾቹ ዋስትና እንዲፈቀድላቸው የሚጠይቅ 13 ገጽ ጽሁፍ ለፍርድ ቤቱ ማስገባቱን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
10ሩ ተከሳሾች ህዳር 11/2007 ዓ.ም ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ላይ ዋስትና ይሰጣቸው አይሰጣቸው ለሚለውን ውሳኔ ልደታ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

No comments:

Post a Comment