Saturday, November 29, 2014

የስደተኞትና የስደት ተመላሾች እጣ

8EF5BDEB-55F0-43A5-9205-44A05F770A20_w268_r1የምሥራቅ አፍሪቃ አገሮች በስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ላይ የጋራ ራእይና እቅድ እንዲኖራቸው ለማስቻል የታለመ የሁለት ቀናት ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተጀምሯል።
የስደተኞች አንዷ መዳረሻ በሆነችው የወቅቱ የአውሮፓ ሕብረት ፕሬዝዳንት ጣልያን አነሳሽነት የሚካሄደው ይህ ውይይት በአጭርና ረዥም ጊዜ የሚተገበሩ ግቦች ያመነጫል፤ ተብሎ ተጠብቋል።
በሌላ በኩል የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ ትላንት ስትራስበርግ ፈረንሳይ ለሚገኙት የአዉሮፓ ፓርላማና ምክር ቤት ንግግር ስለ ስደተኞች ሰብአዊ መብትና መከበር ንግግር አድርገዋል።
ርእስ ሊቃነ-ጳጳሱ በሁለቱም ስፍራዎች ባደረጉት ንግግር አዉሮፓ የቆመችለትን ሰብአዊ መብትን የማክበር መርህና ዴሞክራዊ እንድታከብር ጥሪ አድርገዋል።
የሮማው ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳስ በ25 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአውሮፓ ተቋማት ያሰሙትን ንግግር ተንተርሶ የተጠናቀረ ዘገባ ነው።

No comments:

Post a Comment