Tuesday, June 16, 2015

ሰማዕት መንግሥቱ ጋሼ – ከወለጋ እስከ ሊቢያ

በእኔ በኩል በሊቢያ ሰማዕታት ጉዳይ ላይ የምጽፈው ማስታወሻዬ ላይ ሌላ ሰማዕት እስካልተገኘ ድረስ ይህ ታሪክ የመጨረሻዬ ነው ብዬ አስባለሁ ※
” ዘ ሐበሻ እና ድሬ ትዩብ የተባሉ ድረገጾችን ሳላመሰግን አላልፍም ። ምክንያቱም እግር በእግር እየተከታተሉ በፌስቡክ ፔጄ ላይ የምጽፈውን የሰማዕታቱን ታሪክ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ አንባቢዎቻቸው መረጃ በማቅረብ የሰማዕታቱ ቤተሰቦች እንዲረዱ ስላደረጉ ከልብ አመሰግናለሁ” ።
መንግሥቱ ጋሼ ሩቅ አልሞ ቅርብ ያደረው ሰማዕት ።
መንግሥቱ ጋሼ ሩቅ አልሞ ቅርብ ያደረው ሰማዕት ።
” በተለይ በየክፍለ ሀገሩ ለማደርገው ጉዞዬ በስዊዘርላንድ በሚኖረው ወንድሜ ጴጥሮስ አሸናፊ አማካኝነት የተዋወቁኳቸው ኢትዮ ዙሪክ የእግር ኳስ አባላትና ደጋፊዎች ፣ በመጨረሻው ጉዞዬ ወንድሜ ዘማሪ ቀሲስ ወንድወሰን በቀለና የሚኒሶታዎቹ አንድነት የሙዚቃ ባንድ አባላት ሙሉ የሆቴልና የትራንስፖርት ፣ እንዲሁም የስልክ ካርድ መሙያ ይሆንሀል ብላችሁ የላካችሁልኝን በአግባቡ ተጠቅሜበታለሁ እናም ምስጋናዬ ካለሁበት ይድረሳችሁ ” ። ይህ ጉዳይ ያለ እናንተ ተሳትፎ የመሳካቱ ነገር አጠራጣሪነቱ ከፍ ያለም ነበር ። ምክንያቱም አሁን እኔ አሁን ባለሁበት ሆኔታ አቅም ኖሮኝ ሁሉንም እንዲህ በተሟላ መልኩ ማቅረብ እችላለሁ ብዬ ማሰቡ ስለሚከብደኝ ማለት ነው ።
ከዚህ በኋላ የሁሉንም የሰማዕታት ቤተሰቦች የመገኛ አድራሻና የባንክ ሒሳብ ጭምር ፖስት ስላደረግሁ ገንዘብንና ሌሎች ጉዳዮችን ከእኔ ጋር ጭምር በትነካኩ ይመረጣል ። አሁን የሰማዕት መንግሥቱ ጋሼን ታሪክ በእርጋታ እንዲያነቡ ልጋብዝዎት ። መልካም ንባብ ።
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/44394#sthash.94HuQ3To.dpuf

No comments:

Post a Comment