Thursday, January 22, 2015

ካድሬዎች በየሜዳው የምርጫ ካርድ በግዳጅ እየሰጡ ነው

election












(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ከተማ ከ2 ምርጫ በፊት በ0 የተሸነፈው የገዢው ስርዓት ባለፈው ምርጫ 96.6% አሸንፍኩ ማለቱን ተከትሎ ምርጫው መሳቂያ እንደሆነበት ብዙዎች ሲተቹበት የቆየ ጉዳይ ነው:: በባለፈው ዓመት ምርጫ ብዙ ሰው “ብንመርጥም ስለሚጭበረበር ግዜዬን አላጠፋም” በሚል ካርድ ያልወሰደ ሲሆን ዘንድሮ በግድ እንዲወስዱ እየተደረገ ነው::
የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ያነጋገሯቸው ምንጮች እንደሚሉት ስርዓቱ ያዘጋጃቸው ካድሬዎች በየቤቱ እየሄዱ የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ እያስገደዱ ሲሆን ከታክሲና አውቶቡስ መውረጃ ቦታዎች ላይ ወንበር እና ጠረጴዛ አስቀምጠው አላፊ አግዳሚውን በግድ የምርጫ ካርድ እንዲውስድ እያስገደዱት ነው::
የምርጫ ካርድ የሚሰጡት የኢህአዴግ ካድሬዎች በመሆናቸው ካርድ ሲሰጡ ኢሕ አዴግን ምረጡ እንደሚሉ የደረሰን መረጃ ያመለክታል::

No comments:

Post a Comment