Wednesday, January 14, 2015

አንድ ጥያቄ ስለ አንድነት! – አቤ ቶኮቻው

አንድነት ፓርቲ ምርጫ ቦርድ ባስጠነቀቀው መሰረት ጠቅላላ ጉባኤውን አድርጎ ሊቀመንበሩን ድጋሚ መርጧል። ይሄንንም ከምርጫው ቀን ቀደም ብሎ ጀምሮ በፎቶግራፍ እያስደገፉ ያፕርቲው ልጆች ሲያሳዩን እኛም እየተደነቅን ላይክም ሼርም ስናደርገው ሰንብተናል። ልክ የጠቅላላ ጉባኤው እለት ታድያ አቶ ትዕግስቱ የተባሉ ሰውዬ ሌላ ቦታ የአንድነት ሊቀመንበር ተደርገው ተመረጠዋል ተባልን።
ከሁሉ ታድያ ግራ የገባኝ ስለ አቶ ትግስቱ የሚከራከሩላቸው የ ኢህአዴግ ስጋ ዘመዶች እንጂ መራጮቻቸው አይደሉም። ምንደነው ነገሩ የኢህአዴግ የስጋ ዘመዶች ስለ አቶ ትዕግስቱ በጣም አብዘተው የተጨነቁት ለምንደነው… የአቶ ትዕግስቱ መራጮችስ ስለምን አደባባይ ወጥተው ”እኛ ነን ትክክለኛውን ምርጫ ያደረገነው…” ብለው ለምን አይሞግቱንም። እውነት እውነት እላችኋለሁ አስራ አንድ ሰው አልጠራም እስቲ አንድ ሰው ጮክ ብሎ እኔ ከአቶ ትግስቱ ወገን ነኝ ሊቀመንበሬ እርሳቸው ናቸው ይበለን… !
ይሄው ቃለ ማህላ ሲፈጽሙ የተነሱት ፎቶ እንኳ ሳይቀር በስለላ የተገኘ ነው! ለንጽጽር የዋናውን አንድነትም ቃለ ማህላ ፎቶ እንየውማ! (የመጀመሪያው ዋናዎቹ አንድነቶች የመረጡዋቸው አቶ በላይ ሲሆኑ ቀጥሎ ያሉት ደግሞ አቶ ትግስቱ ናቸው…)
tigetu

No comments:

Post a Comment