Thursday, January 22, 2015

ሰበር ዜና – የመን እየታመሰች ነው፣ የፕሬዝዳንቱ መኖሪያ በአማጽያኑ ተከቧል


(ECADF News) አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከአውሮፓ ወደ ኤርትራ ሲያቀኑ የተሳፈሩበት አውሮፕላን የመን ላይ መንገደኞችን ሊያወርድ እና ሊያሳፍር ላጭር ጊዜ ባረፈበት ወቅት ነበር በየመን ደህንነቶች ተጠልፈው ለወያኔዎች ተላልፈው የተሰጡት።
Smoke rises from a large explosion in the Yemeni capital on Monday
BBC PHOTO: Smoke rises from a large explosion in the Yemeni capital on Monday
በዚህ የተነሳ ኢትዮጵያውያን በየመን መንግስት ላይ ጥርሳቸውን እንደነከሱ ነው ያሉት።
ይሁንና የመን በራሷ የውስጥ ጉዳይ ቅጥ ባጣ ትርምስ ውስጥ የምትገኝ ደሃ የአረብ ሃገር በመሆኗና ኢትዮጵያውያኑ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በየመን መንግስት ላይ ማሳደር የሚችሉት ተጽዕኖ እምብዛም ባለመሆኑ ለጊዜውም ቢሆን አይናቸውን ከየመን ላይ ለማዞር ተገደዋል፣ ጥርሳቸውን ግን እንደነከሱ ነው!
ከትላንት በስትያ ጀምሮ ግን ከየመን ዋና ከተማ ሰንዓ በመውጣት ላይ ያሉ ዜናዎችን የሚከታተሉ ኢትዮጵያውያን ፊታቸው ላይ ፈገግታ ሊነበብ እንደሚችል መገመት ብዙም አያስቸግር። ምናልባት የየመን ወዳጅ ለሆኑት ወያኔዎች ዜናው ሊፈጥር የሚችለው እንደምታ የተለየ ሊሆን ይችላል።
የመን ቀውጢ ሆናለች፣ የየመን ፕሬዚዳንት ዋና አማካሪም በአማጽያኑ ቁጥጥር ስር ውለዋል፣ የሺዓ አማጽያን የፕሬዝዳንቱ አማካሪ በእጃቸው እንደሚገኙ አሳውቀዋል። በሰንዓ በሚገኘው የፕሬዝዳንቱ መኖሪያ ላይ አማጽያኑ ተኩስ ከፍተዋል፣ ማንኛውም አይነት ተሽከርካሪ ከፕሬዝዳንቱ መኖሪያ ብቅ ባለ ቁጥር ከባድ መሳሪያ እየተኮሱ ፕሬዝዳንቱን በገዛ ሃገራቸው እና መኖሪያቸው የቁም እስረኛ አድርገዋቸው ይገኛሉ።
የዜና አውታሮች እንደሚሉት ከሆነ የየመን መንግስት አይደለም መላው የመንን ዋና ከተማዋን ሰንዓን እንኳ አይቆጣጠርም።
የምእራባውያን ፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ ደግሞ የየመን መንግስት መሬት እየከዳው ነው፣ አብቅቶለታል።
ይህ በዚህ እንዳለ የአሜሪካ መንግስት በሰንዓ የሚገኙ የአሜሪካ ኢምባሲ ሰራተኞቹ በተጠንቀቅ እንዲጠብቁና በማንኛውም ሰዓት ሂሊኮፕተሮች በኢምባሲው ቅጥር ግቢ አርፈው ሰራተኞቹን የማውጣት ዘመቻ ሊጀምሩ እንደሚችሉ አሳውቋል። ለዚህም ተግባር ዩኤስኤስ አይዎ ጂማ የምትባለው የአሜሪካ የጦር መርከብ በገልፍ ኦፍ ኤደን ቦታ ይዛ ትጠባበቃለች።

No comments:

Post a Comment