Thursday, August 20, 2015

በተፋፈነ ሁኔታ በአንድ ትልቅ መኪና ተደብቀው ሲሄዱ የተያዙ ከ100 በላይ ኢትዮጵያውያን ታሰሩ

ዳዊት ሰለሞን እንደዘገበው
በኬንያ መሩ ካውንቲ በቁጥጥር ስር የዋሉት 100 ኢትዮጵያዊያን ዛሬ አመሻሽ ነው፡፡በወጣትነት የእድሜ ክልል የሚገኙት ታሳሪዎቹ በተፋፈነ ሁኔታ በአንድ ትልቅ መኪና ተሳፍረው ወደ ናይሮቢ በመገስገስ ላይ እንዳሉ በፖሊሶች በተደረገ ፍተሻ መያዛቸው ታውቋል፡፡ታሳሪዎቹ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት አቅደው የነበሩ መሆናቸውም ተነግሯል፡፡
እንደ ዴይሊ ኔሽን ዘገባ ከሆነም ስደተኞቹ በሞያሌ በኩል በድብቅ በማለፍ ወደ መሩ ካውንቲ ማምራታቸውን መረጃ የነበራቸው የኬንያ ፖሊሶች በቀላሉ በቁጥጥር ስር ሊያውሏቸው ችለዋል፡፡

- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45994#sthash.zey5Ff9d.dpuf

ethiopia
ኢትዮጵያዊያኑ የሚገኙበት የካንጌታ ፖሊስ ጣቢያ ኃላፊዎች ምርመራ በማከናወን ላይ እንደሚገኙ መናገራቸው ተወስቷል፡፡
በሚያዘያ ወር ከሁለት የተለያዩ ቤቶች ከኢስሊና ኪማኢኮ 40 ኢትዮጵያዊያን በፖሊሶች በተደረገ አሰሳ መታሰራቸው ይታወቃል፡፡
እስረኞቹ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማምራት ወደ ኬንያ መግባታቸውን ከመናገር ውጪ ምንም አይነት የጉዞ ዶክመንት አለመያዛቸው ተስተውሏል፡፡
ስደተኞቹ በሁለት ቡድን ተከፋፍለው ወደ ሁለት ቤቶች እንዲያመሩ ከመደረጋቸው አስቀድሞ ወደ ኬንያ በአንድነት መግባባቸውን የተናገሩት ፖሊስ ኦፊሰሩ በርናርድ ኒያክዋካ ‹‹ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ውስጥ እንዲኖሩ ተደርገው ነበር፡፡በዚህ ውስጥ ተሳትፎ ሲያደርጉ የነበሩ ሰዎች ላይ ክስ ለመመስረት ወኪሎቻቸውን በማፈላለግ ላይ እንገኛለን››ብለዋል፡፡
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45994#sthash.zey5Ff9d.dpuf

No comments:

Post a Comment