Thursday, August 20, 2015

በቤንሻንጉል-ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በሚኖሩ ዐማሮች ላይ የተፈፀመ የዘር ማጥፋት ወንጀል - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46023#sthash.dQh0MHWD.dpuf

በዐማሮች ላይ የተፈፀመ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ልዩ ዘገባ ቅፅ ፫፣ ቁጥር ፩ ማክሰኞ ነሐሴ ፲፪ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. ለመስማትም ሆነ ለማውራት ይዘገንናል!! በምን ቋንቋ እንግለጸው! ሰውን ሰው በላው! ጉምዞች ዐማሮችን አርደው በሏቸው!
 ሀ) መግቢያ
 ሞረሽ-ወገኔ ይህ አስደንጋጭ ዜና እንደደረሰው የድርጊቱን ዘግናኝነት እና ፍፁም ኢሰብዓዊነት ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ ከዚያም አልፎ ያለአግባብ ግለሰቦችንም ሆነ ድርጅቶችን ላለመወንጀል፣ ስለሁኔታው ከሥር መሠረቱ መረጃዎችን ለማጣራት ሙከራ አድርጓል። ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን እና ሰብዓዊነት የሚሰማችሁ ግለሰቦች ሁሉ እንድትገነዘቡልን የምንፈልገው፣ በእንዲህ ዓይነት እጅግ የሚሠቀጥጥ ድርጊት ላይ ዘገባ ለማዘጋጀት ምን ያህል ከባድ የኅሊና ፈተና እንደሚደቅን ንፁሕ ኅሊና እና አስተዋይ አዕምሮ ያለው ሰው ይስተዋል አልባልም።

Benishangul

አንዳንድ ጊዜ «ቋንቋ ኃሣብን በትክክል ለመግለጽ ያስቸግራል» ይባላል። ዕውነት ነው፣ እንደዚህ ያለ ለመስማትም ሆነ ለመናገርም የሚቀፍ እና የሚከብድን ድርጊት፣ ድርጊቱን ባየው ሰው፣ በተረዳው እና በገባው መልክ ለሁለተኛ እና ለሦስተኛ ወገን ለመግለጽ ይቸገራል። የቋንቋ ሊቃውንቱም «ቋንቋ አንዳንድ ጊዜ ኃሣብን በትክክል አይገልጽም» የሚሉት እንደዚህ ያሉ ድርጊቶችን በአዕምሯቸው በተቀረጸው መንገድ በቃላት አሳክቶ ለመግለጽ ሲፈልጉ ተስማሚ ቃል ስለሚያጡ ነው። በዚህ በምንኖርበት በ፳፩ኛው መቶ ክፍለ ዘመን፣ ያውም የክርስትና ኃይማኖትን ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ተቀብሎ በኖረ እንደ ኢትዮጵያ ባለ የረጅም ዘመን ታሪክ ባለቤት በሆነ ሕዝብ መሃል፣ «ሰውን ሰው በላው፣» «ጉምዝ የተባለው ጎሣ አባሎች የዐማራውን ነገድ አባሎች በጠላትነት ስሜት ተነሳስተው ከወያኔ በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት አርደው በሏቸው» የሚለውን ክፉ ዜና ላልሰሙና ላላወቁ ሰዎች ማስረዳት እጅግ ይከብዳል፣ ይቀፋል፣ በምን ቃላትም ለመግለጽ እንደሚቻል ያስቸግራል። ድርጊቱ ግን በአሳዛኝ መልኩ ተፈጽሟል። በዕውነትም አንበሣ፣ ጅብ ወይም ሌሎች ሥጋ-በል አራዊት በመሰሎቻቸው ላይ የማይፈጽሙትን ድርጊት፣ ሰው ፣ሰውን አርዶ በሚጥሚጣ አጣጥሞ ሲበላው ላየ ሰው፣ ለሌላ ወገኑ ለመግለጽ ቃላት ያጥረዋል። የአገላለጽ መንገዱም ይጠፋዋል፤ ይከብደዋል። «ሰው ሰውን በላው» ማለት ተራ አባባል ይሆናል፤ የተለመደ ተራ አጠቃቀም ይሆናል። በምን ቃል ቢገለጽ ነው ድርጊቱ «ትንግርት፣ ጉድ፣ እግዚኦ የፈጣሪ ያለህ» የሚያሰኘው! ይህ ነው እንግዲህ «አንዳንድ ጊዜ ቋንቋ ኃሣብን በትክክል ለመግለጽ አያስችልም» የሚባለው። የሰው ልጅ ከጅብ እና ከአንበሣ፤ በአጠቃላይ ሥጋ- በል ከሆኑ እንስሶች የከፋ አውሬ መሆኑ እንዴት ይገለጻል? - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46023#sthash.dQh0MHWD.dpuf

No comments:

Post a Comment