Tuesday, August 11, 2015

“ሰላማዊ ትግል ለማይገባዉ አምባገነን በሚገባዉ ቋንቋ እናናግረዋለን!!” – ድምጻችን ይሰማ ደቡብ አፍሪካ (ደ.ይ.ድ.አ)

  በትናንትናዉ እለት ሰኞ 10/08/2015 በደቡብ አፍሪካ የሚገኘዉ የሰላማዊ ትግል ተምሳሌት ድምጻችን ይሰማ ታላቅ ስብሰባ አደርገ። እንደሚታወቀዉ በቅርቡ አንባገነኑ ወያኔ ሚሊዮኖች በወከሏቸዉ የንጹሃን የህዝበ ሙስሊም ኮሚቴዎች ላይ ታሪክ ይቅር የማይለዉ ኢ_ፍትሐዊ ፍርድ በመፍረዱ ምክንያት የደቡብ አሪካዉ ድምጻችን ይሰማ ኮሚቴ በጠራዉ የዉይይት መድረክ ላይ የተገኙ ሙስሊም ኢትዮጵያዊን ወገኖች ቁጣቸዉን ገለጹ።

በእለቱ የተከበሩ የህዝበ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ተወካዮችና የሐይማኖት ሊቆች፣ሼሆች፣ ኡስታዞች፣ የተገኙ ሲሆን ሼህ መሐመድ አሚን፣ ኡስታዝ ኡስማን አህመድ፣ የየእለቱ መክፈክቻ ንግግሩ ሹሞች ነበሩ።
” ሰላማዊ ትግል የሚነገርዉ ሰላም ለሚገባዉ እንጂ እንደ ወያኔ ላለ አምባገነን አይደለም ይህ አካሄዳችን ፈጽሞ በወያኔ ታጥቦ ተወስዷል በመሆኑም ሰላማዊ ትግል ማለት ነጭ ወረቀት ብቻ ማዉለብለብ አይደለም ” ኢስላም ሰላም ነዉ ” ነገር ግን ይህ ለሚገባዉ ብቻ ነዉ ለማይገባዉ ግን የምንሄደዉ መንገድ ሁሉ ለኛ ሰላም ነዉ! በሚል ታሪካዊ ንግግር የተከፈዉ ስብሰባ በቁጭትና በምሬት የተካሔደ ነበር።


በኦሮምኛ ቋንቋና በአማርኛ ቋንቋ በድንቅ ሁኔታ የተካሄደዉ የትናንቱን የድምጻችን ይሰማ ስብሰባ ላይ በኦሮምኛ ቋንቋ ስነ ግጥም የቀረበ ሲሆን በቅጽል ስሙ ( ፀረ ወያኔ ) በመባል የሚታወቀዉ ገጣሚ አብዱራህማን ቦንከሬ ሙስሊም ወንድሞቻችን በወህኒ ተከርችመዉ መሬት ለመቀራመት ወደ ሐገር ቤት የነጎዱ በሙስሊሙ ስም የሚንቀሳቀሱ የዲን ጠላቶች የወያኔ ዲያስፖራዎችን በቅንፍ ዉስጥ ያስገባ ስነ ግጥም ያቀረበ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ በተለያዩ የህዝበ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን በደቡብ አፍሪካ በሚያደርጉት ዝግጅት ላይ የተለያዩ ጽሁፎችን ይዞ የሚቀርበዉ የጆሐንስበርጉ ጀማል ዲያስፖራ ላሜ ቦራ በሚል እርእስ ከበድ ያለ ምልእክት አስተላልፏል።

በእለቱ የተካሄደዉ ስብሰባ በፍቅር ያስተናገዱት ሼህ ይስሐቅ ሙስሊም ማለት ከግርግዳ ጀርባ ብርሐን የሚመለከት ህዝብ ነዉ ወደ ብርሐንኑም እኛዉ እራሳችን እንሄዳለን ሲሉ ሰምና ወርቅ ያዘለ ንግግር ሲያስቀምጡ ኡስታዝ ፈይሰልም አስተምሮት ያለዉ ድንቅ ንግግር ከማድረጋቸዉም ባሻገር ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ አይወክለንም ሙስሊም ካልሆኑ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ጋር ሊያጋጬን የማይጭረዉ የማይንደዉ ሐረካት እንዳለ እናዉቃለን እኛ የጋራ ጤላታችን ወያኔ ነዉ የሚሉ ታላላቅ ንግግሮችም የእለቱን ታሪካዊነት ሲያጎሉት ። በስተመጨረሻ አጠቃላይ ዉይይቱ ወደ መላዉ ሕዝብ የገባ ሲሆን የዉይይት መድረኩ በድምጻችን ይሰማ ደቡብ አፍሪካ አወያዮች የተመራ ነበር በመሆኑም፡…..

1. ኡስታዝ ሸምሱ
2. ጋዜጤኛ አብዱራህሚን
3. ከድምጻችን ይሰማ ኮሚቴዎች ጋር ታስሮ የነበረዉና በዋስ ከወጣ ወዲህ በስደት ደቡብ አፍሪካ የሚገኘዉ በሌለበት የ 15 አመት ፍርደኛዉ አሊ መኪ፡ ሲሆኑ ዉይይቱን የከፈተዉ ጋዜጠኛ አብዱራህሚን ለትዉስታ ያህል የፍርደኛ ንጹሐን ሙስሊም ወኪሎችን የፍርድ ቤ/ት ዉሎ ባስታወሰ መልኩ የማነቃቂያ ንግግሮች በማድረግ ሐሳብ የመስጤቱ እድል ወደ ህዝቡ ከሆነ ህዝቡ ከደቡብ አፍሪካ ከተለያዩ ስፍራዎች የተገኘዉ በቁጭት የተሞላዉ ህዝበ ሙስሊም እጥዮጵያዊያን ወገኖች ” ጉዞዉ ወደ ትግል ብቻ ነዉ ” የሚል ሐሳብ መሆኑን በጥቅል ያሳየ ሲሆን በሼህ ሸምሱም የተመራዉ የመፈክር ስእነ ስርአት (ለዲናችን እስከመጨረሻዉ ለመስራት ዝግጁ ነን ገንዘብም ሆነ ህይወት ለመስጠት ዝግጁ ነን በወያኔ አያሸብረንም!!! ) የሚል የህብረት መፈክር ።


ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ
ጉድሽ ወያኔ

- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45765#sthash.vWvtmncR.dpuf
south africa

No comments:

Post a Comment