Saturday, August 15, 2015

የአፋር መስተዳደር አዲስ ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳደር ሾመ

afar
አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው:
በኢህኣደግ ሰርዓት እረጂም ዓመታት በክልል መሪነት በማገልገል ሪከርድ የሰበረው ብቼኛ ኣገልጋይ ኣቶ እስማዒል ዓሊ ሲሮ ባለፈው ምረጫ ለፈደራል ፐርላማ መወዳደራቸውን ተከትሎ ዛሬ ኣዲስ መሪ ተሾሟል።
ዛሬ የተሾሙት ኣቶ ኣዋል ዓርባ ዑንዴ ከምርጫው ቀደም ብሎ ከግብሪና እና ገጠር ልማት ቢሮ ወደ ምክትል ረዕሰ መስተዳደር በማምጣት የተሾሙ ሲሆን ኣሁን ደግሞ ከዛሬ ጀምሮ የክልሉ ጊዜያዊ ፕረዝዳንት ሆኖው ይቆያሉ ተብሏል።
በኣሁኑ ወቅት በኣጣቃላይ በኢህዴግ መሪዎች ዉስጥ ያለውን ኣለመግባባትን ተከትሎ የኣፋር ክልል ካድረዎች ዉስጥም ክፍተኛ የሆነ ኣለመግባባት ኢየታየ ነው።
በነግራችን ላይ የኣፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ( ኣብደፓ) በነገው ዕለት ጣቅላላ ጉባኤ ያድርጋል ትብሎ ይጠበቃል።
በዚህ በነገው ሰብሰባ የክልሉ ምክትል ፕርዝድንት፣ የክልሉ ምክሪቤት ኣፌጉባኤ እና የፓርቲ ኃላፊ ይምረጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ወትርዉም ብሆን የኣፋር ክልል መሪ የሚመረጠው በህወሃት ጣልቃ ገብነት ሲሆን ኣሁን በጊዜዊነት የተሾሙት ኣዋል ዓርባ በክልል መሪነት ይቀጥሉ ኣይቀጥሉ ኣይታወቂም።
ኢህአዴግ ህወሀት ባለፉት ሁለት ኣስርት ዓመታት የብሔር ብሔርሰቦችን መብት ኣክብሬያለሁ በሚል ሽፋን በኣፋር ህዝብ ላይ ያደርሰው በደሎች ኢንኳን ጉልቻ መቀያየርን ቀርቶ እራሱ ኢህአደግ ብቀየሪም ታሪክ ይቅር የማይለው የመግደል፣የማፋናቀል፣የማሰር እና በሃብታቸው እንዳይጠቀሙ በማድረግ የፈጸመው በድሎች በኣፋር ክልል የህወሀት ተቃዋሚዎች እንዲበረከቱ ምክንያት ሆነዋል።
በኣሁኑ ወቅት በኣፋር ክልል ወጣቶች ብዙ የትደራረበ ጥላጫ ለኢህአደግ መንግንስት እንዳላቸው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየግለጹ ሲሆን ለምሳሌ ያህል መንግስት በክልሉ ህዝብን በማፋናቀል እየሰራ ያለው ልማት ተብዮው በኣፋር ኣርብቶ ኣደሮች ህይዎት ላይ ያስከተለው ችግር ቀላል ኣይደለም።
እይዉነት ለመናገር የኣፋር ህዝብ ካሁን በፊት ባልፉት ሰርዓቶች በዚህ ሁኔታ ኣልራበም።
በተለይ በምስራቅ የክልሉ ኣክባቢ በኣዋሽ ወንዝ ዳር ይኖሩ የነበሩ ኣርብቶ ኣደሮች ተፈናቅለው መሬታቸው በሙሉ ለመንግስት የስኳር እርሻ ተከለዋል።
የዚህ ዉጤት እነሆ ዛሬ በህዝብ ላይ ክፊተኛ ረሃብ አስከትሎ የኣለም ኣቀፍ ሚዲያዎች መንጋገሪያ ሆኖ ይገኛል።
በኣፋር ክልል እየሞቱ ያሉት ከብቶች ብቻ ኣይደለም፣ ሰዎቹም እየሞቱ ነው።
ኢስካሁን ባለኝ መረጃ መሰረት በዱብቴ ወረዳ ፣ ዳትባሃሪ ኣከባቢ በራሃብ ና በጥም እንዲሁም የቆሸሸ ዉሃ ጠጥተው
የስምንት ህጻናት ህይዎት ኣልፈዋል።
በሚሌ፣ በኦንዳ ፎኦ አከባቢም ከብቶቻቸው ያለቁባቸው ነወሪዎች እራሳቸው ያጠፉ እንዳሉ ሰሚቼያለሁ።
ሌላው ድግሞ በሰሜን የክልሉ ኣከባቢ ከዳሎል ኢስከ ማጋሌ ወረዳ ያለው የትግራይ መሬት ነው በማለት ነዋሪዎችን በማጋጨት ብዙ ኣፋሮች በወያኔ ሚልሻዎች ተገድልዋል።
በባራህሌ ወረዳ የሚገኘው ኣሞሌ ጨው ለኣንድት የትግራይ ሃብታም ካልሰጠሁ በማለት የባራህሌ ወረዳ ኣፋሮችና ወያኔ ከተፋጠጡ ወራት ተቆጥረዋል።
በዳሉል ወረዳ ኣብዛኛው መሬት በዋያኔ ተጠቃሚነት ለውጭ ኣገር ድሪጅቶች የተሰጠ ሲሆን የቀረው መሬትም በቅርብ ለፖጣሽ ኣምራቶች ተሰጥቶ ህዝብ ገና ካሁን በኋላ ልፈናቀል መሆኑን የኣፋር ክልል የወያኔ ኣገልጋይ ተሰናባቹ እስማዕል አሊ ሲሮ ባለፈው ሳምንት በኢቢሲ በሰጡት መግለጫ የገለጹ ሲሆን ኣሁን በኣዲሱ በዳሉል ወረዳ ለፖጣሽ የተሰጠው መሬት ስፋቱ ከሶስት መቶ ሲልሳ ኣምስት በላይ ስከዌር ኪሎ ሚትር መሆኑን በካምፓኒው ዲህረ ገጽ ኣምቢበውለሁ።
ሌላውና ቀዳሚው የኣፋር ክልል የጨው ሃብት ባለበት የሆነችው ኣፍደራ ሲትሆን በኣፍደራ የጨው መሬት የለለው የወያኔ ባለስልጣን፣የወያኔ ጀነራል የለም።
ኢንዲሁም ባለፈው ሳምንት በኣስመራ ታስረዋል የተባለው የኤረትራ የጻጥታ ሀላፊ ( ሚነስተር ) በኣፍደራ የጨው መሬት ኣላቸው፣ የቀድሞው የትግራይ ክልል መሪ ኣቶ ፀጋይ በርሄን ጨምሮ ኢያንዳንዳቸው የህወሀት መሪዎች በኣፍደራ የጨው መሬት ኣላቸው።
ሌላው ዶቢ ዓስቦ ( የዶቢ ጨው ሲሆን ዶቢ የሚባለው በኣፋር ክልል ኢትዮጲያ ከጀቡቲ በሚያዋስን ቦታ ላይ የሚገኝ የጨው መሬት ነው።
ይህ መሬት ሙሉ በሙሉ የኣንድ ባለሃብት ሆኖ ይሚገኝ ሲሆን እርሱ ማሀመድ ሁመድ ይባላል።
በኣፋሮች ዶቢ ዓስማሀማድ በሚል ቅጽል ሲሙ ሲታወቅ በህወሀት የተለመደው ልማታዊ ባለሃብት የሚል ማዓረግ ተስጦታል።
ለነገሩ ልማታዊ ባለሃብት ማለት የወያኔ ደጋፊ የሆነ ባለሃብት ማለት ኣይደል ?
ትርጉሙ በተዘዋዋሪም ብሆን ይህ ብሆን ነው እንጂ ልማታዊማ ብሆን ሲንት ህዝብ በራሃብ ኢና በዉሃ ጥም እየሞተ እያየ እንዳላየ የሚያልፍ ሃብታም ልማታዊ ባለሃብት ሲባል ምን ትለውለህ ?
የብሔር ብሔረሰቦች መብት ኣስክብረናል በሚል ሽፋን የብሔር ብሔርስቦችን ባህሎች፣ሃይሞኖቶች፣ሃብቶችና ክርሶች እያጠፋና እዘረፈ ያለው ህወሀት በኣፋር ክልል ያለው እውነታ ግን ዜሮ ዜሮ ነው።
ለምሳሌ፦ በየኣጋጣሚው ባህላዊ ጨፈራ በተለቭዥን ከማሳየት የዘለለ የተከበረ መብት የለም ።
ኣራት ነጥብ

- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45865#sthash.mI7RfWa2.dpuf

No comments:

Post a Comment