Saturday, August 15, 2015

በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በወረዳው አመራር ላይ በተወረወረው ቦምብ 2 ልጆች ሞቱ * አመራሩና ባለቤታቸው ቆስለዋል - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45841#sthash.PGATYadL.dpuf


news

የደህሚት ድምጽ እንዘገበው በደቡብ ወሎ ዞን፤ ቦረና ወረዳ ውስጥ ሓምሌ 4/2007 ዓ/ም ወደ ወረዳው አመራሩ በተወረወረው ቦምብ ምክንያት 2 ልጆች መገደላቸው ተገለፀ። በአማራ ክልል፤ ደቡብ ወሎ ዞን፤ ቦረና ወረዳ ውስጥ ሓምሌ 4/2007 ዓ/ም ከሌሊቱ 5 ሰዓት ላይ በወረዳው አመራር በአቶ መሓመድ ረሽድ ላይ በተወረወረው ቦምብ 2 ልጆች መሞታቸውና ራሱና ባለቤቱም ጭምር ክፉኛ በመቁሰላቸው ምክንያት ደሴ ሆስፒታል እያተካሙ መሆናቸውና እስካሁን ድረስም ድርጊቱ የፈፀመው አካል እንዳልተያዘ ለማወቅ ተችሏል። በአሁኑ ግዜ በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የስርዓቱ ባለስልጣናት በህዝቡ ላይ በሚያደርሱት ከፍተኛ ችግር ምክንያት ህዝቡ በአስተዳድሪዎቹ ላይ የበቀል እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ይታወቃል - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45841#sthash.PGATYadL.dpuf

No comments:

Post a Comment