Thursday, December 4, 2014

የጽዮንን በዓል አክብረው ከተመለሱ ምዕመናን ውስጥ መኪና ተገልብጦ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ

ከዘመድኩን በቀለ
በየዓመቱ ህዳር 21 ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት የሚከበረውን የህዳር ጽዮን በዓል ለማክበር ከአዲስ አበባ ተነስቶ የነበረው የአቡነ አሮን መንፈሳዊ የጉዞ ማኅበር መኪና 60 ተጓዥ ምእመናንን ይዞ ከበዓሉ መልስ ዛሬ ከወልድባ ሰቋር ጉብኝት በኋላ ወደ ጎንደር በመመለስ ላይ ሳለ ከአንባ ጊዮርጊስ ወጣ ብሎ ልዩስሙ 44 ተብሎ ከሚጠራው ሥፍራ ላይ አደጋ ደርሶበት ብዙ ሰው ተጎዳ ።
axum
 በአደጋው እስካሁን 3 ተጓዥ መንገደኞች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን ቁጥራቸው በዛ የሚሉት ደግሞ ቀላልና ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸው በጎንደር ሆስፒታል በሕክምና ላይ ይገኛሉ ።

 ከእነዚህ መንገደኞች መሃል በተለይ ዘማሪ ምትኩ በከባድ ጉዳት ውስጥ እንደሚገኝ በአደጋው ሰዓት ወዲያው በመድረስ የሞቱትንም ሆነ የቆሰሉትን ወደ ሆስፒታል የወሰደው የማኀበረ ወይንዬው ሰብሳቢ መ/ር ደረጀ ነጋሽ በስልክ ገልጾልኛል ።
 የአደጋው አድራሽ በቅጽል ሰሙ ቀይ ሽብር በመባል የሚታወቀው የቻይና ስሪት የሆነው መኪና ሲሆን የአደጋውን መንስኤ ግን የክልሉ ፖሊስ እያጣራ መሆኑንም ደረጀ አክሎ ነግሮኛል ።
አሁን ይህን ማስታወሻ በመጻፍ ላይ ሳለሁ ደረጀ የሟቾች ቁጥር ወደ 4 ከፍ ብሏል ብሎኛል።
እንግዲህ ምን እንላለን ያረፉትን ነፍሳቸውን ይማር ።

No comments:

Post a Comment