Thursday, December 4, 2014

ኦባንግ ሜቶ ከኢትዮጵያውያን ጋር በሚኒሶታ ሊወያዩ ነው

(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ኦባንግ ሜቶ ወደ ሚኒሶታ በመምጣት የፊታችን ቅዳሜ ዲሴምበር 6 ቀን 2014 ዓ.ም ከኢትዮጵያውያን እና ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር እንደሚወያዩ ታወቀ።
Save Ethiopian Meeting with Obang metho in Israel
ቅዳሜ ሴንት ፖል በሚገኘው ኬሊ ኢን ሆቴል ከቀኑ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በሚደረገው በዚህ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ኦባንግ ሜቶ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ዙሪያ ከሚኒሶታ ሃገር ወዳዶች ጋር ይየሚነጋገሩ ሲሆን የስብሰባው ዋና ዓላማም በተለይ በተቃዋሚዎች አካባቢ መደረግ ስላለባቸው የጋራ ትብብሮች እንደሚሆን አስተባባሪው አቶ ግርማ ብሩ ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል።
“እንደሚታወቀው የኢሕአዴግ መንግስት ላለፉት 23 ዓመታት ካለምንም እፍረት ስልጣኑን በእጁ እንዳስገባ ይገኛል፤ ይህ ሆኖ እያለ ግን በተቃውሚዎች በኩል እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ሁሉም በየፊናው በመሆኑ ትግሉን ወደ አንድ አቅጣጫ ለማምጣትና አንድ ግብ ያለው ትግል ለማካሄድ አቶ ኦባንግ ሜቶን ወደ ሚኒሶታ ጋብዘናል” ያሉት አስተባባሪው አቶ ግርማ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በተጠቀሰው ሆቴል ከቀኑ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያውያኑ ከኦባንግ ሜቶ ጋር ቅዳሜ ዲሴምበር 3 ቀን 2014 ዓ.ም የሚያደርጉበት የሰብሰባ አድራሻ 161 St Anthony Ave, St Paul, MN 55103 ሲሆን የበለጠ መረጃም በ612-325-8690 ማግኘት እንደሚቻል አቶ ግርማ አስታውቀዋል።
በሌላ ዜና በያዝነው ዲሴምበር ወር በአኝዋክ በአንድ ቀን ከ400 ሰዎች በላይ የተጨፈጨፉበት 11ኛ ዓመት የመታሰቢያ ቀን በዚሁ በሚኒሶታ በጋምቤላ ኮምዩኒቲ አማካኝነት ይዘከራል።

No comments:

Post a Comment