Saturday, December 20, 2014

ይህም አልፎ እናየው ይሆናል

ከደቂቃዎች በፊት ሠንጋተራ አካባቢ ነበርኩ፡፡ አንድ ቦታ ላይ ችምችም ብለው የተሠሩና በመጠናቀቅ ላይ ያሉ ሦስት ትላልቅ ሕንጻዎችን አየሁ፡፡ ለቀድሞው ቁጭራ ሠንጋራ ከፍተኛ ግርማ ሞገስ አላብሰውታል፡፡ ከአንድ ሰው ጋር ስለነበርኩ ወሬ ለማጧጧፍ ፈለግሁና በቀልድ መልክ “እርግጠኛ ነኝ እነዚህ ሕንጻዎች የትግሬ መሆን አለባቸው” አልኩ፡፡ ያ አብሮኝ የነበረ ሰው ለካንስ ዝርሩን ያውቅ ኖሮ ቀጣዩን ታሪክ አጫወተኝ፡፡ እኔም ይህ ዓይነቱ ነገር ቢያስጠላኝም ታሪክን እየመዘገቡ ላሉ ሰዎች አንዳች ግባት ይሆናል በሚል እሳቤ ባጭሩ ልነግራችሁ ወደድኩ፡፡ ለነገሩ ሳይመዘገብ የቀረ ወያኔዊ ቅሌት ሲኖር አይደል! ለማንኛውም ምድረ አበሻ በምቀኝነት ተንጨርጨሪ እንጂ ይህችን የሰማሁዋትን ነገር አሁኑኑ እዘረግፋታለሁ፡፡
የዚህ ሕንጻ ባለቤት ብርሃኔ ግደይ ይባላል፡፡ አበባ ግደይ የምትባል እህቱ መገናኛ ሚ/ር ከፍተኛ ባለሥልጣን ናት አሉ፡፡ ሚስቱም የሥዩም መስፍን እህት ናት፡፡ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ እዚሁ ሠንጋራ ላይ “ዮቤክ ኤሌክትሮኒክስ” የምትል አንዲት ትንሽዬ ሱቅ ነበረችው፡፡ በዚያች እየተዳደረ  እንደማንኛውም የአካባቢው አነስተኛ ነጋዴ ራሱንና ቤተሰቡን በዝቅተኛ ኑሮ ያስተዳድር ነበር፡፡ ነገር ግን ወዳለው ተጠጋ ነውና በዘሩ ከእብቁና ከንፋሹ የመሀል አገር ሣይሆን ከ“ወርቁ” ዘውግ የተገኘ ቀብራራ ወያኔ ከመሆኑም በተጨማሪ ከቱባው ወያኔ ከሥዩም መስፍን ደም ጋር ደሙን በጋብቻ በመቀላቀሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ሀብትና ንብረት  ባለቤት ሊሆን በቅቱዋል፡፡ መታደል ነው፡፡ የምን ኅሊና – የምን ማሰብና አንጎልን መጠቀም ነው፡፡ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ያለችው ፍጡር ዱሮ ለወንድሞቼና እህቶቼ የተሰጠች ልዩ መጠሪያ ነበረች፤ አሁን ደግሞ ዘመን ተገለበጠና እኔ ለወያኔዎች መጠሪያነት አዋልኳት፡፡ ይህም ሲያንሳቸው ነው፡፡ በማሰር፣ በመግደል፣ በሸርና በተንኮል ዜጎችን በማጣላትና በማናጨት፣ በጥቅም በመደለል፤ እስከ‹ጥግ›  በመጨከን … ሥልጣንንና ሀብትን እስከወዲያኛው ማቆየት ቢቻል ኖሮ ከወያኔ በብዙ ነገር ይሻሉ የነበሩት ብልጡ ራስ ተፈሪ እና/ወይም አረመኔው መንግሥቱ ኃ/ማርያም ከሁለት አንድኛቸው እሰካሁን አራት ኪሎን የሙጥኝ ብለው ባልለቀቁ ነበር – እንደዚያ ያለ ቀመር አይሠራም፤ የለምም፡፡ ግን ሰዎች ስንባል በጣት ከሚቆጠሩ ጥቂት የታደሉ በስተቀር ብዙዎቻችን በተፈጥሯችን የለየልን ደናቁርት ስለሆንን ይመስላል አንዳችን ከሌላኛችን አንማርም፡፡ የነዚህ የወያኔዎች ድንቁርናና አህያነት ደግሞ ለከት አጣ – ግን እኮ ልማድ ሆኖብን እንጂ አህያ ለመልካም ተምሣሌትነት ነበር መጠቀስ የነበረባት – በለፋችና በቅንነት ባገለገለች ለምን መሳደቢያ ትሁን፡፡ ይህም አንዱና ሌላው ሞኝነት ነው፡፡
ለነገሩ ወያኔዎች ቢ…ሩ ቢቀ…ብን እውነታቸውን ነው፡፡ ለቅጣት መምጣታቸውን ለሃይማኖታውያኑ የስብከት ፍጆታ እንተወውና – እነሱም እንደሌሎቻችን ሁሉ በሕይወት አሉ ብዬ በበኩሌ ባላምንም  – እኛም ከነሱ ከወያኔዎቹ የባስን አህዮች ነን – ከአራት ሚሊዮን የተውጣጡ የጠራራ ወንበዴዎች ዘጠና ምናምን ሚሊዮን ሕዝብ ካነሆለሉና ከፋፍለው ከገዙ “ይደልዎሙ” (ይገባቸዋል) ከማለት ውጪ ምን ሊባል ይችላል? “ወደሽ ከተደፋሽ …” ነው ነገሩ ወንድሜ፡፡ ቀኒቱ ግን አትቀርም፡፡ ሰማይ ዝቅ፣ ምድር ከፍ ብትል የፈጣሪን ፍርድ ሊያስቀር የሚችል ወያኔዊ “ጥበብ”ና ኃይል የለም፡፡ ሃያ አራት ዓመት ደግሞ በሀገር ደረጃ ሲታይ በጣም ኢምንት ዘመን ነው – ከወያኔዎች የተለዬ ጭራቃዊ አገዛዝ አንጻር እንደ 2400 ዓመታት ቢቆጠርም፡፡ ሦስት ሺህ ዘመንስ በከንቱ ነጉዶ የለም እንዴ፡፡ በነገራችን ላይ ወያኔዎች አይዟችሁ – በያዛችሁት መንገድ እንደልባችሁ ፈንጩ፡፡ ግደሉ፤ እሰሩ፤ ጠጡ ፤ ብሉ፤ ጨፍሩ፤ ተዋሰቡም፡፡ የምትኖሩት ዕድሜም ከሺ በላይ በመሆኑ ስለዕድሜ ዘመናችሁ አትጨነቁ፡፡ ብትሞቱም ትተካካላችሁ – እስከዚያው፡፡ ያቺ ክፉ ሰዓት ስትመጣ ግን …
ብርሃኔ በቀሰቀሰብኝ ቁጭት አዲስ አበባን ለቅጽበት ያህል ቃኘሁዋት፡፡ እናም እላለሁ – በተለይ አዲስ አበባ ውስጥ አሥር አዳዲስ ዘመናዊ ሕንጻዎችን ካያችሁ ካለማጋነን ዘጠኙ የወያኔ ትግሬ ናቸው፡፡ አሥር ዘመናዊ አውቶሞበሎችን አስፋልት ላይ ሲፈሱ (“ሱ”ን አጥብቁልኝ ‹ፕሊዝ›) ካያችሁ አሁንም ካለማጋነን ስምንት ያህሉ የወያኔ ትግሬዎች ንብረቶች ናቸው፡፡ አሥር ሱቆችን ካያችሁ በጣም ዝቅተኛ በሆነ ግምት ሰባቱ የወያኔ ትግሬዎች ለመሆናቸው አትጠራጠሩ፡፡ አሥር የዩኒቨርስቲ ምሩቃንን ብታዩ እጅግ ሲያንስ ስድስቱ የወያኔ ትግሬዎች ናቸው፡፡ አሥር ለማኞችን ብታዩ ከዘጠኙ ውስጥ ትግሬ ላታገኙ ትችላላችሁ፡፡ በኔ ይሁንባችና “ሠነፍ” ወይም ብልጣብልጥነት የጎደለው ‹እንከፍ› ወይም ነገን ማስተዋል የቻለ አስተዋይ ወይም ህመምተኛ ካልሆነ በስተቀር የትግሬ ለማኝ አሁን የለም ወይም ቢያንስ ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ አሃ! የሁሉ ነገር አዛዥ ናዛዥ ማን ሆነና! ትንግርት ነው ምዕመናን፡፡ በዓለም ታሪክ ቀርቶ በሲዖል እንኳ እንዲህ ያለ መድሎና ጎጠኝነት ታይቶም ሆነ ተሰምቶ አያውቅም፡፡ ያዝልቅላቸው፡፡ ግን ወዮ ለቀኑ፤ ወዮ የፈጣሪ ፍርድ ወደ ምድር በወረደ ጊዜ! ወዮ ለኢትዮጵያዊው የምፅዓት ቀን! እንዲህ ያለው ጭፍን ጉዞ ምን ሊያስትከል እንደሚችል የማያውቅ እንደብርሃኔ ግደይና እንደ‹ሐጎስ ጎይቶም› ያለ ድፍን ቅል ዜጋ ጭንቅላቱ ውስጥ ጭቃ እንጂ አንጎል የሚባል ነገር የለውም፡፡ ትንሽነት ለካንስ መድሓኒት የሌለው ክፉ ደዌ ነው፡፡ ትንሽነት ለካንስ በሰው አምሳል እንደሚንቀሳቀስ አውሬና ጭራቅ ማለት ነው፡፡ ከትንሽ አስተሳሰብ ይሰውራችሁ፡፡ በቃኝ፡፡
ግን ግን ቢበቃም ቅሉ ለነአብርሃ ደስታ፣ ለነፀጋዬ ገ/መድኅን፣ ለነጌታቸው ረዳ (የኢትዮሰማይ ድረገፅ አዘጋጅና ባለቤት)… ስንት ቆጠርኩ ይሆን? አይ፣ ደከመኝ ይቅርብኝ፤ እናም ከምር በቃኝ፡፡
አንዱ ነኝ ከአዲስ አበባ – ስም ዱሮ ቀረ!


Comment

No comments:

Post a Comment