Saturday, May 14, 2016

ሰቆቃዎ ብሔረ ዐማራ

Filed under: News Feature,ነፃ አስተያየቶች | 
  • 924
     
    Share
ከብሥራት ደረሰ
ይህን ጽሑፍ ከዐማራ ውጪ ማንም ባያነበው ይመረጣል፡፡ ምክንያቱም ዐማራን በተለዬ ሁኔታ የሚወቅስ ጽሑፍ በመሆኑ ለሌሎች ብዙም የሚጠቅም ነገር የለውም፡፡ መወቃቀስ ለዕድገት መሠረት ነው፤ ጉድፍን ለማጥራትና ጠንካራ ጎንን አጠናክሮ ለመቀጠል ሂስና ግለሂስ ጠቃሚ ናቸው፡፡ ተድበስብሶ መጓዝ ግን በግልም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ጠንቅ ነው
Displaced-Amharas-from-West-Shewa-Aremya-province-Dec-2015-1.jpg
ውድ ዐማሮች እንደምን ከረማችሁልኝ? ያለፉትን 40 ዓመታት እንዴት አያችኋቸው? የደርግ መንግሥት አስብቶ ለወያኔው የባንዳዎች ቡድን ለዕርድ አመቻችቷሁ መሄዱን ቀስ እያላችሁ በጊዜ ሂደት ስትነገዘቡ ምን ተሰማችሁ? አሁንስ እንዴት እየሆናችሁ ናችሁ? ስደቱ፣ሞቱ፣ ወያኔ ያወጀባችሁ የዘር ፍጅቱና ዐማራን ከየቦታው ማጽዳቱ፣ እስር-እንግልቱ፣ ከመንግሥት ሥራና ከንግድ – ከቤትና ከመሬት –  ከሕይወትና ከሃይማኖት፣ ከርስትና ከሚስት መፈናቀሉ፣ በጥይት መቆላቱ፣ እንዳትዋለዱና ዘር እንዳትተኩ በትግሬ ዶክተሮች መምከኑ – (አዎና በትግሬ የህክምና ዶክተር! እነፕሮፌሰር አሥራትን የገደለ መርፌ ባላገርን ማምከን ደግሞ ያቅተው እንዴ? ብዙ የሚወራረድ ዕዳ አለባቸው ትግሬ ወያኔዎች!!)፣ በማይድን በሽታ መለከፉ፣ በኑሮ ውድነት መጠበሱ፣ በማይምነት ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ መንጠራወዙ፣… እንዴት ይዟችኋል ወንድሞቼና እህቶቼ? የማይለመድ የለምና መቼም ይህን ሁሉ ዘመን አመጣሽ ግፍና በደል ሳትለምዱት እንደማትቀሩ አምናለሁ – ኑሮ ካሉት ፍሪጅስ ማለቴ መቃብርስ ይሞቅ የለም? ደርጎች “የማይለመድ የለም፤ ውስኪውንም ለመድነው “ ብለው ነበር ያኔ ካረቂ መለኪያና ከጠላ ሽክና ወደዊስኪ ብርጭቆ ሲንጠለጠሉ፡፡ እንደምታዘበው በዚህች ምሥኪን ሀገራችን ምድረ ደንቆሮ ከቀበሮ ጉድጓድ ወጥቶም ይሁን ከበረሃ ገስግሶ ሥልጣን የሚይዘውና ለመያዝም የሚቋምጠው መቼም ለዚያ ለፈረደበት ሆድ እንጂ ለመንፈሣዊ እርካታና ለሀገር ባለው ብሔራዊ ስሜት አልሆነም፡፡

No comments:

Post a Comment