Monday, May 30, 2016

አርከበ እቁባይ የራሳቸውን ሞራል እየገነቡ ነው

equbai

ዘ-ሐበሻ) “የመለስ ራዕይ የሚባል በቃ” ሲሉ እየተከራከሩ ቆይተዋል የሚባሉት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ‘ልዩ’ አማካሪ አቶ አርከበ እቁባይ “Made in Africa industrial policy in Ethiopia” የተሰኘውና በርሳቸው ስም ይጻፍ እንጂ እርሳቸው ይጻፉት አይጻፉት ያልተረጋገጠውን መጽሐፋቸውን ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማስተማሪያነት በስጦታ መልክ አብርክቻለው በሚል ዜናውን በሚያዟቸው ሚዲያዎች በማስነገር በመገባት ላይ ናቸው::
“Made in Africa industrial policy in Ethiopia” የተሰኘውና በአቶ አርከበ ስም የወጣው መጽሐፍ አቶ አርከበ እንዳልጻፉት እየተነገረ ቢሆንም ዘ-ሐበሻ ለዚህ ጉዳይ ማረጋገጫ ማግኘት አልቻለችም:: ሆኖም ግን የመጽሐፉ ጸሐፊ ነኝ ያሉት አቶ አርከበ ከ20 በላይ ለሚሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት “መጽሐፋቸው” ለማስተማሪያነት እንዲውል ማበርከታቸውን በከፍተኛ የመንግስት ሚድያዎች እንዲዘገብ አድርገዋል::
ከዚህ ቀደም በርካታ ጥልቅ እውቀትን የያዙ መጽሐፍ የጻፉ ወገኖች መጽሐፍቶቻቸውን ለክፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለማስተማሪያነት ቢያበረክቱም እንደ አቶ አርከበ የመንግስት ሚዲያ ሽፋን ሳያገኙ ቀርተዋል

No comments:

Post a Comment