Tuesday, May 31, 2016

ኢትዮጵያውያን ምን እስኪፈጠር ነው የምንጠብቀው? (ስዩም ወርቅነህ)

3618556593_4674679485


~ 2.4 ሚሊዮን የአማራ ክልል ተወላጆች በህዝብ ቆጠራ ወቅት ጠፉ
~ ከ125 በላይ ህፃናት በጋምቤላ ክልል በሙርሌዎች ተዘረፉ
~ የእምነት ነፃነት በመጠየቃቸው ብቻ የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው እስራት፣ ግርፋት፣ ግድያና እንግልት ዛሬም ቀጥሏል።
~ ላለፉት 25 ዓመታት በስርቱ ተላላኪዎች የተቃጠሉ ገዳማትና ቤተክርስቲያን ቁጥር ቀላል አይደለም።
~ ከ2000 በላይ ከብቶች በሙርሌዎች ተዘረፉ
~ ከ225 በላይ የጋምቤላ ተወላጆች በሙርሌዎች ተገደሉ
~ ከ400 በላይ የአኟክ ተወላጆች በህወሃት/ኢህአዴግ ተወላጆች በጠራራ ፀሃይ ተገደሉ
~ ከ200 በላይ ዜጎች ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ በህወሃት/ኢህአዴግ የፌደራልና የመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ
~ ከ10 ዓመት በኋላ በሚደረገው ህዝባዊ ቆጠራ የጉራጌ፣ ኦሮሞ፣ አማራና የሌሎችም ዜጎች ቁጥር ቀንሷል
~ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ከ80ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን አለቁ
~ ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ አያሌ ኢትዮጵያውያን ሶማልያ ውስጥ ሰላም ለማስከበር በሚል ተልከው ተገድለዋል። የቀድሞ ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ስንት ሰው እንደሞተ ለመግለፅ ፓርላማ ውስጥ ተጠይቀው የማሳወቅ ግዴታ የለብኝም ብለው እንቢ ማለታቸው የሚታወስ ነው።
~ አማራ ክልል ውስጥ ወላድ እናቶችን ክትባት በመስጠት እንዳይወልዱ ተደርገዋል። ያረገዙትም እንዲያስወርዳቸው ተደርገዋል።
~ ለሃገራችን የሚጠቅሙ አያሌ ኢትዮጵያውያን በሰበብ አስባቡ በእስር ቤት ታግደው ይገኛሉ።
~ ስርዓቱ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ምቹ ባለማድረጉ ምክንያት አያሌ ኢትዮጵያውያን ለስደት ተዳርገዋል። ያሰቡበት ያልደረሱትም የበረሃ ሲሳይ ሆነዋል። ሌሎችም በሜደትራኒያን ውቅያኖስ ተወስደዋል። በየበረሃው በባዕዳን ተደፍረው ለእብደት የተደራጉትና ለዘላለም የህሊና ጠባሳ እስረኛ የሆኑ ብዙ ናቸው። የዱር አራዊትና የአሳ መብል የሆኑትም ብዙዎች ናቸው።
~ 28 ኢትዮጵያውያን በISIS አንገታቸውን ተቀልተው ተገድለዋል።
~ ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ ኢትዮጵያውያን በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው Xenophobia እስከነ ህይወታቸው ከጎማ ጋር በመጠፈር ተቃጠለው ተገድለዋል። እሚከራከርላቸው አጥተው በየቀኑ የሚገደሉትም ቁጥር ስፍር የላቸውም።
~ የመን ውስጥ በተቀሰቀሰው የርስበርስ ጦርነት በስደተኛ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአየር መደብደባቸው የሚታወስ ነው።
~ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መግቢያ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዋናው ቅጂ ተሰርቆ ወጥቷል።
~ በጎንደር በኩል ለሱዳን 160 ኪሎ ሜትር መሬት ወደ ውስጥ ተላልፎ ተሰጥቷል
~ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 25 ዓመታት ወደብ አልባ ተደርጋለች
~ ላለፉት 25 ዓመታት የተገደሉትና የታሰሩ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር በውን የሚታወቅ አይመስለኝም። በቅርብ ጊዜ በተፈጠረው ተቃውሞ እንኳን ከ200 በላይ የኦሮሞ ተወላጆች ተገድለዋል፣ ከ3000 በላይ ታስረዋል፣ አያሌዎች ተደብድበዋል፣ ለስደት ተዳርገዋል።
~ በየአረብ ሃገራ በእህቶቻችን ላይ የሚደርሰው ስቃይና በደል ለሁላችንም ግልፅ ነው
~ የማንነት ጥያቄ ባነሱት የወልቃይት ጠገዴ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ኢ-ሰብዓዊ ተግባር የሚዘገንን ነው።
~ ሌላም ሌላም……..
…,……………………..……..

ይህ ሁሉ በደል አልበቃ ብሎ ምን እስኪያደርጉን ነው የምንጠብቀው??

No comments:

Post a Comment