Friday, May 20, 2016

ግርግዳ የሌለው ቤት በሩ ይቆለፋል ወይ? | ከመኳንንት ታዬ (መ..ታ )


ethiopia
የምንኖርባት አለም ሰዎች የሚተዳደሩባት የሚያስተዳድሩባትም ፤ ብበሎም  ገዢና ተገዢ ሃብታም እና ደሃ ፤እያለ ይቀጥላል ።እንዲህ ባለው ስርአት ውስጥ  የተፈቀደልንን መስመር እየረገጥን እንኖራል።በዚህ ሄደት  አንዳንዶች ቆዳቸው ሲሰፋቸውና ጫማቸው ሲያድግባቸው  እሰው መስመር ልኬት ገብተው በመርገጥ ፉርሽ ነው ይሉናል ። የረገጥነው የተፈቀደልንን መሆኑን ስናቅ ፤የለም በልኬ ነው ያለሁት ባልን ግዜ  ያልተገቡ ረጋጮች  ይጣሉን ይጀምራሉ።በዚህን ግዜ በንኪኪ የሚመጣ ጥል ይፈጠርና በቅርብ በሚያስቡና በሚያዩ ዘንድ  ጥፋተኛነታችን ሲነገረን ይኖራል።አርግጥ በዚህ ምሃል ግጭት የመነሳቱ ሁነት  አውነት ነው ። አሸናፊው  እንደ አያያዙ  ይሆናል። አብዛኛውን ግዜ እራስ ወዳዶች  ጫማቸውም  የራስ ቅላቸውም ሰፊ ስለሆነ  የሰው መስመር መርገጥ ይቀናቸዋል ።እንዲህ ካለ ስርአት እያደገ ሄዶ ሐገር ጥግ ሲደርስ  የራሳቸውንም የሰውንም መስመር መርገጥ የሚቀናቸው አስተዳዳደሪዎች ይፈጠራሉ። የዛኔ ሃገርም ፤መኖሪያ ሰፈርም ፤መኖሪያ ቤትም ፤በልኩ የሚረግጡ ሰዎች ባለቤቷ አይሆኑም ።ምክንያት ከላይ ሲውርድ እንደመጣው አይነት የእድገት ደረጃ  ባለቤቱ  ሆኖ የተፈጠረው ግለሰብ ነውና ።
ለመንደርደሪያ ታህል ይህን ካልን ግርግዳ የሌለው  ቤት በሩ ይቆለፋል ውይ ? ወደሚለው ርእስ  እንዲህ እንዝግም። በዚህ ርእስ ሰንሰለት  አጥርና በር ብሎም ግርግዳ የሌላት ሃገራችንን እናስታውስና እንዲህ እንበል። መሪዎቻችን ሊያኖሩን አልያም እየቆጠሩ ህዝብ አለ ሊሰኙበት ሃገሪቷን ከተረከቡ  ብዙ ዘመን አለፈ።ቁጥሩን መጥቀስ አስፈላጊነቱ አላመንኩበትም። ለማውራት የፈለኩት ከታች ጀምሮ ከሆነ እለቀ መሳፍርት  ወረቀት አይበቃም። ስለዚህ በቅርብ ከተፈጠረው  ከጋንቤላ እንነሳ ።መገደል ብርቃችን አደለም ።ምን እሱ ብቻ ገዳዮቻችንንም  መቃወም ያስገድላል።ይህ አይነት አስተዳደር ለማንኛውም  አለም ላይ ለሚገኝ ፍጡር  ያማል ።በር የሌላት ሃገር፤ህዝቦቿ በሄዱበት እየተዋረዱ  የሚሸማቀቁባት ሃገር ፤ ሃገር ፤ሀገር ……፤እያለ በየማዝናቱ አሳፋሪና አስፈሪ ነገሮች ባለቤት የሆኑ ህዝቦች ፤ስሟ  ኢትዮጲያ በተባለ ሃገር እንኖራለን። በዚህ ምክንያት  ሃገር ስም  የያዙትስ ትልቅናቸውና  ትንሽ ልብ ባለው  መንግስት  ከቶ ይፈሩ ይሆናል ።እንዴት  የአንድ ብሔረስብ ወሮ በላ ጎሳውች የአንድን ሐገር  ህዝብ ገድለውና ልጆ ቻቸውን ከብቶቻቸውን  ወስደው ሲያበቁ  በድርድር ለማስመለስ በሚል ደካማ ሃሳብ ይኖራል ። አረ እንደውም  የጋምቤላው አስተዳዳሪ እንዳሉት ልጆቹ ይመለሱ እንጂ ከነኚ ጋር ማን ይነጋገራል አይነት ነው። በቃ ኢትዮጲያዊ እንዲህ ነው ።አለቀ ።ይህ በርግጥ ከሙት ባህር አጠገብ  የተቀመጠ ሙት አስተዳደር ነው እንጂ፤ በእውነቱ ስም ያላት ሀገርን የሚያስተዳደር መንግስት  ከቶ ሊዋጥለት አያስፈልግም።አስከመቼስ  የታጠቀውን መሳሪያ  የገዛ ህዝቡን የሚያስፈራራበት ይሆናል ።ለሚቃወሙተስ ስንት አስር ቤት? ስንት አሳሪ ፖሊስ?  ስንት ፈራጅ ዳኛ? ስን ስንት ስንት ያስፈልጋል። በአገዛዝ ደረጃ  ለተቀመጡት  ባለዱላዎቸስ በስልጣን   የተቀመጡ መሪዎች ጉልበታችሁን እንዴት አሳንሰው እንደሚመለከቱት  አለመገንዘባችሁ ምን ቢጠፋችሁ ወይስ ምን ብታጡ ነው።ትልቅነት ነገን  ማየት እንጂ  ዛሬ ላይ በድንግዝግዝ እየኖሩ በዳበሳ መሄድ አደለም።
ማንነታችን እኛነታችንን የምናፅበት መስመር የተሰራልን ያለሙግት  የምንኖርባት ሐገር ባለቤቶች ነን።ትልቅነታችን ሲያስመሰግነንና ሲያስከብረን ኖረን የእኛ ባማይሏት ገዢዎች መስመሯን ስታ  የነገ ባለ እራቁት ሐገር ለማድረግ ደርሻዬ ከሚሉት ባለፈ ሐገርን በገፈፋ እና በብትር ለማስተዳደር መሞከር ክብሩ ምን ያህል ነው?።ሕዝቦች መሪዬ የሚሉት ሲጠፋ እንደመንደር ሰው እየተከተሉ የሚሰድቡት ባለስልጣን ማየት የ25 አመቱ የመልካም አስተዳር  ውጤት  አማራጭ የሌለው አድገት  መሆኑን የተቀረው አለም እንዴት የሚያው ይመስላቸውኋል?።ህዝቦች ብዙዎች ናቸው ያስፈራሉ።የመንግስት ባለስልጣናት ጥቂቶች ናቸው ይፈራሉ።ምክንያቱም የኔ የሚሉት  ሀገር በስማቸው አለችና ነው።ከሀገሩ ክብር  የሸሸ ባለስልጣን ከሚመራው ህዝብ ለሱ ብሎ የተቀመጠ ባለሞኖሩ ዛሬ የምናነየውን  አሰዛዥ  እጣ ፋንታ  ሁሉም በየተሰለፈበት መስመር ሲፈፅም ማየት ነው ።ከወንበሩ በስተቀር በስፋት  የተለየ ነገር  ባለመኖሩ ወደታች በመውረድ በትልቅ ደረጃ አሰራር ያለት ሐገር ግለሰቦች  ከሀገር እንዳይወጡ ፓስፖርታቸው  ዘይት ነካው በሚል ጎስቋላ ምክንያት  ብሎም  በየአይሮፕላን ጣቢያ ተቀምጦ ግለሰቦችን ከስራቸው በማጎሳቆል  ማሰቃየት  ይህ የወንበርን ስፋት ከማየት የመጣ የአንቶ ፈንቶ አስተዳደር  ስርአት  ነው። የሚያሳዝነው  ወደፊት ለመሄድ ከኋላ ስንት ሜትር እንዳለፉ አለማስታወሳችሁ ነው። ዛሬን  በዚህ ስርአትና ውርደት ለመኖር ከሆነ ትላንት የታገላችሁት ሃሰባችሁ ረፍዶበታል ።አልተኛችሁም ለማለት ከሚመጣው  የጋራ ክፉ ነገር  ወንበራችሁ  ላይ  እንዳይነጋ የማታዋን ፀሃይ ተጠቅሞ  ከግርግር መንግስት  የሽግግር መንግስት ብታቋቁሙ ለቤቱ ግርግዳ  ለመዝጊያውም በር  ከህዝቡ ጋር ሆናችሁ ትሰራላችሁ ማለት ነው ።
ቸር እንሰንብተ

No comments:

Post a Comment