Thursday, May 19, 2016

የቤኒሻንጉል ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አህመድ ናስር አረፉ

ahmed


(ዘ ሐበሻ) የቤኒሻንጉል ክልልን ከ2001 ጀምሮ በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩትእና የአማራን ሕዝብ ለይተው ከቤንሻንጉል በማፈናቀል ቤት እና ንብረታቸውን እንዲያጡ በማድረግ ወንጀል ከሚጠየቁ ባለስልጣናት መካከል አንዱ የነበሩት አቶ አህመድ ናስር ሕይወታቸው ማለፉ ተሰማ::

ከሃገር ቤት የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙትና የመንግስት ሚዲያዎችም እንደዘገቡት የርዕሰ መስተዳደሩ የቀብር ስነስርዓት አሶሳ ከተማ ውስጥ ይፈጸማል::
የኢህ አዴግ ተለጣፊ ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆኖእው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (ቤጉህዴፓ) በምክትል ሊቀመንበር የነበሩት አቶ አህመድ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በእርሻ ምህንድስና፤ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በቻይና ሆሃ ዩኒቨርሲቲ በውሃ ምህንድስና የተከታተሉት አቶ አህመድ ናስር በአሁኑ ወቅት የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስቴር በቀድሞው ግብርና ገጠር ልማት ሚኒስትር ዴኤታነት ማገልገላቸውን የመንግስት ሚድያዎች ዘግበዋል::
የበሽታው ዓይነት ባይገለጽም አቶ አህመድ ለረዥም ጊዜ በውጭ እና በሃገር ቤት ህክምና ሲከታተሉ መቆየታቸው ሲሰማ ሕይወታቸው ሲያልፍም የ51 ዓመት ጎልማሳ እንደነበሩ የሕይወት ታሪካቸው ያስረዳል::
በ1957 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ ጠዴቻ መልካ ቀበሌ የተወለዱት አቶ ናስር የአንድ ልጅ አባት ነበሩ ተብሏል::
አህመድ ናስር ከ2 ሺህ በላይ አማሮች ከቤንሻንጉል ክልል እንዲፈናቀሉ ካደረጉ በኋላ መጨረሻ ላይም “እነዚህን አማሮች ያፈናቀልነው በስህተት ነውና ወደ ክልላችን ይመለሱ:: አማሮቹ እንዲወጡ የተደረገው በበታች ባለስልጣናት ግብታዊነት ነው” በማለት ይቅርታ መጠየቃቸው በወቅቱ በዘ-ሐበሻ በኩል መዘገቡ አይዘነጋም:

No comments:

Post a Comment