Sunday, April 10, 2016

ይህ ሁሉ ወንጀል እየተሠራ ያለው በሁለቱም መሪዎቻችን ግፊት ነው!


ምሕረቱ ዘገዬ
በተለይ ካለፉት 25 ዓመታት ወዲህ ዓለምን የሚያስደምም ወንጀል በሀገራችን ውስጥ እየተሠራ ይገኛል፡፡ በዓለማችን የእስካሁንም ይሁን የወደፊት ታሪክ በፍጹም ያልታዬና ሊታይም የማይችል ወንጀል ወያኔ ትግሬዎች እንደልባቸው እየሠሩ ናቸው፡፡ እነዚህ በጣት የሚቆጠሩና የዋናው ዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ቡድን አባላት የሆኑ ጥቂት ትግሬዎች እየሠሩት ያለውን የከፋና የከረፋ ወንጀል ሁለቱም መሪዎቻችን በሚገባ ያውቃሉ፡፡ ነገር ግን ሁለቱም መሪዎቻችን እልህ የተጋቡና አንዳቸው በአንዳቸው ጣልቃ ላለመግባት የወሰኑ ይመስላል በድርድርም ይሁን በመሸናነፍ ቅራኔያቸውን አስወግደው እኛን ሰላም ሊሰጡን አልቻሉም ወይም ምናባልት ጊዜው ገና ነው፡፡ የዝኆኖች መራገጥ ለሣር እንደማይበጅ ሁሉ እኛም በነሱ ሰበብ እየተደቆስን አለን፡፡
እነዚህ ሁለት መሪዎች የሰማይና የምድር ጌቶች ናቸው፡፡ የሰማዩ ጌታ በኔ ግንዛቤ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሲሆን የምድራችን የወቅቱ ገዢ ደግሞ የ13 ቁጥር እመቤት ልዕልት አሜሪካ ናት፡፡ ሁለቱ ናቸው ዓለምን የፊጥኝ አስረው በፉክክር አሣራችንን እያበሉን የሚገኙት፡፡ በነዚህ በሁለቱ መሪዎቻችን ፊትና ግፊት ነው እንግዲህ ከዚህ በታች የምገልጸው ወንጀል በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተፈጸመ የሚገኘው፡፡
ሰሞኑን ወደ ማርካቶ የምሄድበት ጉዳይ ነበረኝ፡፡
ከማርካቶ በፊት ወደ ጎንደር ጎራ ልበል መሰለኝ፡፡ ጎንደር ክፍለ ሀገር ውስጥ ወልቃይትና አካባቢው ቀደም ካለ ጊዜ ጀምሮ ወያኔ ከትግራይ በርካታ ትግሬዎችን እያመጣ በመሰግሰግ የሕዝቡን አሰፋፈር እየለወጠው እንደነበረ የአደባባይ ምሥጢር ነው፡፡ ጎንደሬውን ወልቃይቴ በማንኛውም ዘዴ ከአካባቢው እያፈናቀለና በግልጽም በሥውርም እንደዐይጥ ጨፍጭፎ እየገደለ  የጎንደርን ነባር ይዞታዎች በትግሬ መሙላቱና የጎንደርን መሬት ወደትግራይ ክልል በጉልበት ማካተቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህ ተፈጥሯዊ ያልሆነ ሰው ሠራሽ የሕዝብ አሰፋፈር አሁንና ዛሬ ብቻ ሣይሆን ነገና ከነገ ወዲያ ምን ዓይነት ሀገራዊና ክልላዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ዕድሜ የሰጠው ኋላ ላይ የሚያየው መሆኑ እንዳለ ሆኖ በወያኔ ሤራ እየተከናወነ ያለው አጠቃላይ ወንጀል ሲዳሰስ ግን ነውረኛ ድርጊቱ በአንድ አካባቢ ብቻ የተወሰነ ሣይሆን መላ ሀገሪቱንና የፌዴራል ተብዬውን የይስሙላ መዋቅር ሁሉ በስፋት የሚያዳርስ ትልቅ የክፍለ ዘመኑ ወንጀል ሆኗል፡፡
የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን የሥራ አቀጣጠር ስናይ ትግሬ ዜጋ አጥተው ካልሆነ በስተቀር ሌላውን በምንም መንገድ ሥልጣንና የጥቅም ቦታ ላይ እንደማያስቀምጡና ሀገሪቱ የትግሬዎች ጥገት መሆኗን ከመነሻው እናውቃለን፡፡ እነሱ ሀፍረትና ይሉኝታ ባለማወቃቸው እኛው ስለነሱ እየተሸማቀቅንና አንገታችንን እየደፋን መኖር ከጀመርን 25 ዓመታችን ሆነ፡፡
የትግሬዎች ቁጥር ከኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር አንጻር ሲሰላ ዱሮ 6 በመቶ ነበር፡፡ አሁን ምናልባት ሌላውን በተለይም ዐማራውን እያመከኑና በሚችሉት ሁሉ እየጨፈጨፉ ስላሳነሱት፣ በሌላም በኩል የነሱን ዘር በሌሎች ላይ ለማንገሥ ባላቸው ቁርጠኝነት የተነሣ የወሊድ መከላከያ የሚባል ሲያልፍ አይነካቸውም ስለሚባል ያ አኃዝ ዛሬ ላይ ተለውጦ 10 በመቶ ሆነዋል ብንል ከዚህ አጠቃላይ ሕዝብ የወጡ ጥቂት ወራሪዎች ናቸው ከነጀሌያቸው የመላዋን ኢትዮጵያ ሀብትና ሥልጣን በግል ተቆጣጥረው የሚገኙት፡፡ ይህ በጣም የታወቀና ፀሐይ የሞቀው እውነታ ስለሆነ ወደ ዝርዝሩ መግባት አስፈላጊ አይደለም፡፡
እንጂ በተለይ አመራርን በሚመለከት ጦሩን ሙሉ በሙሉ፣ ደኅንነቱንና ፖሊሱን ሙሉ በሙሉ፣ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ፣ ሕይወት (እስትንፋስ) ባይኖራቸውም ፍርድ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ፣ የክልል መንግሥታት ተብዬዎችን ሙሉ በሙሉ፣ የልማት ፕሮጀክቶችን ሙሉ በሙሉ፣ የማዕድንና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ምንጮችን ሙሉ በሙሉ፣ የመንግሥት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ፣ የገቢና ወጪ ንግዶችን ሙሉ በሙሉ፣ እርሻና ኢንዱስትሪን ሙሉ በሙሉ፣ ሪል እስቴትና ቤት ግንባታን ሙሉ በሙሉ፣ የመሬት አስተዳደርን ሙሉ በሙሉ፣ ማዘጋጃና ከፍተኛን እንዲሁም የወረዳ አስተዳድርን (በጭምብል እንደራሴዎቻቸውና ኮንዶማዊ ምስለኔዎቻቸው ጭምር) ሙሉ በሙሉ፣ ኪነ ጥበብንና ሙዚቃን ሙሉ በሙሉ፣ የመጻሕፍት ኅትመትንና የትምህርት መሣሪያዎች ምርትን ሙሉ በሙሉ፣ የትምህርት ተቋማትንና መያዶችን ሙሉ በሙሉ፣ የሃይማኖት ተቋማትንና አመራሩን ሙሉ በሙሉ፣ የዜጎችን የማሰብ፣ የመናገር፣ በሕይወት የመኖር፣ የመንቀሳቀስና ያለመንቀሳቀስ መብት ሙሉ በሙሉ፣ … ከሰማይ በታች ሁሉንም ነገር ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውን መናገር በተቻለ ነበር፡፡ እነሱ የሌሉበትና ራዳራቸውን ያልተከሉበት፣ በቀጥታም ይሁን በተዛዋሪ የማይቆጣጠሩት ነገር የለም – ፀሐይዋና አየሩም ሣይቀሩ በነሱ ቁጥጥር ሥር ሳይገቡ አይቀርም፤ የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና አሁን አንድ ነገር ቀርቷቸዋል ብዬ እማስበው እኛ ባሎች ከሚስቶቻችን፣ ሚስቶቻችን ደግሞ ከኛ ከባሎቻቸው የምናገኘውን የወሲብ እርካታ በየጭኖቻችን መካከል በሚያስቀምጡት ቆጣሪ ወይ ባልቦላ በመለካት ወርኃዊ ግብር ማስከፈል እንዳይጀምሩ ነው – በሌላ የገቢ ርዕስ በኅቡዕ መድበው እስካሁን የማያስከፍሉን ከሆነ ነው እሱንም፡፡ የሚገርመው ይህን ሁሉ ወያኔያዊ ወንጀልና የአካይስት ተግባር ሁለቱም መሪዎቻችን ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ የምድሪቱ ንግሥት ዓላማዋና ተልእኮዋም ስለሚታወቅ በበኩሌ የርሷ አይገርመኝም፡፡ ከቁጥር ዕውቀቴ አንጻር የ13ንም ሆነ የ666ንና መሰል ቁጥሮችን መነሻና መድረሻ እረዳለሁና በነሱ ምክንያት እንዲህ እንዲህ ሆን ብዬ አላማርርም፡፡ እኔ የሚያሳስበኝ ይልቁንስ ባለብዙ ዐይኑ ፈጣሪያችን ለባለአንድ ዐይኑ የጨለማው ገዢ አስረክቦን በነሱ ልጆች ይህን ያህል እንድንሰቃይ ፈቃዱ ሆኖ የመገኘቱ ክፍለ ዘመናዊ ምሥጢር ነው፡፡ እርግጠኛ ነኝ – ከኛ በኩል ትልቅ የምናወራርደው ታሪካዊ ስህተት ፈጽመን መሆን አለበት! የወላጆቻችንን ታሪክ እንመርምርና ጌታ ምሕረቱን እንዲልክልን እንማጠነው፡፡ አለበለዚያ በዚህ አያያዝ ዘር ላይተርፍ ነው፡፡ የሰይጣን መንጋ ተለቆብናል፡፡ በሀገራችን ብቻ እንዳይመስላችሁ – በሌላውም፡፡
ብዙውን ጊዜ ማርካቶ እሄዳለሁ፡፡ ዱሮ በጉራጌ ተጥልቅልቆ አይ ነበር፡፡ እንደዚያም የሆነው ጉራጌዎች በንግድ ጎበዞች ስለነበሩ የዱሮዎቹ ብልህ የሀገር መሪዎች ባመቻቹት መንገድ ነበር  – ለሸርና በሸር ሣይሆን ለሀገር በሚጠቅም ተፈጥሯዊ መንገድ፡፡ ወያኔ ሀገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ ግን ያ ሁኔታ በእጅጉ ተለውጦ ሌላ መልክ ይዟል – በአሣፋሪነቱ ወደር የሌለው መልክ፡፡
ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ዱሮም ትግሬ ይበዛበታል፡፡ ወደላይ ሂዱ – ወደ መስጊዱ – ወደ ጎጃም በረንዳ(አሁን ትግሬ በረንዳ ቢባልስ?) – ወደሰባተኛ – ወደ ጭድ ተራ – ምን አለፋችሁ ወደየትም ሂዱ ማርካቶ ስትገቡ መቀሌ የገባችሁ ያህል ይሰማችኋል፡፡ ይህ ዓይነቱ የአንድ ነገር ጣልቃ ገብት በግልጽ የሚንጸባረቅበት የዜጎች መፈናቀልና በአንድ ዘር ብቻ የመተካት ሂደት አሳሳቢ ነው፡፡ አሁን አሁን እኔ ማርካቶ ስሄድ በእጅጉ እደነግጣለሁ፡፡ ለነገሩ አዲስ አበባ ውስጥ የትም ስሄድ የማየው የትግሬዎችን መብዛት ነው፡፡ ይቅርታ አድርጉልኝና በየቦታው የማየውን ይህን የሀገሬን ሰዎች ብዛት ስታዘብ በተፈጥሯዊ መዋሰብ የተገኙ ስለመሆናቸው እጠራጠራለሁ፡፡ ሌላው ወዴት እየገባ እንደሆነ ማወቅ ባለመቻሌም እጨነቃለሁ፡፡ በከተማዋ ከዳር እዳር ብትሄድ ንግዱንና መላውን ማኅበራዊ እንቅስቃሴ የተቆጣጠሩት በአብዛኛው ትግሬዎች ናቸው – ሆቴሎችንና መዝናኛ ቤቶችንማ ተዋቸው – ሌላ ዜጋ በሀገሪቱ ያለም አይመስል፡፡ እኔ ማንም ቢቆጣጠር ችግር የለብኝም፡፡ ነገር ግን ሌላውን አፈር ድሜ እያስጋጡና መርዝ ጠጥቶ ወይም በገመድ ታንቆ እንዲሞት በኪራይና በግብር እያበሳጩ አንዱን ወገን ብቻ ያለውድድር ማንገሣቸው ወንጀል ብቻ ሣይሆን ኃጢኣትም ጭምር ነው፡፡ እግዚአብሔር ከ“እንቅልፉ ሲነቃ” ብዙ የሚያወራርዱት ሒሣብ ተዘፍዝፎ ይጠብቃቸዋል፡፡ ሰው የዘራውን ያጭዳልና፡፡
እንደምንም እየተውተረተረ የምታገኙትን የማርካቶ ጉራጌ ጠጋ ብላችሁ ብትጠይቁት የሚነግራችሁ ሁሉ ጉድ ነው፡፡ ወያኔ ትግሬዎች በሌሎች ዜጎች የሚሠሩት ወንጀል ተወርቶ አያልቅም፡፡ ለምሳሌ በዓመት 15ሺህ ብር ለማይገኝባት የሱቅ በደረቴ ዓይነት ሚጢጢዬ ሱቅ ወያኔዎች ከንግድ ጽ/ቤት ውሾቻቸውን ‹ጃዝ ቡቺ› ብለው ይልኩና 150ሺ ብር ዓመታዊ ግብር ያስመድቡበታል – ወገብ ቆራጩ የቤት ኪራይ ሳይነሳ ነው እንግዲህ፡፡ ያኔ ያ ጉራጌ ያለው አማራጭ ሁለት ቢበዛ ሦስት ብቻ ነው፡፡ አንደኛ ራሱን ማጥፋት፣ ሁለተኛ ብዙ ጉቦ ከፍሎ ያን የገንዘብ ክምር ማስቀነስ፣ ሦስተኛ በረንዳ አዳሪ መሆን፡፡ በዚህ ሁኔታ ራሳቸውን ያጠፉ፣ ወደበረንዳ ሕይወት የተዛወሩ ወይም ዐብደው ጨርቃቸውን የጣሉ ሞልተዋል፡፡ በነሱ ምትክ ታዲያ እዚህ ግባ በማይባል የቦታና የቤት ኪራይ በዚያ ላይ አላንዳች ግብር ወይም ለወጉ ያህል ብቻ ትንሽ እንዲከፍል ተደርጎ ትግሬው ገብቶ ይነግዳል – (ይህን ድርጊት ጤናማ ነን የምትሉ ትግሬዎቸ እባካችሁ በጥሞና አስቡትና “ይሄ ነገር በውነቱ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ለወደፊት ሊያቀባብረን ይችላል ወይ ብላችሁ?” አጢኑት፤ ራሳችሁን በሌላው ዜጋ ጫማ ውስጥ አስገቡና “በነሱ ቦታ እኔስ ብሆን ኖሮ ?” ብላችሁ እንደ አንድ አስተዋይ ሰው አስቡት፤ ይህን ስታደርጉ ግን ከሆድና ከዘረኝነት ተፅዕኖዎች ራሳችሁን ነፃ አድርጋችሁ መሆን አለበት)፡፡ አንድ ሰው የዐርባ ቀን ዕድሉ ቀንቶት ትግሬ ሆኖ ከተፈጠረና ኅሊናውን በዘረኝነት ካሳወረ በአሁኑ ወቅት ምንም ምድራዊ ችግር የለበትም – ከገንዘብ አኳያ ማለቴ ነው፡፡ ካለቫት ቢነግድ የሚደርስበት ነገር እንደሌለ ስለሚያውቀው ደረቱን ነፍቶ ነው ዕቃውነን ሰጥቶህ ገንዘቡን አለደረሰኝ ይዘህ ከሱቁ ውልቅ እንድትል በዐይኑ የሚሸኝህ፡፡ ከውጭ የምትመጡ ሰዎች በትግሬና በሌላው ዜጋ መካከል ያለው ልዩነት ቦሌ አየር ማረፊያ እንደደረሳችሁ አፍ አውጥቶ ሲናገር ትሰማላችሁ፡፡ አይ፣ ምነው ሸዋ! ሰው መሆን እንጀምር እንጂ እናንተ፡፡ እስከመቼ ደንቆሮና ዐይነ ሥውር ሆኖ መኖር ይቻላል? አንገት የተፈጠረውስ ዞሮ ለማየት አይደለምን? አብረን እንደነበርን አብረን እንኖር ይሆናልና እናስብበት ጎበዝ፡፡ ወረት አላፊ ነው፡፡ ጥጋብ አላፊ ነው፡፡ ሰው ሟች ነው፡፡ ሥርዓት በሥርዓ ይተካል፡፡ ቋሚ ነገር የለም፡፡ ዮዲት ጉዲትና ግራኝም ታይተው እንደበራሪ ከዋክብት በቅጽበት አልፈዋል፡፡ ታዲያ ተጋሩ ወንድሞቼ ከታሪክ ተምረን ለምን አንጨምትም እነዚህን ጉግማንጉጎች እንራቃቸው፤ እንኮንናቸው፤ እንታገላቸውና የጋራ የሆነ ሥርዓት እንትከል፡፡ በቃ፡፡ እሹሩሩ ይብቃን፡፡
ማርካቶ ውስጥ ስሙን ከድር ወይም ዘበርጋ ወይም ፈይሣ ሲሉት ትሰማለህ፡፡ ዘወር ብሎ ከጓደኞቹ ጋር ሲነጋገር ግን በትግርኛ ነው፤ ሲያስመስል እንጂ ትግሬ ነው፡፡ እስስቶች መልካቸውን እንደሚለዋውጡ ወያኔዎችም ስማቸውንና እንዳስፈላጊነቱም ሥራቸውን እንደየአካባቢው በመለዋወጥ ኢትዮጵያን መቦጥቦጡን፣ ሌሎች ዜጎችን ማፈናቀሉንና መከራ ውስጥ መክተቱን በስፋትና በጥልቀት ቀጥለዋል፡፡ ሁለቱ መሪዎቻችንም ተፋጠዋል፤ ምናልባት በቅርብ ይለይላቸውና አንዳቸው አሸናፊ ሌላኛቸው ተሸናፊ ይሆኑ ይሆናል፡፡ እኔ በበኩሌ ይህን አስገራሚ ትርዒት በጉጉት ከሚጠባበቁ የዓለም ዜጎች አንደኛው ነኝ፡፡ ለማንኛውም የሥጋ ፍላጎትን መቆጣጠር ተስኖት በወንድሞቹ ሞትና አጠቃላይ ኪሣራ የሚደሰት ወገን የማይኖርባትን ኢትዮጵያ ሳላይ እንዳልሞት እጸልያለሁ፡፡ ጌታ የሚሳነው ነገር የለምና ምኞቴን እንደሚያሳካልኝም አምናለሁ፡፡

No comments:

Post a Comment