Tuesday, April 5, 2016

በአምቦ ምንም ባላጠፋው ወንጀል ተደብድቦ ለአልጋ ቁረኛ የነበረው ወጣት ሕይወቱ አለፈ


rip
ከየኔሰው ገብሬ
በፍቶው ላይ የምትመለከቱት ለግላጋ ወጣት ተክለ ቶማ ይባላል። የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሶሽኦሎጅ ድፓርትመት 2ኛ ኣመት ተማሪ ነበር ። ህዳር ወር መጨረሻ አካባቢ በኣምቦ ዩኒቨርሲቲ በተነሳው የተማሪዎች ተቃውሞ ተያይዞ ምንም ባላጠፋበት ኣፍነው ከያዙ በኋላ የአጋዚ ወታደሮች ተራ በተራ እየተፈራረቁ ከፍተኛ ድብደባ አድርሰውበት ላለፉት 4 ወራት የኣልጋ ቁረኛ ሆኖ ከቆየ በኋላ መጋቢት 24 ህይወቱ ማለፍ ችሏል ።
ደማችን እንድ እስከሆነ ድረስ ሰብአዊ ፍጡር ሁሉ ይህንን አረመኔያዊ ድርጊት በጋራ ማውገዝ አለበት ። የልጁ ቤተሰቦች ምንም አይነት መረጃ እንዳይሰጡ ከሞትና ከህይወት አንድ አንድመርጡ የሚል ማስጠንቀቂያ ስለተሰጣችሁ ዝም ብለዋል ። ገዳዩች ለፍርድ እንዲቀርቡ ። ምስኪን ቤተሰቦቹ ተገቢ ካሳ እንዲከፈላቸው በጋር እንጩህ።

ፍትህ ለወጣት ተክለ ቶማ ቤተሰቦች ።
የወጣቱ ትውልድ ቦታ ዳውሮ ሎማ ወረዳ ደቡባዊ የኢትዮጵያ ክ/ሃገር ነው። ደማችን አንድ ነው ።

ዋይታ በጋራ እናሰማ

No comments:

Post a Comment