Saturday, April 30, 2016

ደቡብ ሱዳን ከ125ቱ ኢትዮጵያውያን ህፃናትና ሴቶች 32ን ከአጋቾቹ ተረከብኩ አለች – 93ቱ የት ናቸው? * የጋምቤላው ክልል ፕሬዚዳንት መረጃው የለኝም አሉ

Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች | 

Gambela

(ዘ-ሐበሻ) ከሁለት ሳምንት በፊት የሙርሌ ጎሳ አባላት ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያንን ገድለው 125 የሚሆኑ ህፃናትን እና ሴቶችን አፍነው ከወሰዱ በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት ‘ሕጻናቱ ያሉበትን ቦታ ደርሼበት ከብቤያለሁ” የሚል ዜና አሰምቶን ነበር:: ከበባው ቀናት አስቆጠረ:: ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን የት አሉ? እያሉ ሲጠይቁ ከረመ:: ያሉበትን ቦታ ከብቤያለሁ ያለው መንግስት ልጆቹን ለማስለቀቅ ድርድር ውስጥ ገባሁ ይለን ጀመር::
ዛሬ አሶሲየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ደግሞ ከታፈኑት 125 ህፃናትና ሴቶች መካከል 32ቱን የደቡብ ሱዳን መንግስት ማግኘቱን አስታውቋል:: የደቡብ ሱዳን ቦማ ግዛት አስተዳዳሪ አቶ ኦጋቾ ቻን ሊኩአንጎሌ በሚባል ሶስት መንደሮች ህጻናቱን እንደተረከቡ ሲገልጹ በቅርቡም 32ቱ ህፃናት ወደ ጁባ ሄደው ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ ሲሉን አስተያየታቸውን ለአሶሲየትድ ፕሬስ ሰጥተዋል:: እንደ ዜናው ዘገባ አፋኞቹ ህፃናቱን ሊኩአንጎሌ የተባለው መንደር ውስጥ ህጻናቱን ሳይለቋቸው አልቀረም::
እኚሁ አገረ ገዢ ቀሪዎቹን 93 ህፃናትና ሴቶች ካሉበት ቦታ ለማስለቀቅና ለማሰባሰብ እንሞክራለን” ብለዋል::
በሌላ ዜና ዋሽንግተን ፖስት እንደዘገበው የጋምቤላው ክልል ፕሬዚዳንት ጋትሉክ ቱት ስለልጆቹ መገኘት የሚያውቁት መረጃ የላቸውም:

No comments:

Post a Comment